Get Mystery Box with random crypto!

Sheger Press️️

የሰርጥ አድራሻ: @sheger_press
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 40.24K
የሰርጥ መግለጫ

Official channel of sheger press
If you want to give a suggestion or comment, contact us 👉 @birukepromo

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2024-04-16 08:32:39
ጌታቸው ረዳ

የሕወሃት ኃይሎች በራያ አላማጣ አንዳንድ ቦታዎችን መቆጣጠራቸውን ተከትሎ ፤ የፕሪቶሪያዉ ስምምነት ጠላቶች ያደረጉት እንጂ በሕወሃት አልያም ጊዜያዊ መስተዳድሩ የተፈጸመ አለመሆኑን አቶ ጌታቸዉ ረዳ ተናገሩ

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር ጌታቸው ረዳ ፣ በደቡብ ትግራይና በሌሎች በኃይል የተያዙ የትግራይ ግዛቶች ባኹኑ ወቅት የተፈጠረው ክስተት በፌደራል መንግሥቱ እና በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ወይም በሕወሃት ወይንም በትግራይ እና በአማራ ክልሎች መካከል የተፈጠረ ግጭት አይደለም ሲሉ ትናንት እኩለ ሌሊት ላይ በኤክስ ትስስር ገጻቸው ላይ መለጠፋቸውን ዳጉ ጆርናል ተመልክቷል።

ጌታቸው፣ ክስተቱ ኹለቱ ወገኖች የፕሪቶሪያውን ስምምነት ተግባራዊ ለማድረግ እያደረጉት ያለውን አወንታዊ ግንኙነት ለማደናቀፍ የፈለጉ የስምምነቱ ጠላት የኾኑ ኃይሎች የፈጠሩት ነው በማለት ከሰዋል።

ከሩቅም ከቅርብም የግጭት ማቆም ስምምነቱ ጸር የኾኑ ኃይሎች ጦር እየሰበቁ መኾኑን የጠቀሱት ጌታቸው፣ ብቸኛው አዋጭ መንገድ ግን ሰላም ነው ብለዋል።

ኹለቱ ወገኖች ችግሮችን ለመፍታትና የሚስማሙባቸውን ጉዳዮች ለማጎልበት አዲስ አበባ ውስጥ ስብሰባ ላይ እንደኾኑም ጌታቸው ጠቁመዋል።

ሕወሃት ጥቃት ከፍቶ ተቆጣጥሯቸዋል የተባሉት አካባቢዎችን በተመለከተም አብን ማምሻውን ጠንከር ያለ መግለጫ አሰራጭቷል።

አብን የሕወሃት ኃይሎች በድጋሚ በአማራ ሕዝብ ላይ "አራተኛ ዙር" ጥቃት ከፍተዋል ሲል ትናንት ምሽት ባወጣው መግለጫ ከሷል። የፌዴራሉ መንግሥትና የአማራ ክልላዊ መንግሥት ሕወሃት በአማራ ሕዝብ ላይ የከፈተውን ሌላ ዙር ጥቃት ባስቸኳይ እንዲያስቆሙ የጠየቀው አብን፣ የአማራ ሕዝብ ከመከላከያ ሠራዊት ጋር በመቀናጀት የሕወሃትን ጥቃት እንዲመክትም ጥሪ አድርጓል።

አብን፣ መንግሥት የሕወሃትን ጥቃት በዝምታ ከተመለከተ፣ ድርጊቱ "የኹሉ ነገር መፍረሻና ማፍረሻ" እንዲኾን ፈቅዷል ማለት ነው ብሏል።

አብን ይህን መግለጫ ያወጣው፣ የሕወሃት ኃይሎች በራያ አላማጣ አካባቢ አንዳንድ ቦታዎችን እየተቆጣጠሩ ስለመኾኑ በተሰማ ማግስት ነው።

@sheger_press
@sheger_press
12.9K views05:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-16 07:10:24 ከአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ አብን የተሰጠ መግለጫ
***
ከትናንት ታሪካዊ ስህተቱ የማይማረው ህወሐት ለአራተኛ ዙር በህዝባችን ላይ ወረራ ፈፅሟል። የፌዴራልና የአማራ ክልል ክልሉ መንግስታትም በህዝብ ላይ የተቃጣውን የጥፋት ወረራ በአስቸኳይ እንዲያስቆሙ አበክረን እንጠይቃለን!

የኢትዮጵያ ህዝብ ዘላለማዊ ጠላት የሆነው ወያኔ ህወሐት በህዝብ ትግል ተገፍትሮ ወደ ትግራይ ከተሰበሰበ በኋላ በተደጋጋሚ ወረራ በመፈፀም በህዝባችን ላይ ለጆሮ የሚከብድ ዘግናኝ ግፍ ፈፅሟል። ምንም እንኳን ህወሐት በተደጋጋሚ ጊዜ በቆሰቆሰው ጦርነት የአማራ እና የአፋር ህዝብ በቀጥታ የገፈቱ ቀማሽ ይሁኑ እንጅ ዋና ዓላማው ኢትዮጵያ ሐገራችንን መበታተን እና የፈራረሰች ሐገር መፍጠር መሆኑን በአፈ ቀላጤው በኩል በተደጋጋሚ ተናግሯል።

ይህ የእናት ጡት ነካሽ ቡድን የሐገራችን ደጀን የሆነውን የሰሜን እዝ የመከለከያ ሰራዊት በማጥቃቱ ከመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ያጋጠመውን ቁጣ መቋቋም ተስኖት ለሶስተኛ ጊዜ እየተመላለሰ ያደረገው የሐገር ማፍረስ ሙከራ ባይሳካለትም እንኳን አድፍጦ ለጦርነት ከመዘጋጀት ግን ቦዝኖ አያውቅም።

ህወሐት ከጦርነት ውጭ መኖር የማይችል፣ በጦርነት አድጎ በጦርነት ያረጀ ቡድን በመሆኑ በመላው የኢትዮጵያ ክልሎች የሚገኙ አማፂያንን ከማስታጠቅ አልፎ ከታሪካዊ ጠላቶቻችን ጋር በመወገን ሐገራችንን የጦር ቀጠና ለማድረግ ያላሰለሰ ጥረት ሲያደርግ ነበር የከረመው። በቀጥታ ከሚደግፋቸው የጥፋት ኃይሎች በተጨማሪ የራሱን ኃይል በማደራጀት የሰርጎ ገብ ኃይል እየላከ ህዝባችንን ሲረብሽ መክረሙ ሳያንሰው በአሁኑ ሰዓት በራያ በኩል ቀጥተኛ የሆነ ጥቃት በህዝባችን ላይ ለአራተኛ ጊዜ ወረራ ከፍቶ ይገኛል።

ኋላ ቀርነት እና ግትርናት ዋና መገለጫው የሆነው የጥፋት ቡድን የሚሊዮኖችን ህይዎት በቀጠፈውና ከተደጋጋሚ ስህተቱ ባለመማር ዛሬም ለሌላ ዙር እልቂት ተዘጋጅቶ በህዝባችን ላይ ጦርነት ከፍቷል።

በህዝቦች እኩልነት እና በብሔረሰቦች መብት ፈፅሞ የማያምነው ህወሐት እኔ የማልገዛት ኢትዮጵያ ተረጋግታ መኖር የለባትም የሚል ያልተገራ ክፉ አመሉን በተደጋጋሚ አሳይቷል። በዚህም እንደ ሌሎች ኢትዮጵያዊያን እኩልነትን ፈፅሞ እንደማይሻ አረጋግጧል።

ለህዝባችን የሚከተሉትን መልዕክቶች እናስተላልፋለን

1. ምንም እንኳን አሸባሪው እና ተስፋፊው ወያኔ የሁሉም ኢትዮጵያውያን ጠላት ቢሆንም ፣ በተለይ የአማራ ህዝብ የቡድኑ ወረራ ቀጥተኛ ሰለባ እና ገፈት ቀማሽ በመሆኑ ጦርነቱን የመመከት ኃላፊነት ያለበት መሆኑ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም በሁሉም አካባቢዎች የሚገኘው ሕዝባችን ካለፈው የጥፋት ግዜ በመማር ከታሪካዊ ጠላቱ የሚሰነዘርበትን ወረራ ከኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ጋር በመቀናጀት እንዲመክት፣

2. ህዝባችን ከወያኔ ትጥቅ አስፈች ፕሮፖጋንዳ ራሱን እንዲጠብቅ እና ከዚህ ታሪካዊ ጠላት የሚመጣን ማንኛውንም ውዥንብር ጆሮ እንዳይሰጥ፣ ከዚህ ጋር በተያያዘ አንዳንድ የወገን ኃይሎች ለወያኔ የሚያሳዩትን የተለሳለሰ የባንዳነት መንገድ ህዝባችን ፈፅሞ እንዳያዳምጥ እና እንዲህ ያሉትን ቡድኖች አጥብቆ እንዲታገል፣

3. የአማራ እና የአፋር ህዝብ የጦርነቱ ዋና ገፈት ቀማሽ በመሆኑ የኢትዮጵያ ኃይሎች የሚፈልጉትን ሁሉ በማቅረብ ከሐገሩ ጎን እንዲቆም

4. ህዝባችን ይህን ታሪካዊ ጠላት በመቅጣት የተለመደ ጀግንነቱን እንዲወጣ ስንል ጥሪ እያቀረብን፤ በተለይ መንግስት በህዝባችን ላይ ለአራተኛ ጊዜ እየተፈጸመ የሚገኘውን ወረራ በዝምታ የሚመለከት ከሆነ፤ ህዝባችን ስርአትን አምኖ ችግሮች ሁሉ በህግ አግባብ ይፈታሉ የሚል ቀናኢነቱ ማታለያ ሆኖ ከዋለ፤ ይህ በራያ ብቻ የማይቆም ይልቁንም የሁሉ ነገር መፍረሻና ማፍረሻ እንዲሆን መንግስት የፈቀደ መሆኑን ታሪክ የሚመዘግበው ሀቅ ይሆናል።

5. በህወሐት ችግር የአማራና የትግራይ ህዝቦች እንዲሁም መላ ሀገሪቱና ቀጠናው ችግር ውስጥ እየወደቀ በመሆኑ ይህ በአስቸኳይ እንዲቆም እያሳሰብን በተለይ የፌዴራሉ መንግስትና የአማራ ክልል መንግስት በህዝባችን ላይ እየተፈጸመ የሚገኘውን ወረራ በአስቸኳይ እንዲያስቆሙ አበክረን እንጠይቃለን!

ሚያዝያ 07/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ/ኢትዮጵያ

@sheger_press
@sheger_press
13.0K viewsedited  04:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-15 14:11:49
ከደቡብ ሱዳን ተሻግረዉ ወደ ጋምቤላ ክልል የመጡ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸዉ የሙርሌ ታጣቂዎችን ወደመጡበት መመለስ ቢቻልም አሁንም በአንዳንድ አካባቢዎች ይገኛሉ ተባለ

ከደቡብ ሱዳን የኢትዮጵያን ድንበር ጥሰዉ በመግባት በተከታታይ ጥቃት ሲፈጽሙ የነበሩት የሙርሌ ታጣቂዎች ከሰሞኑ በጋምቤላ ክልል ዲማ ወረዳ ጥቃት ፈጽመዉ እንደነበር ብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ሰምቷል።

ታጣቂዎቹ መጋቢት 13 ቀን 2016 ዓ.ም ጥቃቱን ፈጽመዋል የተባለ ሲሆን አሁንም በወረዳዉ ሁለት ቀበሌያት ላይ እንቅስቃሴ እንደሚያደርጉ ስማቸዉን የማንጠቅሳቸዉ የወረዳዉ አንድ ባለስልጣን ለጣቢያችን ተናግረዋል።

ታጣቂዎቹ በአኩላ እና አቻኛ ቀበሌዎች እንቅስቃሴ እያደረጉ ይገኛሉ የተባለ ሲሆን በተለይም አኩላ በተሰኘዉ ቀበሌ በጸጥታ ሀይሎች ቅኝት እና ክትትል እየተረገ ነዉ ብለዉናል። አንዳንዶቹም በዚህ ክትትል ከመሸጉበት በቁጥጥር ስር መዋላቸዉ ተነግሯል። ከፍተኛ ቁጥር ያላቸዉ ታጣቂዎች የኢትዮጵያን ድንበር ጥሰዉ መግባታቸው ከተሰማ በኋላ እንዲመለሱ ቢደረግም አሁንም በሁለቱ ቀበሌያት እንቅስቃሴ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል።

ከደቡብ ሱዳን የሚሻገሩ ታጣቂዎች በተደጋጋሚ ወደ ኢትዮጵያ ድንበር ዘልቀዉ በመግባት በተለይም የዲማ ወረዳን ከደቡብ ሱዳን ጋር በሚያዋስኑ አካባቢዎች ጥቃቶችን ፣ እገታ እና የእንስሳት ዘረፋ ሲፈጽሙ እንደነበር ብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን መዘገቡ ይታወሳል።

@sheger_press
@sheger_press
13.8K viewsedited  11:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-13 07:00:18
Are you interested in becoming an AI engineer?

Join the Kifiya AI Mastery Training Program (Kifiya AIM 1) by Kifiya Financial Technology and 10 Academy. It's a 3-month intensive course beginning on April 29, 2024, focusing on Machine Learning and Data Engineering. Gain fast career advancement in AI and data science through industry-led projects, expert sessions, and explore fintech career opportunities in Addis Ababa, Ethiopia. Special consideration for women and vulnerable groups.

Eligibility criteria:

- Undergraduates (preferred) aged 22-34

- Has legal right to work in Ethiopia.

- Fluent in English (B1 CEFR level), with some background in Python, SQL, and Statistics.

- Ready to commit 30-40 hours weekly, with a strong work ethic and community spirit.

Submit your application by the deadline of April 17, 2024.

Application link: https://apply.10academy.org/login

Learn more about the program: https://10academy.org/kifiya/learn-more

For any question, contact us at kifiya_ai@10academy.org
16.7K views04:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-12 07:00:12
Did you miss our February edition EdTech Mondays radio show? No worries, all you have to do is click on the below link and access the full show where we highlight Ethiopia's Digital Education Strategy and Implementation Plan. Join our community and explore the innovative pathways transforming education in Ethiopia. Be part of the conversation!

#EdTechMondays #EdTechMondaysEthiopia #Ethiopia #Africa #Education #EdTech #Tech #AddisAbaba #ICT #Infrastructure #Digital #DigitalLiteracy #Shega #mastercardfoundation

Check out the full video at

12.6K views04:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-22 07:00:10
ታላቅ የምስራች ለቤት ፈላጊዎች

በ 560ሺ ብር ቅድመ ክፍያ ብቻ የቤት ባለቤት ይሁኑ

40/60 ወይም 50/50 የባንክ ብድር
ከ 10% ቅድመ ክፍያ ብቻ የቤት ባለቤት ይሁኑ
##ካሬ አማራጮች
##ስቱዲዮ 56.6 ካሬ
##ባለ 1 መኝታ ከ 77.7 -90 ካሬ
##ባለ 2 መኝታ 123.1-155.8 ካሬ
##ባለ 3 መኝታ 146.8-181.8 ካሬ
##ባለ 4 መኝታ 177.1-186.9 ካሬ
ግንባታቸው ፈጣን እና ጠንካራ በሆነ የአልሙኒየም ፎርም ወርክ ቴክኖሎጂ እየተገነቡ ያሉ።
በአንድ ህንፃ ላይ 5 አሳንሰር፣ የመዋኛ ገንዳ፣ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራ፣ የኤሌትሪክ መኪና ቻርጅ፣
24/7 የደህንነት ጥበቃ ፣ ባለከፍተኛ ፍጥነት ዋይፋይ እና እንደ ጂም፣ የውበት ሳሎን፣ ስፓ እና ሬስቶራንት ያሉ የቅንጦት አገልግሎቶችን በውስጡ የያዘ ዘመናዊ ጊቢ አፓርትመንቶች እና የንግድ ሱቆች።
0923827796 / 0938626981
እስከ 25% ልዩ ቅናሽ

በተለያዪ አማራጮች ፍላጎትቶን ሰምተን እናስጎበኞታለን

ከ CDC አፍሪካ በ 1.5 ኪ.ሜ(3 ደቂቃ በተሽከርካሪ) ርቀት ላይ የሚገኘው ሳይታችን እጅግ በጣም ፅዱ እና ምቹ ጊቢ ውስጥ ለቡ መብራት ኃይል
ከ ቻድ ኢምባሲ አጠገብ ይገኛል።
13.0K views04:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-21 07:00:10
#Kabba

ለስኬት ከሚሮጥ ጠንካራ ሰራተኛ ጀርባ ሁሌም ካባ አለ፡፡ በታክሲ ሰልፍ ድካም፣ እንግልት፣ በመጋፋት ገንዘባችን መሰረቅ ፣ደክሞን ስራ ቦታ መገኝት ...ሀሳብዎን ጣል ያድርጉ፣ ካባ የትራንስፖርት አገልግሎት በመዲናችን አዲስ አበባ ለሰራተኞች እና ለድርጅት አዲስ አገልግሎት ይዞ መጥቷል።

በተመጣጣኝ ወርሀዊ ክፍያን በመክፈል ወደ ስራዎ በጊዜ ገብተው በጊዜ ወደ ቤትዎ ይመለሱ።

አሁኑኑ ይመዝገቡ 0903534997 ይደውሉልን።
ለመመዝገብ ይሄን ይጫኑ https://bit.ly/48uCuRW
15.0K views04:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-01-15 21:00:28
የጋዜጠኛ አስፋው መሸሻ ቀብር በኢትዮጵያ እንደሚፈጸም ተነገረ!

በእሁድን በኢቢኤስ ፕሮግራም አዘጋጅነትና አቅራቢነት ተወዳጅነትን ያተረፈው አንጋፋው የራዲዮና ቴሌቪዥን ፕሮግራም አዘጋጅና አቅራቢ አስፋው መሸሻ አስከሬን ረቡዕ ጥር 8 ቀን 2016 ዓ.ም በዋሽንግተን የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ አዳራሽ ቤተሰቦቹ ወዳጆቹና አድናቂዎቹ በተገኙበት የሥንብት ሥነስርዓት እንደሚካሄድ ኢቢኤስ ቴሌቪዥን አስታዉቋል፡፡

የፊታችን ሃሙስም ጥር 9 ቀን 2016 ዓ.ም በሜሪላንድ በሚገኘው መድሃኒዓለም ቤተክርስቲያን የፍትሃት ሥርዓት እንደሚከናወንለትና ቅዳሜ ጥር 11 ቀን 2016 ዓ.ም ደግሞ ከአሜሪካ ወደ ኢትዮጵያ የአስከሬን ሽኝት ይደረግለታል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተነግሯል።

በአዲስ አበባም በቀብር ሥነስርዓቱ አፈጻጸም ዙሪያ በአገር ውስጥ ኮሚቴ ተዋቅሮ ዝግጅት እየተደረገ ሲሆን የቀብሩን ቀንና ሌሎች ተያያዥ መረጃዎች በይፋ በሚሰጥ መግለጫ እንደሚነገር ኮሚቴው አሳውቋል።ጋዜጠኛ አስፋው መሸሻ ባደረበት ህመም በህክምና ሲታገዝ ቆይቶ ለህክምና በሄደበት በአሜሪካ ዋሽንግተን ቅዳሜ ጥር 4 ቀን 2016 ዓ.ም ለሊት ህይወቱ ማለፉ ይታወሳል።

[ዳጉ ጆርናል]
@sheger_press
@sheger_press
12.8K viewsedited  18:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-01-07 20:32:56 “ሠላም ከሌለ ኮርማም ቢታረድ አይጣፍጥም” - ተፈናቃዮች

የገና በዓል በኦሮሚያ ክልል ግጭት፣ ስጋት እና ዋጋ ንረት ተጭኖታል!

በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ዞን ኪረሙ ወረዳ የተፈናቀሉ አንድ አርሶ አደር አስተያየት ሰጪ እንዳሉት “በአሉ ቀዝቃዛ ነው፡፡ የበዓልም ድባብ የለም፡፡ በዚ ላይ መንገዶች በብዛት ስለሚዘጋጉ ሽንኩርት የለም፤ ሌላውም ሸቀጥ ስለማይገባ በዓሉን አስቸጋሪ አድርጎብናል” በማለት የጸጥታው ስጋት በህይወታቸው ሁሉ ፈታኝ እንደሆነባቸው አስረድተዋል፡፡

እንደ ሰማይ ርቆ የናረው ኑሮ እንኳን በዓል ማክበር ነገን የሚያስናፍቅ ብርቱ ፈተና ደቅኗልም በማለት ያሉበትን ሁኔታ አስረድተዋል፡፡ “እርሻ ካቆምን ሶስት ዓመት ነው፡፡ ምንም የሚላስ የሚቀመስ የለንም፡፡ ከሌላ ቦታ የሚመጣው ሸቀጥማ በታም እየተወደደ ነው” ብለዋል፡፡

አሰርተያየት ሰጪው ከምንም በላይ የራቀንና የናፈቀን ያሉትንም ሲያስረዱ “ከሁሉም በላይ እኛ የምንጓጓለት እና የሚናፍቀን ሰላም ነው” ብለዋል፡፡ያለ ሰላም የሚከበር በዓልም ሆነ ደስታ ባዶ ነው ሲሉም ሃሳባቸውን አከሉ፡፡

በግጭት የተፈናቀሉ በምሥራቅ ወለጋ ዞን ኪረሙ ወረዳ የሚገኙ ነዋሪ “ሠላም ከሌለ ኮርማም ቢታረድ አይጣፍጥም” ሲሉም ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል።

በቅርቡ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ዘረጋሁ ባለው የአስተዳደር መዋቅር ከፍተኛ አለመረጋጋት በተፈጠረበት ምስራቅ ቦረና እና ጉጂ ዞን አዋሳኝ ወረዳ በሆነው ጎሮዶላ የሚኖሩት አስተያየት ሰጪ ጸጥታውና በዓሉን በማስመልከት ሃሳባቸውን ካጋሩን ናቸው፡፡ ዱሬቲ ባነታ የተባሉት እኚህ አስተያየት ሰጪ የጸጥታው ይዞታ በዓሉን ከማደብዘዝ አልፎ ህይወትን ፈታኝ አድርጎብናልም በማለት ሃሳባቸውን አጋርተውናል፡፡መከላከያ ሠራዊት እና የኦሮሚያ ጸጥታ አስከባሪዎች ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሎ ከሚጠራው ታጣቂ የገቡበት ግጭት እስካሁን መፍትሔ አላገኘም።

“በዚህ በዓል በኛ ዘንድ የሚከወን የበኣል ዝግጅት እና መንፈሱ የለም፡፡ እኔ አሁን የክርስትና እምነት ተከታይ ነኝ፡፡ ግን ባለው የጸጥታ ችግር ምንም የበዓል ስሜትም አይሰማኝም፡፡ መንግስት በሰላም እየኖርን እያለን ነው ድንገት ያላሰብነውን መዋቅር ዘረጋሁ በሚል ሰላማችን የጠፋው፡፡ይህን ተከትሎ በተፈጠረው የህዝብ ቅሬታ ሰላማችን በብዙ ተፈትኗል፡፡ እናም እኛ ጋ ምንም የበዓል ስሜት የለም አሁን፡፡ አሁን ባለንበት ሁኔታ በዓሉን ማክበርም አንችልም” በማለት ነው አስተያየታቸውን ያጋሩን፡፡

---ዘገባው የዶቼ ቬሌ ነው----

@sheger_press
@sheger_press
13.2K viewsedited  17:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-01-07 19:22:01 እንድታውቁት

ከቦሌ - በኦሎምፒያ - መስቀል አደባባይ - ብሔራዊ ቤተ -መንግሥት  እንዲሁም አራት ኪሎ በሁለቱም አቅጣጫ ከነገ ታህሳስ 29/2016 ጀምሮ ሞተር ሳይክሎችና ከሁለት ቶን በላይ የሆኑ ከባድ ተሽከርካሪዎች መንቀሳቀስ እንደማይችሉ  የአዲስ አበባ ፖሊስ  አሳስቧል።

በመንግዶቹ ክልከላውን የሚገልፁ ምልክቶች መተከላቸውን ያስታወቀው ፖሊስ የተላለፈውን መልዕክት በማያከብሩ  አሽከርካሪዎች ላይ ህጋዊ  እርምጃ እንደሚወስድ አስታውቋል፡፡

@sheger_press
@sheger_press
12.6K views16:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ