Get Mystery Box with random crypto!

የፍቅር ጎጆ

የቴሌግራም ቻናል አርማ yefiker_gojo — የፍቅር ጎጆ
የቴሌግራም ቻናል አርማ yefiker_gojo — የፍቅር ጎጆ
የሰርጥ አድራሻ: @yefiker_gojo
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 479
የሰርጥ መግለጫ

Call us if you want to promote your product and service !!
FOR ANY PROMOTION
CONTACT ☎️ 251923715770 📩 @AbenaG

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 12

2023-03-15 12:23:16 ስለ እኔ ያገኘሁት አስገርሞኛል

የ ተወለድበትን ወር መርጠው ስለ ራሶ ምን እንደሚል ተመልከቱ
626 viewsМι¢кєу Eℓ, 09:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-14 09:31:43
እባክሽ ፍቅሬን ጠብቂልኝ


,,,,,,,,,,, ,,,,,,,,,,
        •═••• •••═•
  
    
@Yefiker_Gojo    ,, @AbenaG
━━━━━✦ ✿ ✦━━━━━
     
3.0K views♕𝙰𝙱𝙴𝙽𝙸 𝙹𝙲❥̟, edited  06:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-12 21:52:51 ሁለት
፨፨፨
አስረኛው ቀን ላይ ደወለችለት። እሱ መሆኑን ነግሯት እሷ መሆኗን ከነገረችው ቡኃላ ያለበትን አድራሻ ብቻ እንዲልክላት ጠዬቀችው። ሳይግደረደር ላከላት። ማመን አልቻለም። ቤቱ ገብታ እየተዟዟረች እያያት ራሱ እውነት ናት ብሎ መቀበል ከብዶታል።

<<ጠፋሽኮ!>> አለ ብዙም ግድ የሌለው ለመምሰል እየሞከረ።
<> አለችው ድንገት ቶኗን እየቀዬረች።
<<ማለት?>> አለ ለማለት የፈለገችው ሳይገባው ቀርቶ ሳይሆን እርግጠኛ መሆን ፈልጎ።
<<ስምንቱን ቀን አላነበብኩትም ነበር በስራ ምክኒያት። ትላንት እንቅልፍ እንቢ ብሎኝ አንዱን ጀምሬ ማቆም አልቻልኩም። ሲሪዬስሊ! እንደዚህ ቆንጆ ፅሁፍ ካነበብኩ ረጅም ጊዜ ሆኖኝ ነበር። እየቀለድክ አይደለም። አሁን አንድ ነገር ብቻ ልልህ ነው እዚህ ድረስ የመጣሁት!>>

<<ምን?>> አለ...ሁሉም ስሜቶች አንድ ላይ እየተሰሙት።

<<በርግጠኛነት ሌሎችም ፅሁፎች አሉህ! በልዑል ሞት ይዤሀለሁ አስነብበኝ?! የምትሰጠኝን እስከማነብ ድረስ ደግሞ ሌላ ፃፍ።>>
ራሱ በሰራው ገፀባህሪ ስም እየለመነችው ነው?
<> አለ በእርካታ ስሜት።
<<ምኑን ነው ያወቅከው?>>
<<አላነበብሽው ሆኖ እንጂ ብታነቢው እንደዚህ እንደምትሆኝ እርግጠኛ ነበርኩ። ልሞትብሽ ስል ለጥቂት ነው የደረሽልኝ!>> አለ በጭንቀት እየተነፈሰ።
<<ቆይ አንተ የሰው አስተያዬት ለምን ይሔን ያህል ግድ ይሰጥሀል?>>
<<እኔ ያደኩበት አከባቢ በቀላሉ ስለማይገኝ የቫይታሚን ላቭ እጥረት አለብኝ።>>
<<የልዑልን ዲያሎግ አትኮርጅ!>>
<<እንዴ ሉላ'ኮ ራሴ የቀረፅኩት ገፀ-ባህሪ ነው!>>  አለ እየሳቀ።
<<ሁለተኛ ሉላን ገፀባህሪ ነው ስትል እንዳልሰማህ። የምር እጣልሀለሁ። ደግሞ ከሁሉም በላይ የሱን ቀጣይ ክፍል ነው ማወቅ የምፈልገው።>>
<<ገና አልተፃፈም።>>
<<ፃፈው ፃፈው። እንዲያውም እዚህ ድረስ የመጣሁት ለሱ ብዬ ነው።>>
<<ቆይ ምኑ ነው የገረመሽ?>>

<<<ከዛ ሌላኛው ስቶሪ ላይ በልጅነቱ ብቻዋን ያሳደገችውን እናቱን የሰፈር ሰዎች "ቡዳ ነች" በሚል አሉባልታ ምክኒያት በደቦ ደብድበው እንደገደሉበት....ከዛ ደግሞ ጠፍቶ አዲሳባ ከገባ ቡኃላ በማደጎ ቤት በብቸኝነት እንዳደገ ሳውቅ ምናምን አንጄቴ ተንሰፈሰፈለት። ለካስ ለዛ ነው የሰው ወሬ የሚጠላው...ለካስ ለዛ ነው በሁሉም ነገር ላይ አስተያዬት የምትሰጠውን ሶስናን ሊገላት የሚፈልገው...እያልኩ ሁሉም ነገር ስሜት ሰጠኝ። ከሁሉ በላይ ግን ያ እናቱ የተገደለችበት ህፃን እንዴት ብሎ ነው ያን ሁሉ ሀዘን ተሸክሞ ማደግ የቻለው? የሚለውን እያሰብኩ አለቀስኩለት።>>

እያወራችው በድጋሜ ሆዷ ተላወሰባት። ሒዳ እሱን አቀፈችው። በዝምታ አቅፎ ፀጉሯን መደባበስ ጀመረ።
<<እንደዚህ አግኝቼው እቅፍ ባደርገው ደስ ይለኛል ጌታን!>> አለችው ድምጿ እየሰለለባት።
ቢጨንቀው የበለጠ ጥብቅ አድርጎ አቀፋት። ቀጥ ብላ አዬችው። ቁልቁል አያት።
<<ልዑል እንደሆንክ እያሰብኩ ጫፏ ጋር ልሳምህ?>>
ራሱን በእሺታ ነቀነቀ። ነካ አደረገችው...በከንፈሯ...ከንፈሩን! ተቀብሎ አፀፋውን መለሰላት። አሳሳሙ እንደተጠማት ያስታውቃል። ሳታውቀው ወጥመድ ወስጥ የገባች መሰላት።

በቁሙ እየሳመ ሊጠግባት ስላልቻለ አንስቶ ሰፋው ላይ ወረወራት።  መቼ ተጀምሮ መቼ እዚህ እንደደረሰ ለመረዳት ተቸገረች። ከእግር ጥፍሯ እስከ ራስ ፀጉሯ አንድ ቦታ እንኳን ሳያስቀር ሳመላት። እሷ ብቻ የተሳመች ይመስል ልቧ ተሰወረችባት። ከዚህ በፊት የተሳመችው ሁሉ ከላዩዋ ላይ ሳይተን ይቀራል? አሳሳሙ ገረማት።  "ኧረ ይሔ አሳሳም?" አለች ለራሷ..."ኧረ ይሔ አሳሳም ከ'እወድሻለሁ'ም ይበልጣል....ኧረ ይሔ አሳሳም ከ'ታስፈልጊኛለሽ'ም ይበልጣል....ይሔ?....ይሔማ የአምልኮ ነው" አለች ለራሷ። አፈፍ አድርጎ አንስቶ በስጋ ብቻ ሳይሆን በነፍስም ጠለቃት። የወሲብን ቅዱስነት ገለጠላት... "እንዴት ነው የንግስትነት ክብሬን ሳይቀማ እንደ ባሪያ ያንገላታኝ?" እያለች ራሷን ጠየቀች። አያያዙ ብቻ ሳይሆን አለቃቀቁም አስገረማት። ከሰባተኛው ሰማይ አድርሶ ሲለቃት ብትን ብላ ደረቱ ላይ ተጎዘጎዘች።

እንደተንተራሰችው ሀሳብ ውስጥ ገባች። ሀሳብ ውስጥ ሁና ፈገግ ስትል ቁልቁል እያያት <<ምነው?>> አላት!
<<የቀድሞ ፍቅረኛዬ ለምን አንድ ቀን አብራው ላደረችው ሴት ጥሎኝ እንደሔደ አሁን ነው የገባኝ። እሱ ባይቀድመኝ ኑሮ እኔ ላንተ ትቼው እሔድ ነበር።>> አለች ፈገግ ብላ።
ግንባሯን ሳማት። ትላልቅ አይኖቿን ከደነቻቸው።
<<መልአኬ ነሽ ለኔ!>> አላት። አልተጠራጠረችውም። ቀደም ሲል ከንፈሩ ያለ ድምፅ ነግሯታል። 
<<አለማመን መብትሽ ነው ግን የመጀመሪያዬም የመጨረሻዬም ነሽ!>> ሲል ቀጠለ እርግጠኝነት በተሞላው ቶን።

ደንግጣ አይኗን ገለጠች።

<<የምርህን ነው? How??>> አለች እየተገረመች።
<<ነግሬሻለሁኮ! እርግጠኛ ካልሆንኩ መፃፍ አልጀምርም። መፃፍ ከጀመርኩ ደግም ስርዝ ድልዝ አይኖረኝም።>>
ጥብቅ አድርጋ አቀፈችው። ሲያቅፋት እሱም ሰላም ተሰማው። "ቡዳ ነች" ብለው ደብድበው ከገደሉበት እናቱ ቀጥሎ ባያት ቁጥር ደስ የምትለው የመጀመሪያዋ ሴት ነች ሩሀማ።

የልዑል ታሪክ የራሱ ቢሆንም  ስሜቱን እንዳታጣው ሊነግራት አልፈለገም። ሁሉ ነገሩ ራሱን ነው። የጨመረውም ሆነ የቀነሰው ነገር የለውም። ወደ እብደት ጎዳና እየተንደረደረ በነበረበት ወቅት ሩሀማ በስካር መንፈስ ሆና የተናገረችው ንግግር ህይወቱን ላንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ቀዬረው። በዚህ ክስተት ምክኒያት ለናቴ ምትክ እንድትሆን ከፈጣሪ የተላከች መልአኬ ናት ብሎ አመነ። በቀላሉ ሊተዋትም አልወደደም። "መልክተኛ መልአኬን መፈለግ አለብኝ" በማለት በተገናኙበት ባር አከባቢ ሲፈልጋት ከረመ። በመጨረሻም የዛን ቀን አብሯት የነበረውን ልጅ (ኤክሷን) ወተት እና ቢራ ተሸክሞ ሲሔድ አገኘው። የሆነውን ሁሉ አስረድቶ እንዲያፋልገው ጠዬቀው። ልጁም በጣም ደስ ብሎት ስለሷ ባህሪ የሚያውቀውን ከነገረው ቡኃላ ወዳለችበት መራው። እንዳዬችው እንዳላስታወሰችው ሲያውቅ ከማናገር ይልቅ ትኩረቷን መሳብን መረጠ። እናም በዙዎችን ከሚያስገርሙ ባህሪዎቹ አንዱ የሆነውን ባዶ ወረቀት የመጣል ትዕይንት ፊቷ መጫወት ጀመረ። አንድም እንኳን በአጋጣሚ የሆነ ነገር የለውም።

ተነስታ መስታውቱ ጋር ቁማ ልብሷን እየለባበሰች <<ይሔንን አደረገ ብዬ የምተውህ እንደይመስልህ? አሁንም ቢሆን የልዑልን ቀጣይ ክፍል እፈልጋለሁ!>> አለችው። ዝም አላት።
ዝም ሲል ዙራ አዬችው። በሀሳብ ጭልጥ ብሎ በትንሹ ፈገግ ብሏል።
<<ምን እያሰብክ ነው እንደዚህ የምትፈገው?>> አለችው!

<<የልዑልን ህይወት ቀጣዩን ክፍል!>>  አላት ፈገግታው ሳይጠፋ። <<ይሻልሀል!>> አለች ቀጣዩ ክፍል እሷጋ የሚኖረው ህይወት እንደሆነ ያልገባት ሩሀማ።
1.8K viewsflawoless , 18:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-12 21:46:57 ሁላቹም በዚ እድል ተጠቀሙ አያምልጣቹ
1.6K viewsflawoless , 18:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-12 21:46:33
abdela ሰው add ስላደረክ ብቻ ሳፋሪኮም በባንክ አካውንትህ 500 ብር ገቢ አድርጎልሀል

እናመሰግናለን



አስደሳች ዜና


ሳፋሪ ኮም ለናንተ ለውድ ደንበኞቹ ልዮ እድል
ይዞ መጣ እዚ ግሩፕ ሰው add  በማድረግ ወደ ግሩፑ ሰው ስታስገቡ ሳፋሪ ኮም ለናንተ ለውድ ደንበኞቹ 500 ብር ሽልማት ከዚ ሰአት ጀምሮ በባንክ አካውንታችሁ ገቢ ያደርጋል

500 ብር መሸለም ከፈለጋችሁ አሁኑኑ ሰው add አድርጉ እኛ ብሩን በአካውንተወ ገቢ እናደርጋለን!!



https://t.me/+Id1OEEOYvbpkNDA0
1.6K viewsflawoless , 18:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-12 21:46:00 ምኞት

ክፍል 41

ድርሰት በጥላሁን ተስፋዬ
.
.
.
የመጣችው?" አለች እጅን ከአንግታ ለማስለቀቅ እየተጣጣረች።
ድጋሚ እቅፉን እያጠበቀ "ናርዶሴ ነቻ እህት አለም የማታው እማ
ልዩ ነበር እንደ ሌላ ግዜው ታይታ ጥፍት ያለችብኝ መሰለሽ ብዙ
ሰአት እኮ ከኔ ጋር ነበረች እንቅልፍ ባይወስደኝ እርግጠኛ ነኝ
ለምን ለምን ጥላኝ እንደሄደች ልታወራኝ ፈልጋ ነበር በጣም ነው
ደስ ያለኝ እህቴ ።"እያለ ትንቢተ ትንፋሽ እስኪያጥራት አንገታን
አጥብቆ እንዳቀፈ አወዛወዛት።ምኛት እቃ ቤት ሆና የምትሰማው
ነገር ከራሷ አሳዛኝ ታሪክ በላይ ስለሆነባት እያለቀሰች"ፈጣሪዬ
ለምን እዚህ ነገር ውስጥ ከተትከኝ ለምን"
ለምን?እኔ በፍቅር ተጎዳሁ ተገፋሁ እያልኩ ሳማርርህ በፍቅር
ተጎድቶ እራሱን የጣለውን እሄን አሳዛኝ ወጣት እዚህ ጉያዬ ድረስ
ያመጣክብኝ ከኔም የባሰ እንዳለ እንድረዳና እንድፅናና ወይስ
በፍቅር የቆሰለ ልቧን እየነካካ እሳም አብራው ትበድ ይለይላት
ብለህ ነው። ፈጣሪዬ ግራገባኝ እሄ ነገር አጋጣሚ ነው ብዬ
ማለፍ ከበደኝ ለምን?ለምን?ሁለት የተገፋን ሰዎችን በአንድ ቦታ
ሰብስበህ አንዳችን አንዳችንን ማፅናናት በማንችልበት ሁኔታ እርስ
በርስ እንድንላቀስ ፈረድክብን። ፍቅርን የተማርነው ካንተ ሆኖ ሳለ
በሰው ላይ ክፋትን የሚያደርጉ ይደሰቱ ዘንድ ፈቅደህ ሰው
በወደድን ሰው ባፈቀርን የመከዳት መራራ ፅዋ እንድንቀምስ
ሂወታችንን በለቅሶ እና በሀዘን እንድናሳልፍ ፈረድክብን ።
ያፈቀረ ሰው ምን ይሆን ሀጥያቱ?ዝም አትበለኝ እባክህ መልስህን
መጠበቅ ደከመኝ አምላኬ እባክህ ንገረኝ ይህቸ አለም የማን
ነች? የኩፉዋች፣ የሸረኛች እና የካሀዲዋች? ወይስ ወይስ የቅን
ልቦች?
ፈጣሪዬ እኔ የምፈልገውን ሳይሆን ህይወት የሰጠችኝን ተቀብዬ
ከሰው እንዳልተፈጠርኩ ከሰው ተገልዬ ተስፋ የቆረጠ ልቤን
የተቀበረ ፍቅሬን ከተኛበት የሚቀሰቅስ ሁኔታ ውስጥ ለምን
ከተትከኝ ?ወላጆቼን ነጠክከኝ እሱም ሳይበቃ ለምን የምድር
ሂወቴን አከበድከው አምላኬ ? እኔም እንደሁሉም ባንተ ፍቃድ
አይደል እንዴ እዚህ አለም ላይ የተፈጠርኩት ለምን እኔ ላይ ?
ለምን ስቃዬን አበዛከው ?ለምን ለምን ንገረኝ ዝም አትበል ንገረኝ
መቼ ነው ሚያበቃው ንገረኝ ንገረኝ ንገረኝ!!!"
እያለች ጮኸች አለቀሰች። በዚህ ሰአት እጅግ መራር የሀዘን
ስሜት ውስጥ ነበረችና ድንገት በእጆቻ ከታፈነው አፏ ውስጥ
አፈትልኮ የወጣ በሲቃ የታጀበ ፍጨት የሚመስል ቀጭን ድምፅ
በመሳይ እቅፍ ባለችው ትንቢተ ጆሮ ውስጥ በጣም በስሱ
አቃጨለባት።
ትንቢተ ድንገት ሹክ ብሎ ያስበረገጋትን ድምፅ ለማረጋገጥ
ስለፈለገች "እሺ ቆይ እስቲ አንድ ግዜ ወንድሜ"አለችና እጅን
ከአንገቷ ላይ እንደምንም አስለቅቃ ተነስታ ወደ መውጫው በር
አመራች።
በሩን ከፍታ ወደ በረንዳው ወጣች ። ዝር የሚልም ሰው የለም
።ግራ ገባት ።ተመለሰችና "ቁርስ ብላና ታወራኛለህ" አለችው እና
ቁርሱን አቀረበችለት ።መሳይ መልስ ሳይሰጣት ቁርሱን መብላት
ጀመረ።
"እኔም እንደሱ መቃዥት ጀመርኩ?ወይስ ጆሮዬ ነው ? ድምፅ እማ
ሰምቻለሁ!በትክክል የሆነ ደስ እማይል የሚረብሽ ድምፅ
ሰምቻለሁ" አለች ለራሷ።መሳይ ፍቅረኛውን እንዳያት ሲነግራት
ደስታው ከሌ ግዜው ላቅ ያለ መሆኑ ቢያስገርማትም በህልሙ
አይቷት አልያም እንደለማዱ እየቃዥ ነው ብላ ደምድማለች።
እንደተወዘጋገበች ተነሳችና ወደ መኝታ ቤት ገብታ አየት አትጋ
ወጣችና ቀጥታ ወደ ሽንት ቤቱ አመራች ።የሆነ ድምፅ የሰማሁ
መስሎኝ ነበር ከጎረቤት ነው እንዳልል ተዘጋግታል አለች ጮክ
ብላ።ምኛት ሰማቻት ትንቢተ ወደ ሽንት ቤት ስትገባ ከመቅፅበት
ከፍራሻ ለይ ተፈናጥራ በመነሳት መሬት ለይ በመቀመጫዋ
ዝርፍጥ ብላ ተቀመጠችና መሀል ላይ እንደ መከለያ ባቆመችው
አሮጌ የማይሰራ ፍሪጅ ላይ ወገባን በማስደገፍ ሁለት እግሮቻን
ዘርግታ በሩን ለመዝጋት የምትጠቀምበት ግማሽ ቀረጢት ሲሚንቶ
ላይ በማድረግ ወደ በሩ አጥብቃ ያዘችው።ትንቢተ ሽንት ቤት
ገብታ እንደወጣች ሽንት ቤቱ በር ላይ ቆም አለችና ከእቃ ቤቱ በር
ጋር ተፋጠጠች። ግጥም ተደርጎ ቢዘጋም ከውጪ ሰረገላም ይሁን
ተቀርቃሪ አልያም ተንጠልጣይ ቁልፍ የለውም ።ጠጋ አለችና ገፋ
አደረገችው ዝግ ነው ሀይል ጨምራ ገፋችው አይነቃነቅም
"ከውስጥ በምን ዘጉት" ግራ ገባት እቃ ቤቱ በውጪ የመስታወት
መስኮት እንዳለው እንዳየች ትዝ አላት።
በቃ ቤቱ መስኮት ወደ ውስጥ ለመመልከት ወደ በረንዳው
ወጣች.....

.............ይቀጥላል............

150 ከገባ#ክፍል 42 ዛሬ ይለቀቃል

ቀጣዩን#ክፍል እንዲቀጥልLike ማድረግ እንዳይረሳ ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
1.4K viewsflawoless , 18:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-12 21:46:00 ምኞት

ክፍል 40

ደራሲ ጥላሁን ተስፋዬ
.
.
.
ስለናቱ እያወጋት ድንገት በመሀል " እባክሽ የኔ ፍቅር እሄን
ካጠገቤ ተኝቶ እኔ አንቺን ሳወራሽ የሚያገጠውን ጥርሳም ሰውዬ
ከዚህ ቤት አስወጭልኝ አላት •••
ምኛት ቀደም ብሎ ብቻውን ተቀምጦ አጠገቡ ሰው ያለ
እስኪመስል ድሩስ ሲከራከርና ሲጨቃጨቅ ስትሰማው ብትቆይም
ፈራች በቀስታ ቤቱን ከዳር እስከዳር ቃኘት አደረገችና በእንባ
የረጠበ ፉቷን ሽቅብ መልሳ ለሷ እና አጠገባ ላለው ሚስኪን
እብድ ፀለየች።
እናቴ ደስ ይበልሽ ልክ ነበርሽ አለና መሳቅ ጀመረ በሳቁ መሀል
እሄው ትመጣለች ባንተ አትጨክንም ከሀዲ አይደለችም ትይኝ
አለነበርሽ ። እንዳልሽው ተመልሳ መጥታለች ተመልሳም
አትሄድም ደስ አለሽ እናቴ? ክዳኛለች ካሀዲ ነች ብዬ ሰድቤሽ
ነበርኮ ይቅር በይኝ እሺ ፍቅሬ እናቴ ግን ሁሌ
ተው እንደሱ አትሁን ሰው እሚያጋጥመው አይታወቅም ቀድሞ
ማመስገንም ቀድሞ መኮነንም ደግ አደለም።
"እኔ እናትህ ጠፋች ጥላኝ ሄደች ስትለኝ ውስጤ አልደነገጠም
እናቴ ምን አለች ትለኛለህ ተመልሳ መምጣቷ አይቀርም ብቻ
አንተ በርታ በልልኝ። ልጄ ለኔ ለናትህ አታዝንልኝም አንድ ልጄ
እንዲህ ስትሆን ከማይ ሞቴን እመርጣለሁ ልጄ ተው እሺ
በለኝ።ትልና ጎንበስ ብላ እንደ ህፃን ልጅ ጉንጮቼን ትስመኛለች።
እኔ አንቺን ፍቅሬን ሳጣሽ ህይወት አስጠልቶኝ የተመኘሁት ሞት
በምድር ላይ አንድ አለችኝ የምላትን እናቴን ነጠቀኝ ። እሂ ክፉ
ሞት የለመንኩትን እኔን ትቶ የምወዳትን ነጠቀኝ።
ግን መሞቷን ሰምተሻል የኔ ፍቅር እሄን እማ ይነግሩሻል ደና ነገር
አያወሩም እንጂ የሰውን ውድቀትና መርዶ ለማውራት ማን
ይቀድማቸውና! አላት ድክም ባለና የሀዘን ሲቃ ባዘለ ድምፅ።
ምኛት የመሳይ ንግግር ከራሷ እናት እና አባት በሞት መነጠቅ
መራር ሀዘን ጋር ተደምሮ አብራት የነበረውን ድምፅ አልባ ለቅሶ
ያለመንሰቅሰቅ ያለመጮህ ትግሏን አሸንፎ ያነፋርቃት ጀመር በልቧ
አዝላ የምትኖረውን የተጠራቀመ የመገፋት እና የብቸኝነት ብሶት
ከተቀበረበት ፈነቃቅሎ እየወጣ እየዬ አስባላት።
ጮኸች እስኪወጣላት ተንሰቀሰቀች።መሳይ ግን የመጨረሻዋን
ንግግሩን እንደተናገረ መዳኒቱ አሸንፎት ነበርና ስታለቅስ ሳይሰማት
እንቅልፍ ጥሎቷል ።
አልቅሳ ሲወጣላት የታጠፈውን የመሳይን እጅ አስተካክላ አንሶላ
አለበሰችው እንዳይበርደውም ብርድልብሱን ደረበችለት።
አጠገቡ ቁጭ ብላ የተኛውን መሳይ ቁልቁል እየተመለከተችው
ስለ ፍቅር ሀያልነት ማሰላሰል ጀመረች።
ፍቅር ግን ምንድን ነው?
ትልቅ አይል ትንሽ፣ሀብታም አይል ደሀ፣የተማረ አይል
ያልተማረ፣ያበደ አይል ያላበደ
ጤነኛውን የማሳበድ ያበደውን ጤነኛ የማረግ ሀይል ያለው
ማንም ላይ ለመንገስ ከልካይ የሌለው ሁሉን የሚያንበረክክ
በስቃይ ውስጥ በችግር ውስጥ በረሀብ ውስጥ በእብደት ውስጥ
ቦታውን የማይለቅ ግዛቱን የማያስደፍር የማይለዋወጥ ጣፋጭ
ስቃይ።ለነገሩ ፍቅር ከፈጣሪ ነውና እሱን የሚቋቋም ሀይል
አለመኖሩ አይገርምም።
አብዶም ስለሷ ሲያወራ ለሷ ያለው ፍቅር ትዝታ የሷ ናፍቆት
ሁሌም አንድ መሆኑ ይገርማል አለችና በተኛበት ደና እደር ብላው
ወደ መደበቂያ ዋሻዋ ወደ እቃ ቤቷ ገብታ በሯን ዘጋግታ ተኛች።
የመሳይ እህት ትንቢተ ለመሳይ ከቁርስ እስከ እራት የተለያየ እና
የሚወደውን ምግብ ለማዘጋጀት ሌሊት 11:30 ላይ ነበር
ከእንቅልፏ የተነሳችው ። አዘጋጅታ እንደጨረሰች ወደ አባቷ ክፍል
ሄደች ዝግ ነው።ተኝተዋል። የንጀራ እናቷ ስላለች መቀስቀስ
አልፈለገችም። ኮንትራት ይዛ ወደ መሳይ ጋር ሄደች።ምኛት እና
መሳይ በሂወት አጋጣሚ በተለያየ ምክንያት እቃቤትና ሳሎን ቤት
ሳይፈልጉ ወደ ተጣሉበት ኮንደሚንየም እስክትደርስ ስለ ወንድሟ
መሳይና ወንድማን ወስዶ ስለደበቀው አባቷ ጭካኔ እያሰላሰለች
ትብሰከሰካለች።
አባቷ መሳይን እዛ እንዳስቀመጠው የሙት እናቷ ዘመዶች
እንዳይሰሙ የሚያደርገው
ጥንቃቄ ጭራሽ የተበዳይነት ስሜት እንዲሰማት በማድረጉ እልህ
ይዟት አባቷ ወንድማ የንጀራ እናታቸው እቤታቸው እንድትገባ
ስለማይፈልግ ብቻ አንድ ኮንዶሚንየም ወደ ሚባል የከተማ
ውስጥ ምሽግ አስገብቶ ከውጪ በመቆለፍ ብቻውን
እንዳስቀመጠው ለመናገር ጫፍ ላይ ደርሳለች።
"እርግጠኛ ነኝ እንኳን የማሚ ዘመዶች የራሱ ዘመዶች እንኳን
ቢሰሙ አባቢ ላይ ያዝኑበታል ግን ደሞ ሲሰሙ መሳይን እኛ ጋር
ይሁን ማለታቸው አይቀርም በዚህ ሁኔታ ላይ እያለ ደሞ ወንድሜ
የሰው ፊት እንዲያይ አልፈልግም።"እያለች ከራሷ ጋር ታወራለች።
"ለማሚ ዘመዶች ግን አሁን ቁርሱን አብልቼው እንደወጣሁ ነው
ሄጄ ሁሉንም አንድ በአንድ የምነግርለት ። አሁን እማሚ ብትሆን
እንደዚህ ታደርግ ነበር?በፍፁም አታደርግም!!"
አለችና እምባ ሲተናነቃት እፉፉፉ ብላ በመተንፈስ እንባዋን
ለመቆጣጠር መከረች"
"በሰላም ነው?ችግር አለ እህቴ?" አላት ሹፌሩ።
መልስ ሳትሰጠው እንዳቀረቀረች ደርሳ ወረደችና አይናን
እየጠራረገች ደረጃውን ቶሎ ቶሎ ወጥታ የኮንደሚንየሙን በር
ከፍታ ገባች።እዚህ ኮንደሚንየም ተደብቃ መኖር ከጀመረች ጀምሮ
እንቅልፏ ሁሉ የዛፍ ላይ እንቅልፍ የሆነባት እና እሷ ብትተኛም
ጆሮዋ የማይተኛው ምኛት ትምቢተ በሩን ከፍታ እንደገባች
ወድያው ነበር ከንቅልፋ በመንቃት ተነስታ ቁጭ ያለችው።
ትንቢተ ወደ ሳሎኑ ስትዘልቅ መሳይ የሞት ያህል በጥልቅ
እንቅልፍ ውስጥ ነበር።
ጠጋ ብላ እንደ እባብ ጥቅልል ብሎ የተኛውን መሳይ ሀዝንና
ስስት በተሞላ ስሜት ቁልቁል ታየው ጀመር።
ፍራሹ ላይ በጉልበቷ ሸብረክ አለችና በዝግታ እያንቃነቀችው
"ወንድሜ መስ አንተ መሳይ"
እያለች ስትቀሰው ፍንጥር ብሎ ተነሳና ሲሮጥ የመጣ ያክል
ዙርያውን እየቃኘ ያለከልካል ።
ትንሽ እስኪረጋጋ ግዜ ሰጠችውና "ምንድን ነው ምትፈልገው ምን
ሆነካል ወንድሜ?"
አለችው።
ምንም ሳያወራ ተወርውሮ አንገቷ ላይ ተጠመጠመና...
"ማታ መጥታ ነበር እህት አለም :ማታ አብራኝ ነበረች :እውነቴን
ነው እህቴ ማታ በትክክል ነክታኛለች አብራኝ አምሽታለች
መዳኒቴንም አውጣኛለች።
እህቴ ማታኮ መጥታ አብራኝ ፍራሹ ላይ ነበረች ስትገቢ
አላገኘሻትም? መጣሁ ብላሽ ሄዳ ነው? ንገሪኝ እህቴ?
ትመለሳለች አደል ? ጥላኝ አልሄደችም አደል እህት አለም?"
አላት በማልቀስ እና በመሳቅ መሀከል ሆኖ ድብልቅልቅ ባለ
ስሜት ።
አንገቷን ከመጠን በላይ ጥብቅ አርጎ ስለአቅፏት ትንፋሽ ያጠራት
ትንቢተ
" ማን ....ነች እ.....ሷ ? ወንድሜ! ማነች ማታ የመጣችው
ስትለው........

.............ይቀጥላል............

140 ከገባ#ክፍል 41 ዛሬ ይለቀቃል

ቀጣዩን#ክፍል እንዲቀጥልLike ማድረግ እንዳይረሳ ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ

            
1.3K viewsflawoless , 18:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-12 21:46:00 ምኞት

ክፍል 39

ደራሲ ጥላሁን ተስፋዬ
.
.
.
እማዬ የኔ ፍቅር አሳዝኜሽ ነው እምታለቅሽው ለምንድን ነው?
እንዲህ ሆኜ ስታይኝ አሳዝኜሽ ከሆነ አንቺ ተመልሰሽ አትሂጅብኝ
እንጂ እኔ የድሮው መሳይ እሆናለሁኮ።እባክሽ ዛሬ እንኳን የሆነ
ነገር በይኝ ።ባለፈውም በለሊት እንደዛ አወዛውዘሽ ቀስቅሰሽኝ
ስነሳ አጠገቤ ሆነሽ እጅሽን እያወናጨፍሽ ታወሪኛለሽ ግን እኮ
ምን እንደምትይ አልተሰማኝም ልይዝሽ ስሞክርም አትያዥልኝም
ሲጨንቀኝ ጮህኩኝ ከዛ እየራቅሽኝ እየራቅሽኝ ስትሄጂ ልከተልሽ
ፈልጌ ነበር ወድያው አባዬ እና ትንቢተ መጡና እጅና እግሬን
ይዘው እሄውልሽ እሄን መድሀኒት : አለና በፍራሹ እራስጌ በኩል
አንድ በፌስታል የተቋጠረ ነገር በማንሳት ቋጠሮውን ፍትቶ
ውስጡ ካሉት መድሀኒቶች አንድን በማውጣት እሄንን እምጠላውን
መድሀኒት አዋጡኝ በማለት መዳኒቱ ይዞ ወደ ምኛት ለመጠጋት
ሞከረ።
በተመስጦ ስትከታተለው የነበረችው ምኛት እንደመባነን አለችና
በድንጋጤ ቀኝ እጃን በመሳይ ደረት ትይዩ በመዘርጋት መኪና
እንደሚያስቆም ትራፊክ እንዳትጠጋኝ የሚል መልክት ያዘለ
ምልክት አሳየችው።
መሳይ ደንግጦ መዳኒቱን መሬት ላይ በመጣል ወደ ጀርባው
አፈገፈገና ፍራሹ ጠርዝ ላይ በመቀመጥ እሺ እሺ እሺ አልጠጋሽም
አለ መሬት መሬት እያየ።
ቀና ብሎ ሲመለከታት አሁንም እጇ እንደተወደረ ነው ።ተነስቶ
ፍራሹ ላይ ወጣ ወደ ግድግዳው ጥግ ተጠግቶ ከሷ ራቅ ብሎ
በፍራሹ እራስጌ ኮርነር ላይ ኩርምት ብሎ በመቀመጥ አይን
አይኗን ተመለከታት ። አስተያየቱ እሄው አልደርስብሽም አሁንስ
ከዚህ በላይ መሄጃ የለ ወዴት ልሂድ የሚል መልክት የያዘ መስሎ
ተሰማት ሆዷ ተላወሰ አንጀታ ተንሰፈሰፈባት የዘረጋችውን እጅ
ብታወርድም እንባዋን ግን ከመውረድ ልታቆመው አልቻለችም
መላ ፍቷ እስከ አንገቷ በእንባ ታጠበ። ምን ያህል ቢያፈቅራት
ነው። ፈጣሪዬ ይቅር በለኝ አለች እራሷን ለማዳን በፍቅረኛው
ተመስላ በምታረገው ነገር የጥፋተኝነት ስሜት ተሰምቷት።
ወድያው መሬት ላይ የወደቀውን ፌስታል አንስታ ገለጥ ስታደርገው
የንቅልፍ ኪኒንን ጨምሮ ብዙ አይነት መድሀኒቶች
ተመለከተች።የንቅልፍ ኪኒኑ ያኔ ደርጉ የህቷ ባል ሲያሰቃያት
በጭንቀት ምክንያት እንቅልፍ በማጣቷ ከታዘዘላት
መድሀኒት ጋር ተመሳሳይ ነው ።ከመሀል የንቅልፍ ከኒኑን
በማውጣት አንድ ፍሬ ፈልቅቃ ወሃ ቀዳችና በቀስታ ቁጭ ብሎ
ወደሚቁለጨለጨው መሳይ ተጠጋች።
ፈራ ተባ እያለች መጀመሪያ መዳኒቱን እንዲቀበላት እጇን ዘረጋች
።መሳይ እንኳን መዳኒት ድንጋይም በሷ እጅ ቢሰጠው ከመዋጥ
የሚመለስ አይመስልም። ደስ እያለው ነበር የተቀበላት።
ቀጥላ ውሃውን አቀበለችው እሺ የኔ ፍቅር ዛሬ መዳኒቴንን አንቺ
ነሽ እምታውጪኝ አደል?አለ።ጭንቅላቷን ወደ ላይ እና ወደ ታች
በማወዛወዝ "አዎ" አለችው። መዳኒቱን ዋጠው ።በምልክት
እንዲተኛ ነገረችው ጀርባውን ሰጥቷት ተኛ ሁኔታው አንጀት
ይበላል። ፍራሹ ጫፍ ላይ ተቀምጣ ቀስ ብላ እጃን ወደ
ጭንቅላቱ በመላክ ስትደባብሰው ።እማ እሄን ነገር አረሳሽውም
አደል አላት ጮክ ብላ ላለማልቀስ አፏ ውስጥ ሻርፓን
ጎሰጎሰችው ።
የዋጠው መድሀኒት ስራውን እስኪያጠናቅቅና እንቅልፍ
እስኪወስደው ድረስ ፀጉሩን ስለደባበሰችው በደስታ ተሞልቶ ነበር
የሚያወራት።
"ከምንም በላይ የምወዳት እናቴ ምናለበት ይቺን ሰአት ከማን ጋር
እንደሆንኩ ባየችልኝ።
የኔ እናት እኮ አንቺን በማጣቴ ፣ሳዝን አብራኝ አዝናለች፣ስትናፍቂኝ
እሷም ናፍቃሻለች፣ስታመም ከኔ በላይ ታማለች።
አይ የኔ እናት ሁሌም አንቺን ድንገት በማጣቴ ስሰቃይ ስጨነቅ
እና እንቅልፍ ሳጣ አባቴ ተኝቶ ሲያንኮራፋ እሷ ግን እኔን ሳታስተኛ
ከክፍሌ አትወጣም ነበርኮ።
እንዲህ እንደአንቺ አጠገቤ ቁጭ ብላ ፀጉሬን እየደባበሰች" ኪያዬ
አንተ ኪያ ትለኛለች"
አቤት እናት አለም"ስላት
"ያንተ ናርዶስ ከአቅማ በላይ የሆነ ችግር ቢገጥማት እንጂ ባንተ
የሚጨክን አንጀት የላትም።
እስቲ አስበው ኪያዬ የኔ ውድ ልጅ እንደዛ አንድ ቀን ያላየችህ
እንደሆነ ካላበድኩ የምትል ልጅ ካደችኝ :ጠላችኝ ብለህ እያሰብክ
እራስህን መጉዳት ልክ አደለም ይልቅ ደግ ደጉን ማሰብ ይሻላል።
እባክህን የኔ ልጅ እራስህን አትጉዳ ነገ እውነቱን ስትረዳ
ይፀፅትሀል ትለኝ ነበር" •••
እያለ ስለናቱ እያወጋት ድንገት በመሀል " እባክሽ የኔ ፍቅር እሄን
ካጠገቤ ተኝቶ እኔ አንቺን ሳወራሽ የሚያገጠውን ጥርሳም ሰውዬ
ከዚህ ቤት አስወጭልኝ!" አላት ...

.............ይቀጥላል............

130 ከገባ#ክፍል 40 ዛሬ ይለቀቃል

ቀጣዩን#ክፍል እንዲቀጥልLike ማድረግ እንዳይረሳ ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
1.3K viewsflawoless , 18:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-12 21:46:00 ምኞት

ክፍል 38

ደራሲ ጥላሁን ተስፋዬ
.
.
.
ካሁን ካሁን ዘሎ አነቀኝ ብላ ባለችበት ደርቃ ቀረች።
እንኳንስ መሳይ የለየለት ጤነኛውም ቢሆን መብራት ጠፍቶ
ሲመጣ ድንገት ብቻውን እነበረበት ቤት ውስጥ አንድ ቆንጆ ሴት
ሳሎን መሀል ላይ ተገትራ ቢያጋጥመው ደንግጦ ወደ
እሚያምንበት አቤት ማለቱ የማይቀር ነው። ሳሎን መሀል ላይ
አንደ እንጨት ደርቃ የቆመችውን ምኛት ሲመለከታት ሁሌም
በህልሙም በውኑም በሀሳብም በአካልም እየመጣች
የምታሰቃየው ጥላው የሄደችው ፍቅረኛው ዛሬም ስለመምጣቷ
ባይጠራጠርም ከተወሰነ ነገር ውጪ የመልኳ መቀያየር ግራ
ያጋባው ይመስላል።
ምኛት አሁን ላይ መልኳም ሰውነታም እንደበፊቱ ወደ አዲስ አበባ
ስትመጣ እንደነበረው አይደለም እጅግ ተለውጣለች መብላት
መተኛቱ ከአዲስ አበባ ቅዝቃዜ ጋር ተስማምቷታል የበፊቱ
አስደናቂ ውበቷ ቀስ በቀስ መመለስ ጀምራል።
አንድ እለት በመስታወት ፍቷን እያየች ከዛ ከደርጉ አውሬ ጋር
ከመኖር የማይሻል የለም አሁን እሄም ኑሮ ሆኖ ነው መልኬ
የተመለሰው ይገርማል አለች ለራሷ እራሷን ፈገግ ብላ
በመስታወት ውስጥ እያየችው።
ዛሬ ደሞ እብዱ መሳይ ፊት ተገትራ አይን አይኑን ታየዋለች "
መብራቱ ዛሬ እኔን ሊያዋርድ ካልሆነ በቀር እስቲ ጠፍቶ ሳያድር
መጥቶ ያውቃል ይገርማል"።ትላለች አይኗን ከመሳይ ላይ
ሳትነቅል።
ፍቅረኛው እንደልማዳ ልታሰቃየው እንደመጣች ቢገምትም
።ለደቂቃዎች ግራ በመጋባት ስሜት ሲመለከታት ከቆየ ቡሀላ
ከተቀመጠበት ብድግ ሲል የምኛት የልብ ምት እጥፍ ሆነ።
ቅፅበታዊ የማምለጫ ሀሳብ ብልጭታዎች በየተራና ከብርሀን
በፈጠነ ፍጥነት አእምሮዋ ውስጥ ይሰገሰጉ ጀመር።
"እሩጭ በሩን ከፈችና ብን ብለሽ አምልጭ።
"ወደ ውጪ ከመሮጥ እቃ ቤት ገብተሽ ብዘጊ ይሻልሻል።
የትም ብትገቢ ተከትሎ ያንቅሻል። ወይኔ ጉዴ ያንን ቻይናዊ
ማጅራቱን ብላ የጣለችበትን ዱላ የት እንዳለ ለማስታወስ
ሞከረች።
ወይ ምኛት ሞኝ ነሽ እብዶች እኮ ባላቸው ጉልበት ላይ እላያቸው
ላይ የሰፈረው የጋኔኑ ወይም የሰይጣኑም ጉልበት
ስለሚጨመርላቸው ብትመችውም ተነስቶ ለማነቅ ጉልበት
አያጣም።
ምኛት አእምሮዋ ውስጥ ቶሎ ቶሎ የሚቀያየሩት ፍርሀት
የወለዳቸው ሀሳቦች ፍርሀቷን ከነበረበት እጥፍ አደረጉት ጉልበታ
ተብረከረከ።
ያሰበችውን አንዱንም ሳታደርግ ከቆመችበት ሳትንቀሳቀስ እሱ
ተነስቶ እንደቆመ ሳይንቀሳቀስ በስስትና በሚያሳዝን አይታ
ይመለከታት ጀመር።
ፊቱ ላይ እምታየው የስስት እና የፍቅር አስተያየት ብሎም ከንፈሮቹ
መናገር ማውራት እየፈለጉ ቃላት ለማውጣት ከብዷቸው
ሲንቀጠቀጡ መመልከቷ ምን አስቦ ምን ፈልጎ እንደሆነ ለመረዳት
እንድትፈልግ ቢያስገድዳት ይበልጥ ግራ የመጋባቱና የፍርሀቱ
ስሜት ተደበላልቆ ቢዥ አረገባት።
ከቆመበት አንድ እርምጃ ወደ ምኛት ሲጠጋ እሳ በተመሳሳይ
በአንድ እርምጃ ሸሸችው ።
እንደምትሸሸው ሲረዳ ...
"እባክሽ ፍቅሬ ፣ የኔ እመቤት ፣የኔ ጤንነት፣የኔ ፀሀይ፣የኔ ንጋት
፣የኔ ብርታት፣፣የኔ ርሀብ፣የኔ ጥማት፣ የኔ እብደት፣የኔ ሳቅና
ፍካት...
እባክሽን ዛሬም እንደሁሌው ሳታናግሪኝ እንዳትሄጂ።ሳታ ሳታወሪኝ
ተመልሰሽ አትጥፊብኝ እባክሽ!።
ደሞ የኔ ፍቅር ዛሬ ልዩ ሆነሻል ጭራሽ እኮ ሌላ ሰው መሰልሽ።
እርግጠኛ ነኝ ጥለሽኝ የሄድሽው ወደ አሜርካ መሆን አለበት። ወይ
እቺ አሜርካ ፊትሽን ማሳመራ ይሁን ፣የቆዳሽን ቀለም መቀየራ
ይሁን፣ አፍንጫሽን መገተሯ ይሁን፣ አይንሽን ማሳመሯ ይሁን
ጭራሽ ቁመትም መጨመር ጀመረች አይ አንቺ አሜርካ ለንቺ ምን
ይሳንሻል።
ምኛት ለመሳይ ፍቅኛው በመንፈስ የመጣች እንደመሰለው ሲገባት
ልቧ በሀዘን ተሰበረ።አይኖቿ በእንባ ተሞሉ።
በነኛ ውብ አይኖቻ የተንቸረፈፈውን እንባ መሳይ እንዳያይ ባት
አቀረቀረች ። አይንሽንም፣መልክሽንም፣ቁመትሽንም ይቀይሩት ብቻ
አንቺ እመሪልኝ እና ደስ ይበልሽ ግን እነዚህ አሜርካኖችን አምነሽ
ሁሉ ነገርሽን አትስጫቸው ጥሩ ነው ያሉሽንም ሁሉ አትመኛቸው
ነገ በነካ እጃቸው ፆታሽንም እንቀይር ከማለት
አይመለሱም።ካስቸገሩሽ ጥለሻቸው እኔጋ ነይ እሺ። አሏት።
በመሀል ዝም ስላለ ቀና ብላ አየችው እያለቀሰች መሆኑን
ተመለከተ ፍቱ ወዳያው በሀዘን ተዋጠና እምባው ከሷ በላይ
መውረድ ጀመረ...

.............ይቀጥላል............

110 ከገባ#ክፍል39 ዛሬ ይለቀቃል

ቀጣዩን#ክፍል እንዲቀጥልLike ማድረግ እንዳይረሳ ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
አሰተያየት ካላችሁ
            
1.7K viewsflawoless , 18:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-11 21:28:43
ሁሌ በእንቅልፍ ልቤ የማይሽ ህልሜ
ከእንቅልፌ ስነቃ የማስብሽ ሀሳቤ
የሁል ጊዜ ደስታዬ እና የማረሳሽ
.
.
.
ትዝታዬ ነሽ



,,,,,,,, ,,,,,,,,,,
        •═••• •••═•
  
    
@Yefiker_Gojo    ,, @AbenaG
━━━━━✦ ✿ ✦━━━━━
     
5.8K views♕𝙰𝙱𝙴𝙽𝙸 𝙹𝙲❥̟, edited  18:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ