2023-10-10 00:38:49
ፓስፓርትን በተመለከተ የተከፈቱ ሀሰተኛ የማኅበራዊ ሚዲያ ገጾች ላይ የኢፕድ መረጃ ማጣሪያ ዳሰሳ አድርጓል
በአጭበርባሪዎቹ ላይ ርምጃ እየተወሰደ መሆኑንም አረጋግጠናል
***
ሰሞኑን ለኢፕድ መረጃ ማጣሪያ ገጽ ከሚደርሱት የመረጃዎችን አጣሩልን ጥቆማዎች መካከል ከፓስፓርት አገልግሎት ጋር በተያያዘ የተከፈቱ የቴሌግራም አካውንቶችን የተመለከተው ይገኝበታል።
በኢሜግሬሽን እና ዜግነንት አገልግሎት ስም እና በሚሰጠው አገልግሎት ዙሪያ የተከፈቱ እና በዚያ በመጠቀም ተገልጋዩ ላይ መደናገርና የገንዘብ ማጭበርበር የሚፈጽሙ ሀሰተኛ ገጾች እንዳሉ ማረጋገጥ ተችሏል።
ብዙዎቹ በርካታ ተከታይ ያላቸው በተቋሙ ስም የተከፈቱና ፓስፓርት እና ተያያዥ አገልግሎቶችን በተመለከተ መስፈርቶችን በመጥቀስ ገንዘብ የሚጠይቁ መሆናቸውን የኢፕድ መረጃ ማጣሪያ አረጋግጧል።
የኢፕድ መረጃ ማጣሪያ ያነጋገራቸው የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሰላማዊት ዳዊት በተቋማቸው ስም በርካታ ሀሰተኛ የቴሌግራም ቻናሎች ተከፍተው ህብረተሰቡን በማጭበርበር ላይ መሆናቸውን እናውቃለን፤ በዚህ ማጭበርበር ላይ የተሳተፉ ግለሰቦች ላይም ሕጋዊ ርምጃ ወስደናል ብለዋል።
በቀጣይም መሥሪያ ቤታቸው ይህንኑ ተግባሩን አጠናክሮ ይቀጥላል ያሉት ወ/ሮ ሰላማዊት፤ ኅብረተሰቡም ይህንን ተገንዝቦ ሕጋዊውን መንገድ እና በተቋሙ ትክከለኛ የቴሌግራም ቻናል ላይ የሚለቀቀውን መረጃ ብቻ እንዲከታተል አሳስበዋል።
ትክክለኛው የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት የማኅበራዊ ሚዲያ አድራሻዎች ሊንክ ከታች ተያይዟል።
https://t.me/IcsEthiopiaOfficial
https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=887563862734676&id=100044432109537&mibextid=Nif5oz
12.6K viewsSeyoum Teshome, 21:38