Get Mystery Box with random crypto!

Natnael Mekonnen

የሰርጥ አድራሻ: @natnaelmekonnen21
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 173.42K
የሰርጥ መግለጫ

በቀጥታ መረጃዎችን ለመስጠት ሲፈልጉና ማስታወቂያ ማሰራት ከፈለጉ 👉 @NatnaelMekonnen7
Facebook.com/natnaelmekonnen.et
Instagram.com/natnaelmekonnen21

Ratings & Reviews

1.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 382

2022-05-27 20:03:16
Must Listen

#Ethiopia : ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!" በሚል ቁጭት ነው ኢትዮጵያን የሚመጥን የመከላከያ ኃይል ለመገንባት እየሰራን ያለነው።

የጦር ኃይሎች ም/ጠ/ኢታማዦር ሹም ጀኔራል አበባው ታደሰ
25.2K views17:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-27 19:19:08 ፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ

የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ የኦፕሬሽን ዋና መምሪያ ኃላፊ ሙሊሳ አብዲሳ የሰጡት ማብራሪያ ፦

#Ethiopia : " ህግ ማስከበር ሲባል ብሄርን አይለይም፤ ሃይማኖትን አይለይም ፤ የፖለቲካ status አይለይም ፤ የሚዲያ አክቲቪስት ማንም ማንም ይሁን የSocial Status ፣ ሃይማኖቱ ምንም መሰረት አያደግም። ህግ ለሁሉም እኩል ነው። እንደ ፖሊስ ሞያዊ ነፃነቱን ጠብቀን የምርመራ ስራ ጥቆማ ሲደርሰን በየትኛውም አካል ላይ ህግ የማስከበር ስራ እየተሰራ ነው የሚገኘው።

እንደሚታወቀው በአሁን ሰዓት ብዙ የሚዲያ ተከታይ ያላቸው ሰዎች ብሄርን ከብሄር የሚያጋጩ፣ ሃይማኖትን ከሃይማኖት የሚያጋጩ ፣ ጥርጣሬን የሚፈጥሩ የህዝቦቻችንን ፣ አጠቅላይ የኢትዮጵያን ህዝብ አብሮነት የሚፈታተኑ እነሱ ጥቅም የሚያገኙበትን በሚዲያ ዘመቻ የሚያደርጉትን በሽብር ድርጊት ውስጥ የተሳተፉትን ሰዎች በማስረጃ ላይ ሆነን መረጃ በመሰብሰብ በህግ ቁጥጥር ስር በማዋል ወደ ህግ እያቀረብን ነው።

ስለዚህ የሆነ ሚዲያ ወይ ጋዜጠኛ የሆነ ምንም ቢሆን እንደ defense ሊቀርብ አይችልም። በወንጀል ውስጥ የተሳተፈ መረጃ የተገኘበት ማንኘውም ሰው ላይ እርምጃ ይወሰዳል፤ በህግ ይጠየቃል፤ ግልፅ በሆነ ነፃ በሆነ ፍርድ ቤት አቅርበን ምርመራ ስራ እንሰራለን።

ስለዚህ በአሁን ሰዓት የሚዲያ ስራ ላይ የተሳተፉ ሰዎች እሱን እየተጠቀሙ አጠቃላይ stability እንዳይኖር የሆነ title እየሰጡ እንደ ገቢ ምንጭ የኢትዮጵያ ህዝብ ያልተረዳው ነገር እነኚህ አክቲቪስት የተባሉ ታሰሩ የተባሉ ግለሰቦች እንደ ገቢ ምንጭ የሚጠቀሙት አይነት ነው ያለው።

በምርመራ እንዳገኘነው አንድ ግለሰብ ከ4 ዩትዩበሮች ጋር ውል አስሯል፣ ከአንዱ ዩትዩበር 25 ሺህ ብር ነው የሚከገለው በአንድ ጊዜ እስከ 100 ሺህ ነው የሚከፈለው፤ ይሄን ለማድረግ ተመልካች እንዲያገኝ ለማድረግ ብሄርን ከብሄር የሚያጋጭ፣ ሃይማኖትን ከሃይማኖት የሚያጋጭ ፣ ወይም የመንግስትን ተቋም ፣ ወይም የመንግስትን ተሿሚዎች በሚያሸማቅቅ መልኩ ግልፅ በሆነ መልኩ characterize በማድረግ title እየሰጡ እንዲህ እያደረጉ ተመልካችን፣ like , share በብዛት እንዲያገኙ ብዙ ነገር በማድረግ ይሄን መሰረት በማድረግ destabilize በማድረግ የተለያዩ የወንጀል ድርጊቶችን፣ የሃሰት የውሸት ፕሮፖጋንዳዎችን በመልቀቅ ህዝቦች አብረው እንዳይኖሩ ሀገሪቱ በሰላም ተረጋግታ እንዳትኖር አጠቃላይ የማወክ ስራ እና ጥርጣሬ በሚፈጥር መልኩ ጥላቻን በውሸት ዘመቻ እያደረጉ ህዝቡ ላይ ይሄን እየጫኑ ለራሳቸውን የገቢ ምንጭ አድርገው ሀገሪቷን አደጋ ላይ ለመጣይ የሚሰሩ አካላት ናቸው በቁጥጥር ስር የዋሉት።

ይሄንን ደግሞ ፖሊስ ህግን መሰረት በማድረግ ፍርድ ቤት በማቅረብ የጊዜ ቀጠሮ በመጠየቅ በራሳቸው ፍላጎት በሚፈልጉት ጠበቃ ተወክለው በቤተሰቦቻቸው እየተጠየቁ ይሄን የምርመራ ስራ ፣ የህግ ማስከበር ስራ በደንብ እየተሰራ ነው።

ስለዚህ በአጠቃላይ ማንኛውም ሰው ከህግ በታች ነው።

ከህግ በታች እስከሆነ ድረስ ጥቆማ የቀረበበትን እንደፖሊስ ሙያን መሰረት አድርጎ የህግ የማስከበሩን ስራ ማንኛውም ሰው ላይ በየትኛውም ላይ ብዙ እሱን የሚከተል ሰው ሊኖር ይችላል ከዚህ በፊት እንደተደረገው ፣ የሃይማኖት ሰው ሊሆን ይችላል፣ ማንኛውም ሰው ሊሆን ይችላል ዋናው መሰረት የህግ ስህተት አለ ? ወይስ የለም ? የሚለው ነው። ስለዚህ እስካሁን ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ ስም ብዙ ነገሮች ተችለዋል በአሁን ሰዓት ግን የለየለት የሽብር ስራ ፣ የሽብር ፈጠራ ፣ ሀገርን የማፍረስ ስራ ፣ ህግ የሌለ እስከማስመሰል ፣ የፍትህ ተቋማት እርምጃ መውሰድ አይችሉም የሚያስብል ደረጃ ላይ ደርሶ ሀገርን የማፍረስ ተልዕኮ ላይ እየሰሩ ያሉት አካላት ላይ የህግ የበላይነት ለማስከበር ከምን ጊዜውም በላይ የፌዴራል ፖሊስ ከሌሎች የፍትህ ተቋማት ጋር በመሆን የምርመራ ስራን እየሰራ ይገኛል። "

የፌደራል ፓሊስ ወንጀል ምርመራ
28.1K views16:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-27 18:47:17
ሀጂ ዑመር እድሪስ "ከስልጣን እንደተነሱ ተደርጎ የተወሰነው ውሳኔ በየትኛውም ተቋም ተፈጻሚነት የለውም" ተባለ!

#Ethiopia : ተቀዳሚ ሙፍቲ ሃጂ ዑመር ኢድሪስ፤ ትናንት በሸራተን ሆቴል በተደረገ ስብሰባ ከሥልጣን መነሳታቸው በየትኛውም ተቋም ተፈፃሚነት እንደሌለው የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አስታወቀ፡፡

ም/ቤቱ በዛሬ መግለጫው፤ ትናንትና ግንቦት 18 ቀን 2014 ዓ.ም `የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት የአስቸኳይ ጠቅላላ ጉባዔ ስብሰባ ውሳኔዎች` በሚል በአዲስ አበባ ሸራተን አዲስ ሆቴል የተካሄደውን ስብሰባም ህገወጥ መሆኑን ገልጿል ፡፡

ህገ ወጥ የተባለው የሸራተኑ ስብሰባ ባካሄደው ምርጫ የኦሮሚያ እስልምና ጉዳዮች ም/ቤት ፕሬዝዳንት ሼኽ ሀጂ ኢብራሒም ቱፋ የመጅሊሱ ፕሬዝዳንት እንዲሁም የደቡብ ክልል እስልምና ጉዳዮች ም/ቤት ፕሬዝዳንት ሼኽ አብዱልከሪም ሼኽ በድረዲን የመጅሊሱ ምክትል ፕሬዝዳንት አድርጎ መርጦ ነበር።

ከዚህ ባለፈም በስብሰባው ተቀዳሚ ሙፍቲ ሀጂ ዑመር እድሪስ እና ምክትላቸው ጄይላን ከድር (ዶ/ር) እንዲሁም ሌሎች የመጅሊሱ አመራሮችም ከቦታቸው እንዲነሱና የፈትዋ ምክር ቤት አመራር እንዲሆኑ ተወስኖ ነበር።

ውሳኔው ተቀባይነት እንደሌለው በመግለጽ ዛሬ አርብ ግንቦት 19 ቀን 2014 ዓ/ም መግለጫ የሰጠው የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ስብሰባውንም ሆነ የስብሰባውን ውሳኔ ውድቅ አድርጓል፡፡
28.2K views15:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-27 18:47:11
የስራ ማግኛ ኦንላይን ፕላትፎርም /ሊንኮችህ/ ዝርዝር ለማግኘት

Join our telegram

https://t.me/+kpVVJnBHB5ZhZjI0
24.8K views15:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-27 17:19:44 በስዊዘርላንድ በአማራና አፋር ክልሎች ጉዳት ለደረሰባቸው ተቋማት የሚሆን ሃብት የማሰባሰብ ዘመቻ ተጀመረ Swizerland

#Ethiopia : በስዊዘርላንድ የሚገኙ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች በአማራና በአፋር ክልሎች ጉዳት የደረሰባቸውን የጤና ተቋማትና ትምህርት ቤቶች መልሶ ለመገንባት የሚያስችል የሃብት ማሰባሰብ ዘመቻ በይፋ ጀምረዋል::

በመርሃ ግብሩ የተሳተፉት በስዊዘርላንድ የኢትዮጵያ አምባሳደር ዘነበ ከበደ÷ በአገሪቱ የሚኖሩ የዳያስፖራ አባላት በአገራችን በጦርነቱ ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖች ለመርዳት እስከዛሬ እያደረጉት ላለው አጠቃላይ ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡

ሪስቶር ሆፕ እና ገበታ ለወገኔ በተሰኙ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች የተጀመረው የሃብት ማሰባሰብ ስራም እጅግ የሚያበረታታ መሆኑን የገለፁት አምባሳደሩ÷ የሃብት ማሰባሰቡ ስራ የተያዘለትን ግብ እንዲመታም ኤምባሲው አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል፡፡

በበይነ መረብ የተሳተፉት የጤና ሚኒስቴር ከፍተኛ አማካሪ ዶክተር ማርታ ምንውየለት በበኩላቸው÷በሁለቱ ክልሎች ጤና ተቋማት ላይ በጦርነቱ የደረሰውን ጉዳት በመንግስት እንዲሁም በአጋር አካላት እየተደረገ ስላለው የማደራጀት ስራ እና ያለበትን ደረጃ በተመለከተ ገለጻ አድርገዋል፡፡

ሁለቱ በጎ አድራጎት ድርጅቶች ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖቻችንን ለመደገፍ እያደረጉት ያለውን እንቅስቃሴ ያደነቁት ክፍተኛ አማካሪዋ÷ የተሰበሰበው ሃብት ወደ አገር ቤት ደርሶ የታለመለትን ዓላማ እንዲያሳካ አስፈላጊውን ትብብር እንደሚደርግ ተናግረዋል፡፡

በዕለቱ በነበረው የበይነ መረብ ውይይትም ከተሳታፊዎች ከ7 ሺህ በላይ የስዊዝ ፍራንክ የተሰበሰበ ሲሆን÷ በቀጣይም ስራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል መገለጹን ከኤምባሲው ያገኘነው መረጃ ያመላክታል::
28.6K views14:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-27 16:47:47
በህገ ወጥ መንገድ ሲጓጓዝ የነበረ ከ5 ሺህ 100 በላይ ተተኳሽ ጥይት በማኅበረሰብ ጥቆማ መያዙን የዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር እና የአርጎባ ልዩ ወረዳ ፖሊስ ፅሕፈት ቤት አስታውቀዋል፡፡

#Ethiopia : የአርጎባ ልዩ ወረዳ ፖሊስ ፅሕፈት ቤት ምክትል ኮማንደር መሐመድ ባህሪታ እንደገለፁት ÷ ከህዝብ በደረሰ ጥቆማ በወረዳው ፖሊስ ጽሕፈት ቤት በተካሄደ ክትትል 1 ሺህ 900 “ኢንፎርት” ተተኳሽ ጥይቶች እና 60 የክላሽ ጥይቶች በድምሩ 1 ሺህ 960 ተተኳሽ ጥይቶች ተይዘዋል።

ጥይቶቹን የጫነው ባጃጅ ኬላ ጥሶ ከፀጥታ አካላት ለማምለጥ ሙከራ አድርጎ ነበር ተብሏል፡፡

በተመሳሳይ በዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ጋዝጊብላ ወረዳ አንድ ግለሰብ ”ላልኪው” አካባቢ የሚገኘውን ኬላ በሌላ መንገድ በማሳበር በህገ ወጥ መንገድ 2 ሺህ 141 የክላሽ ጥይት በኬሻ ጠቅልሎ ወደ ላስታ ሊያሻግር ሲሞክር በወረዳው ፖሊስ ፅህፈት ቤት በቁጥጥር ሥር ውሏል፡፡

ተጠርጣሪዎቹ በህግ ቁጥጥር ሥር ውለው ጉዳዩያቸው እየተጣራ እንደሚገኝ ተመልክቷል፡፡

ኅብረተሰቡ የህገ ወጥ መሳሪያ ዝውውርንና ንግድን ለመከላከል በሚደረገው እንቅስቃሴ እያደረገ ያለውን ያልተቆጠበ ትብብር አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ መተላለፉን ከኢዜአ እና ከአርጎባ ልዩ ወረዳ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
28.7K views13:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-27 16:38:42
#Ethiopia : በአማራ ክልል በህግ ማስከበሩ ዙሪያ የተሰጠ መግለጫ የምዕራብ ጎጃም ዞን ዋና ሰተዳዳሪ
27.1K views13:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-27 15:29:47
በሀሰተኛ ገንዘብ ነዳጅ ቀድቶ ለማምለጥ የሞከረው አሽከርካሪ ከቆመ ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ ህይወቱ አለፈ

#Ethiopia : በሃሰተኛ ገንዘብ ነዳጅ ቀድቶ ለማምለጥ የሞከረው አሽከርካሪ ከቆመ ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ ህይወቱ ማለፉን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡ የትራፊክ አደጋው የደረሰው ግንቦት 18 ቀን 2014 ዓ.ም ከሌሊቱ 6፡30 ሰዓት ገደማ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 ልዩ ቦታው ሚካኤል አደባባይ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ መሆኑ ተመልክቷል ፡፡

የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 1- 30262 አ.አ የሆነ ተሽከርካሪ ከጀሞ 1 አቅጣጫ ወደ ሚካኤል አደባባይ እየተጓዘ 67 ማዞሪያ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በሚገኝ ነዳጅ ማደያ ውስጥ ነዳጅ ሊቀዳ መግባቱን በአዲስ አበባ ፖሊስ የትራፊክ አደጋ ምርመራ ቲም ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ስጦታው ወልዴ ገልፀዋል፡፡

አሽከርካሪው ነዳጅ ከቀዳ በኋላ አምስት ባለ መቶ ሀሰተኛ የብር ኖቶችን ለነዳጅ ማደያው ሰራተኛ ሰጥቶ በሚሄድበት ወቅት ነዳጅ ቀጂው የብሮቹን ትክክለኛነት በመጠራጠሩ ሊያስቆመው መሞከሩን የጠቀሱት ምክትል ኢንስፔክተር ስጦታው አሽከርካሪው ግን በፍጥነት በማሽከርከር ለማምለጥ ጥረት ሲያደርግ መንገድ ዳር ቆሞ ከነበረ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3A- 60203 አ.አ ከሆነ አይሱዙ ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ ህይወቱ ማለፉን ተናግረዋል፡፡

በወቅቱ አብረውት ተሳፍረው የነበሩ 2 ግለሰቦች ላይም ከባድ የአካል ጉዳት በመድረሱ ተጎጂዎቹ በህክምና ላይ እንደሚገኙ ከአዲስ አበባ ፖሊስ ያገኘነነዉ መረጃ አመልክቷል፡፡
29.9K views12:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-27 15:29:47
ናሽ የጥርስ እና የዓይን ህክምና ክሊኒክ
        Nash Dental and Optometry Clinic
 
ናሽ የጥርስ እና የዓይን ህክምና ክሊኒክ ዘመኑ ባፈራቸው መሳሪያዎ ች በመታገዝ ሙሉ የጥርስና የአይን ህክምናን በመስጠት ላይ ይገኛል::  ከምንሰጣቸው አገልግሎቶች መካከል በከፊል
➢  
➢ መጥፎ የአፍ ጠረንን ማከም
➢ የቆሸሹ ጥርሶችን በማሽን እናፀዳለን
➢ በህክምና መዳን የማይችሉትን ጥርሶች መንቀል
➢ ወጣ ገባ ያሉ ጥርሶችን በ ኦርቶዶንቲክ አፕላይንስ እና በብሬስ ማስተካከል
➢ የጥርስ ስር ህክምናን መስጠት
➢ የተቦረቦሩ ጥርሶችን እንሞላለን
➢ የተነቀሉ ጥርሶችን በሰው ሰራሽ አርተፊሻል መተካት
➢ የጥርስ ራጅ አገልግሎት መስጠት
 
➢ የረዥም እርቀት፤ የአጭር እርቀት እና ከእድሜ ጋር ተያይዞ የሚመጣ የቅርብ እይታ መቀነስ ምርመራ እና ህክምና
➢ ሁለት ዓይኖች ተቀናጅተው ያለመስራት ችግር ምርመራ እና ህክምና
➢ በተለያዩ ምክንያቶች የሚከሰት የእይታ መቀነስ ችግርን ምርመራና ህክምና
➢ የህፃናት የአይን ምርመራና ህክምና
➢ ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን የአይን መነጽሮች የሎው ቪዥን ድጋፍ መስጫ የቪዥን ቴራፒ መሳሪያዎች መለካት ማስተካከል እና ማዘዝ
 
 
በሁሉም የህክምና አይነቶች ቅናሽ አድርገናል
      አድራሻ: ቁጥር 1 ሜክሲኮ ገነት ሆቴል ፊት ለፊት ካሳ ግራንድ ሞል 4ኛ ፎቅ
                       ቁጥር 2 ሰሚት ሳፋሪ ፍርድ ቤት ፊት ለፊት ገሊላ ፕላዛ
                       Tel: 0905262626, 0913858561
26.1K views12:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-27 15:29:47
https://t.me/tedtech https://t.me/tedtech
በድጋሚ ከታላቅ ቅናሽ ጋር ገባ

Door Bottom seal strip Stopper
(ዘመናዊ የበር እስር መድፈኛ)

በቀላሉ በር ስር በመድፈን ምንም አይነት ቆሻሻ ፣ በራሪ ነፍሳት ፣ አይጥ ና ንፋስ ወደ ቤት ወስጥ እንዳይገባ የሚከላከል በአይጥ እንዳይበላ ኬሚካል የተደረገበት
ዋጋ-799ብር
------------------------------------------------
ሌላ አዲስ የገብ እቃዎችን
https://t.me/tedtech https://t.me/tedtech
-Push up Board (የፑሻፕ መስሪያ)..1500ብር
-Derma Roller (ፀጉር ማብቀያ)....799
-Boya Dual Mic (የድምፅ መቅጃ).....1800

ይደውሉልን 0961276575 @theo41)

አድራሻ
ቁ-1: ቦሌ ት/ቤት ፊት ለፊት አለምነሽ ፕላዛ ምድር ላይ ሱ.ቁ - 014
ቁ-2:ቦሌ(አትላስ) ግሬስ ፕላዛ 1ኛ ፎቅ ላይ
25.5K views12:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ