Get Mystery Box with random crypto!

የ አማራው ድምፅ (ፋኖ)

የቴሌግራም ቻናል አርማ voice_of_amhara_fano — የ አማራው ድምፅ (ፋኖ)
የቴሌግራም ቻናል አርማ voice_of_amhara_fano — የ አማራው ድምፅ (ፋኖ)
የሰርጥ አድራሻ: @voice_of_amhara_fano
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 7.39K
የሰርጥ መግለጫ

#የአማራው_ድምፅ (ፋኖ)
✅የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው።
የአማራ ሕዝብን
✅ ፖለቲካዊ
✅ ማህበራዊ
✅ ኢኮኖሚያዊ
ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል።
✅ #FANO ✅
🙅🙅🙅

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-06-09 22:14:10
ፋኖ #መሰረት በላይ በምስራቅ ጎጃም ተገደለ

ከአንድ ሻለቃ የማያንስ ጦር ዘምቶበት ነበር

/
ፋኖ መሰረት በላይ በምስራቅ ጎጃም ከሚያሳድዱት የመንግሥት ታጣቂዎች ጋር እየተዋጋ ከቆየ በኋላ፣ ጥይት ሲያልቅበት ባለፈው አርብ ግንቦት 26 ቀን 2014 ዓ.ም. መሰዋዕቱን ቤተሰቦቹ አረጋገጡ። ወደ ፋኖ መሰረት በላይ የዘመተው ከአንድ ሻለቃ ጦር የማያንስ እንደሆነም ታውቋል።

ከተሰዋ በኋላ ገዳዮቹ የእግሩን ጫማ አውልቀው ወስደውታል። በተጨማሪም፣ በኪሱ ውስጥ ያገኙትን ተንቀሳቃሽ ስልክና ገንዘብ ወስደውታል። የዘመዶቹን ቤቶች እየተዘዋወሩ ከበረበሩ በኋላ በሞራላቸው ላይም ተሳልቀዋል።

መሰረት ባለትዳርና በንግድ ሥራ ላይ ተሠማርቶ የነበር ሲሆን፣ በቅርቡ የአማራ ሕዝባዊ ኃይልን (ፋኖ) ተቀላቅሏል።

ይህ በአንዲህ እያለ፣ ባሕር ዳር ከተማ፤ ቀበሌ 14 አኮቴት አደባባይ አካባቢ የሚገኘው የአማራ ሕዝባዊ ኃይል (ፋኖ) መጋዝን ትላንት ማክሰኞ፤ ግንቦት 30 ቀን 2014 ዓ.ም. ከቀትር በኋላ በመንግስት ኃይሎች ተይዟል። በውስጡ የነበሩ የፋኖ አልባሳትን እና ምግቦች በመኪና ተጭነው ባሕር ዳር ዘጠነኛ ፖሊስ ጣቢያ ገብተዋል።

ድርጊቱ በአካባቢው ኗሪዎች ዘንድ ከፍተኛ ቁጣና ብስጭትን ፈጥሯል።

#ጀግና ታግሎ ይሰዋል የጀመረው ትግል ይቀጥላል በወንድሞቹ ድል አድራጊነት ይደመደማል

https://t.me/voice_of_amhara_FANO
8.1K viewsedited  19:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-04 20:05:25
የዚህ ስንታየሁ ታከለ የሚባል ስው የቅርብ ዘመድ ጓደኛ የሆናቹህ ምከሩት
በሶሻልሚዲያ ፕሮፋይል ፎቶውን የአርበኛችን አድርጎ
ስራው ግን አርበኞችን ያሉበትን ቦታ መጠቆም ማስተኮስ እንደሆነ ፋኖች ደርስውበታል

ስለዚህ ፋኖ ለጥላት ብሎ ቆጥሮ የያዘውን ጥይት ባላወቀ ውንድም ላይ ማጥፋ ጥሩ አይደለም ተብሎ ዝምሲባል

ከዚህ በፊት ሁለት ፋኖችን በአንተ ምክንያት እንደተገደሉ እኛ አንረስውም
ስንታገስህ ያዙኝ ለቀቁኝ የምትል ከሆነ በአጭር እንደምትቀጭ ነው የምንነግርህ

ስለዚህ የወንድምነታችንን ምክርአቅርበንልሀል

ቋሪት አማራ ፋኖ
7.9K views17:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-04 05:51:38 ጥንቃቄ

አፋኞች ከድተው የዘመነ ካሴን ጦር ተቀላቀሉ በተባለው ላይ ትልቅ ጥንቃቄ ማድረግ ያሻል።

1. ከውስጥ ሆነው መረጃ ሊያቀብሉ
2. እንደ ጎቤ ዘመነንም በወዳጅ መሳዮች ለማስመታት እንዳይሆን

አቢይና ብአዴን ሲሰሩ ሳይሆን ሲሸርቡ ነው የሚታወቀው

መልእክት ለፋኖ

ዘመነን ልታደገው ብለህ የቤት ስራ አይሁንብህ ፥ ሄጄ ልታደገውም ብለህ ያለበትን ስፍራ አትጠይቅ ፤ ባለህበት ስፍራ የብአዴንና የአብይ ጦር ላይ ዘመነን ሁንበት።

ማስታወሻ፦ ፋኖ ያልነው ብጣሽ ወረቀት ላይ እኔም ፋኖ ነኝ ብሎ ፎቶ የሚነሳውን ቀልደኛ ወይንም ክላሽ አንግቦ ፎቶ የሚነሳውን የከተሜ አራዳን አይደለም

ደም በሚያስተፋ ቁጭት በቃኝ ብሎ መሰረታዊ ውትርድርና የሰለጠነውንና የተነሳውን ነው።

እኔም ዘመነ ነኝ ካልክ
በብአዴንና በአብይ ጦር ላይ አሁን ተነስ

https://t.me/voice_of_amhara_FANO
7.3K views02:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-04 05:48:52
ትውስታችን
5.3K views02:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-03 21:21:28
እስራኤል እኔም ፋኖነኝ

ወይ ዘሜ ዋዛ

ጀግናን እንዲህ በቀላሉ መገመት ብአዴንን ዋጋያስከፍልዋል
5.9K views18:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-26 19:07:20
'ፋኖን ለመንቀፍ ቀርቶ ለመገምገም የሚያስችል ማንነት የለንም" ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ የሰሜን ወሎ ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ሳይመዘገብ የሚሮጥ አትሌት የለም። ይህን ያህል ኪሎ ሜትር እሮጠህ ብታሸነፍ ይህን ያህል ገንዘብ ትሸለማለህ። የወርቅ ሜዳልያ ታጠልቃለህ ተብሎ ነው። ፋኖ ግን የሚሮጠው ሀገሬ በነጻነት መቆየቷ፤ ወገኔ በሠላም መኖሩ ለእኔ ሽልማት ነው ብሎ ነው። ደ*ሙን የሚያፈሰው፥ የሚራበው፥ የሚጠማው በፍፁም ተችዎቻቸው ሳንሆን አክባሪዎቻቸው ነን ::
7.9K views16:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-25 00:01:30
https://t.me/voice_of_amhara_FANO
7.2K views21:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-24 23:41:59
##መረጃ ለቀድሞ የአማራ መከላከያ ሰራዊት እና የልዩ ሀይል ለነበራችሁ

አሻራ ከሰሜን አሜሪካ

ፋኖና የአማራ ሊህቃን ላይ ያተኮረው ኦፕሬሽን በቁጥር 2 እቅዱ ተመላሽ የመከላከያ ሰራዊት እና የልዩ ሀይል አባላት ላይ ከባድ ኦፕሬሽን ታቅዷል። ከዚሁ ጀርባ የታቀደ ሌላ ሃሳብ መኖሩንም የውስጥ መረጃወቻችን ጠቁመዋል። ስለሆነም የቀድሞ የአማራ መከላከያ ሰራዊት እና የልዩ ሀይል አባል የነበራችሁ ጥንቃቄ አድርጉ። አፈናው ወድ እናንተ ሊመጣ ነው። ሴራውንም ለማክሸፍ ተዘጋጁ። ይህን መረጃ በፍጥነት ለሚመለከታቸው የቀድሞ የመክላከያና የልዮ ሃይል አባላት አድርሱ። መረጃን ቀድመን በማድረስ የወገኖቻችን ደህንነት እናስከብር::

#ንሥር ብሮድካስት\

https://t.me/voice_of_amhara_FANO
6.4K viewsedited  20:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-24 23:39:50
"…ይችላል ፋኖ ይችላል…!!

"…አንጋፋው የቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ ደጋፊዎች ናቸው። በባህርዳር ስታዲየም ተገኝተው ይችላል ፋኖ ይችላል ብለው የሚቀውጡት። ቅዱስ ጊዮርጊሶች የአርበኛ ልጆች ናቸው። ጣልያንን የአንበረከኩ የአርበኛ ልጆች። የፋኖን ጥቅም ከቅዱስ ጊዮርጊስ በላይ የሚያውቀው የለም።

"…ከአዲስ አበባ ተነሥተው፣ ባህርዳር ድረስ ተጉዘው። ያለ ሰፈራቸው፣ ያለ ከተማቸው፣ ቢታሰሩ፣ ቢደበደቡ አለሁ የሚል ወንድም እህት በሌለበት ስፍራ ከጎንደር ከመጡት ከፋሲል ከነማ ከአፄዎቹ ልጆች ጋር ሆነው ለባህርዳር እሳት እየዘነበባቸው ለሚገኙት ወንድሞቻቸው አጋር ሆነዋል።

"…የአዲስ አበባ ልጅ ይግደለኝ የሚባለው እኮ ለዚህ ነው። ብራቮ ሳንጆርጅ…!! ማርያምን ዐማራማ ያሸንፋል። ፋኖማ ያሸንፋል። ደግሞ ተራው ደርሶ ኢትዮጵያ ቡናን አይቼ።

"…እየተደመማችሁ…!

Via #zemedkun_bekele
5.6K views20:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-24 21:48:58
"ሀሰተኛ መረጃ ነው!" በሉን እንጂ!

ከቀናት በፊት ጋዜጠኛ ሰለሞን ሹምዬን ለማፈን ወደቤቱ ያመራው የአንባገነኖች ቡድን ፥ ጋዜጠኛውን በአጋጣሚ ከቤቱ ሲያጡት ፥ ከቤት ያገኟትን ታናሽ እህቱን በመያዣነት አግተው እስር ቤት መውሰዳቸውን ሰምተን "አጀብ ጉድ!" ብለን ነበር፡፡

"የባስ አለ …..!" እንዲሉት ነገር ፥ ዛሬ ደግሞ በምስራቅ ጎጃም ዞን የጁቤ ከተማ ነዋሪ የሆነው ፋኖ አበባው እጁን ለመንግስት ታጣቂዎች ይሰጥ ዘንድ ፥ ይህን የሰውን ልጅ ክፋትና ደግነት እንኳ የማያውቅ እንቦቀቅላ ህፃን አግተው ወደፖሊስ ጣቢያ በማስገባት አስረውታል የሚል ፥ በድንቃድንቅ መዝገብ የሚሠፍር ጉድ አሰምተውናል!

መቼም የሆነ ግፍ በጣም ገኖ ጫጫታ ሲበዛ ወይም ፥ ስውር ሴራዎች በአደባባይ ሲጋለጡ ፥ ግፍና መከራውን የተሸከመውን ህዝብ "ዝም ብለህ አትንጫጫ! መረጃው ሀሰተኛ ነው!" ሲሉ አንዳች ሀፍረት አይሰማቸውምና ነገ በሌላ ነውር ዳግም እስክንገናኝ "ሀሰተኛ መረጃ ነው!" ይበሉንና ይረፉት እንጂ! በወንጀላቸው ይወንጅሉን! በነውራቸው ያነውሩን እንጂ!

የህዝብ እምባና ደም ተጠራቅሞ መአበል እስከሚሆን ድረስ ፥ ያሻችሁን ብታደርጉ ምን አለባችሁ! ማንስ ሊጠይቃችሁ!

https://t.me/voice_of_amhara_FANO
5.8K viewsedited  18:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ