Get Mystery Box with random crypto!

ኦፍቲ ቲዩብ-ልበ ጥሞና

የቴሌግራም ቻናል አርማ lebtemona — ኦፍቲ ቲዩብ-ልበ ጥሞና
የቴሌግራም ቻናል አርማ lebtemona — ኦፍቲ ቲዩብ-ልበ ጥሞና
የሰርጥ አድራሻ: @lebtemona
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 195

Ratings & Reviews

4.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 15

2022-06-27 08:15:27 እጅግ ታላቅ የከተማ ወሬ

እሁድ ማለዳ 12፡00 ሰዓት ከዓለምገና መነሻው የሆነ ሀገርህን እወቅ እና "ምርጥ ዘር " መጽሓፍ ዙሪያ ውይይተ- ትምህርተ-ጉዞ ወደ ድንቋ ከተማችን ብሾፍቱ/ደ.ዘ/ የኦፍታና የጉርብትና ህብረት ለአባላቱና ፍላጎቱ ላለው ሁሉ አዘጋጅቷል።

አብረን እንጓዝ?

ለትራንስፖርትና ተጓዳኝ ወጭዎች በኪስዎ ይያዙና ኮንትራት መኪና አይናውን ለማዘጋጀት ያስችለን ዘንዳ ስለመሄድዎ በ0911878798 ደውለው ይመዝገቡ።

አሁኑኑ!
24 viewsጌቱ በቀለ, 05:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-26 17:55:48
25 viewsጌቱ በቀለ, 14:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-26 17:55:30 ዛሬ ሰኔ 19/2014ዓም። አለምገና ሰማይ ስር በፈለገ ብርሃን ቤተመጽሓፍት ይህ ሆነ

የንባብ ባህልን ለየማህበረሰቡ የትውልድ ክፋዮችን አበርካች በሆነው ቤተሰብ ውስጥ ማዋለድ ይጠበቅብናልን ግቡ ሆኖ በሚከወነው አንደኛው የአቶ ጌቱ በቀለ የንባብ ዘመቻ ውስጥ ዛሬ በኦፍታና የጉርብትና ህብረት አደረጃጀት ላይ የሚፈጸመው የተቀጠረው ሁለተኛው በቤተሰብ ደረጃ የጋራ መጽሃፍ አንብቦ የመወያየት መርሃ ግብር የአዲሱ እንግዳ "ኑሮና አእምሮ" መጽሓፍ ዙሪያ በይልማ አድነው ሰለሞን ዘውዴ እና ጌቱ በቀለ ቤተሰብ መካከል የንባብ ውይይቱ በመጽሓፉ ዙሪያ ተከናውኗል።

ሳምንት 3ኛው እንዲነበብና እንድንወያይበት የተቀተረው መጽሓፋችን የኃይለሚካኤል ድረስ "ምርጥ ዘር" ሲሆን በተቀጠረ የሀገርህን እወቅ መርሃ ግብራችን ላይ በጉብኝት ግዜአችን ሰዓት ክፍል ላይ እንነጋገርበታለን።

በዛሬው ውይይት ግዜያችን ያማረም ግዜ ተሰጣጥተናል። ለመጣችሁ ሁሉ እናመሰግናለን።

መርሃ ግብሩ ለሁሉም ክፍት ነው። ተጋብዛችኋል።

ማንበብ አለማወቅን ይገልጻል።
ከማማረር ማምረር።
በድንቁርና ላይ እናምጽ።
19 viewsጌቱ በቀለ, 14:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-22 06:50:51

በአሁኑ ሰዓት በአለምገና ሰማይ ስር በ1ሽህ ሜትር ዙሪያ ገብ በምትሰማው የኦፍታና የማህበረሰብ ሬዲዮዬ በድምጽ እና በማህበራዊ ሚዲያው ማከናወን የምችለው ሁለት ነገር ብቻ ይመስለኛል።
የማህበረሰቤን ሕጸጽ መጠቆምና በኔ የተጠቆመው ተደግሞ እንዳይኖር መተጋትን!

የእኔ እውነት ይሄን ይነግረኛል!
በየትኛውም የኢትዮጵያ ጥጎች የምንጋደለውም ሆነ የምንገደለው
ተመችቶን።
ወደን።
ፈቅደን
እና አምነንበት ነው እላለሁ።

"ምክክር" የሚል ሀገራዊ አጀንዳን ይዘናል። ግና ይህን አዝጋሚውን መንገዳችን ጥሩ ነው አልልም።

በኔ በኩል የምታዘበው አንድ መንፈሳዊ ድብቅ ምስጢር አለን አምኜ ተቀብያለሁ። የኢትዮጵያውያንን ደም እያፈሰሰና እያፋሰሰ ለጌታ ሉሲፈርና ነገደ አጋንንቱ የሚያጠጣ ስውር የግድድል ደጋሽ መኖሩንና፤ ሀገር ላይ ሁሉም ነገር በግዜው እንዳይከናወን እንደመርግና አዚም ህዝቡና አስፈፃሚዎቹ ላይ ተጭኖ የሚያሳንፍና ለውጥን የሚያዘገይ ስውርሽአካል እንዳለ!

መላ የኢትዮጵያ ህዝብ ይህን" ህገ አራዊት" ወዶትና ፈቅዶት የተቀበለው ህገ መንግስቱ ነው እላለሁ። አለቀ መቼም እንዳይቀየር የሚሳሳለት ውድ እንቁው!

ባይሆን ኖሮማ

በአዲስ የብዙሃን ፍላጎት ህገ-መንግስቱ እንዲሻሻል ለመትጋት እቅልፍም ሊኖረን አይገባም ከማለት ይልቅ ህገ መንግስቱ ባለበት የህግ አናቅጽታት ክፍተት የተነሳ ከጎኑ ወገኖቹ ሲጎድሉና ሲገደሉ አይኑ እያየ የምን ቀጠሮ ማንዛዛት ነው።

የምንስ ስራ ገብቶ መስራት ነው። የምንስ ፓርላማ ስብሰባ ነው ህሊና ጸሎት..ብሄራዊ ሀዘን ወዘተ እያሉ "መደናቆር" ነው።

መሆን ካለበትም!
ሞት ሰልችቶናል።
በቃን መጋደሉ።
ስራ በየትኛው ጥግ አቁሙ። እናቁም። ምከሩ እንምከር። የህገመንግስት ማሻሻያ ድምጸ ውሳኔ ህዝብ ባስቸኳይ ይሰጥ።

ከዚያም ቀጥሎ ለሰላሙ ሁሉም አንድ አፍ ተናጋሪ አንድ ልብ መስካሪ ሆኖ ይቁም።
ነው መባል የነበረበት

እኛ ማለት "ቅድሚያ የሚሰጠው" የሚለው ቃለ ሀረግ በመዝገበ ቃላታችን ውስጥ እንጅ በድርጊታችን ውስጥ የማይታወቅ ህዝብና ሀገር ነን። በሌላ ቋንቋ ከሊቅ እስከ ደቂቅ በደመነፍስ እንደ እንስሳ ተኗኗሪ ህዝብ ነን ብዙ ገመናችን ያስብለናል


መርጦ አልቃሽነትንምም..ያንዱ ህመም ለሌላው አለመሰማትና አለመቆርቆር መንፈስንም በእግዚሃብሔር ስም አውግዣለሁ።

ከማማረር ማምረር።
በድንቁርና ላይ እናምጽ።
ማንበብ አለማወቅን ይገልጻል።
አንባቢ ትውልድ ለሀገር ግንባታ-የ2014 ሙሉ ዓመት ሀገር አቀፉ የንባብ ቀን መሪ ቃል።
33 viewsጌቱ በቀለ, 03:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-21 09:18:20

ኑሮም እውቀትም ህይወትም ከተወልድናቸው እናት እና አባት እንዲሁም የትመጣ ጎሳችን እልፍ የማይል ነውውን በገዛ እጃችን ተፈርደን ባሻገር ያለውን ታላቁን የመቻል እግዚሃብሔራዊ ማንነታችን ዘንግተን ከጨለማ ውስጥ በራሳችን ላይ ከርችመን ዘመንን ዝም ብሎ ለመቁጠር ተፈርደናል።

ተነሱ ከአዚማሙ እንቅልፋምነታችን እንባንን

በድንቁርና ላይ እናምጽ።
ከማማረር አምርረን፤ ንባብን እንወዳጅ።

ማንበብ አለማወቅን ይገልጻል!

አለም የምትድነው በንባብ በኩል ነው። ሁሉ ነገረ መፍትሔዎችዋ ንባብ ውስጥ ተደብቀውባታል። በተለይ ለኢትዮጵያውያን
30 viewsጌቱ በቀለ, 06:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-21 07:22:33 ዛሬ መዳን ለሁላችሁም ሆነ።
ይሄን ሀቅ ለማታውቁ ሁሉ
ለሌሎችም ይደርስ ዘንድ አጋሩት

ሁሉም በስራ ድርሻ ክፍፍሉ ላይ 24 ሰዓት ንቁ ነው
እነማን

ነገደ አጋንንት

ውለው ይደሩለት እንጅ ሃይል ቀላቢዎቹ ክፉአን የሰው ልጆች ሁሉ ነን ነቅቶ ውሎ የማደራቸውና የ24 ሰዓት ቆይታ ፊልፕስነታቸው ምስጢር

የምቸከችከው ገብቷችኋል ወይ

#ለማስታወስ

አጋንንት እስከተባረሩበት የትምክህትና ትዕቢት ዋዜማቸው ዕለት ድረስ ሃይልን የሚሞሉት ከፈጣሪያቸው ነበር። ሲጣሉ..ከክብራቸው ሲጎድሉ ግን የሰው ልጆችን እና እንስሳት ደምን በመላስና በማፋሰስ የመሰንበቻ ሃይልን በመምጠጥ በዘለዓለማዊ ባላንጣነት ከአዳም ዘር ሁሉ ጋር ጥርስ ተናክሰው መኖርን ቀጠሉ።

ሃይልን የሚጎናጸፉት በልዩ ልዩ መልክ ነው። በንዴት በቁጣ በክፉ ሀሳብ እና ስራዎች እንዲሁም ቅንቀና በምቀኝነት....ወዘተ ድርጊያዎችን በኩል ሃይልን እያስወጡን በመመጥመጥ።

ሀይላችን ሲባክን ይረከቡንና ሌላ የክፋት/ማሳሳት ድርጊያቸው ታድሰው ይነሳሉ...ይዘምታሉም። መልካምነትን ስናበዛ በጾም በጸሎት ውስጥ ስንቆይ ሀይል ስለማንለቅላቸው 24 ሰዓት በትጋት ከሚከውኑት አሳስቶ ሀይል ጉንጸፋ ድርጊያቸው ተልፈስፍሰው ትቢያ ላይ ሲርመጠመጡ ይከርማሉ። ቢያንስ ጥለውን ወደ ሌላ ስፍራ ሀይል አባካኝ ህዝብ ሰፈር/ሀገር ይዘምታሉ።
አሁን ላይ እነ ሩሲያ ሰፈር በገፍ የደም ድግሱን እየበሉ ነው ኢትዮጵያችንም አንዳንድ ስፍራ ላይ የግድድላችን ድግስ ላይ ታድመው ከጥጋብ አልፈው ስካር ጥግ ደርሰው ደማችንን እየተራጩበት ነው።

ይህ እውነት ነው።
እያንዳንዳችን ጎን በሰባቱ ሻክራችን ከእግዚሃብሔር በየዕለቱ የምንሞላውን ሃይላችንን ለመጥለፍና
ሃይል ለመሞላት የቁጣው ክሹፈ መላክ ሳጥናኤል፤
የኩራትና ትዕቢት ጌታ ሉሲፈር
የንፉግነት ጌታ ማሞን
የሆዳምነትና እልጠግብ ባይነታችን አግበስባሽነት ጌታ ብሄልዜቡል
የጥሎ ማለፍና ምቀኝነት ጌታ ሌዋታን
እንዲሁም የስራ ጠልነትና ስንፍና ጌታ ቤልፋጎር
ለዝሙተኝነታችን ለስካራችን ለቁማራችን ለዘርፈ በዛው ሴሰኝነታችን በልበልን ሊመክሩን ጌታ እስማንድዮስ እና ጋሻ ጃግሬዎቻቸው ሊሰለቅጡን ከበውን አሉ

ካልነቃንና ካልተቃወምናቸው በእያንዳንዳችን ጎን የየነገዳኑ ተላላኪዎቻቸው ሰፍረው ሃይላችንን ለመቆያቸው ሊመጥጡ አስፍስፈው 24 ሰዓታት ያለመታከት ይዞሩናል። ለጥፋተ/ስህተተ- አይነታት ስንመቻችላቸው ሃይል ሰልበውብን ከልፍስፍስነታቸው ይበረቱበታል።

ሰይጣንና ሠራዊቱ ህልውናው ሁሉ በሰው ልጆች ማይምነትና ድንቁርና ላይ የተመሰረተ ነው።

ለማምለጥ

ከማማረር ማምረር።
በድንቁርና ላይ ማመጽ።
ማንበብ አለማወቃችንን እንዲገልጽልን መርጠን እናንብብ

ዘንድሮ ክረምትን ስንት መጽሃፍት ሊያንብቡ አቀዱ

መዳንም ፈውስም ከድህነት ማምለጥና ሰላማችንና ወፍቅራችን በመጽሓፍት ሆድቃ ውስጥ ተሸሽገውብናል።
ስናነብ ብቻ ከዘርፈ በዛው ደዌያችን እንድናለን።

ዘመኑን የሚዋጅ ትውልድ ከንባብ አምባ አሁን
32 viewsጌቱ በቀለ, 04:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-17 16:41:07
57 viewsጌቱ በቀለ, 13:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-17 16:40:24
55 viewsጌቱ በቀለ, 13:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-17 09:03:08 ታላቅ የግቢ ወሬ

ብሔራዊው የንባብ ቀናችን 2 ቀናት ቀሩት።

6ኛ ዓመቱን ያስቆጠረው፤ የኢትዮጵያ የንባብ ቀን ይኑራት ፤ቀኑም የአመቱ ሰኔ 2ኛው እሁድም ይሁንን ጠቋሚው ሀገር አቀፉ የንባብ ቀን አለምገና ፈለገ ብርሃን ቤተመጽሓፍት ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ በንባባዊ መርሃ ግብራት ተከብሮ ይውላል።

የ2014ዓም ሙሉ ዓመት መሪ ቃላችን "አንባቢ ትውልድ ለሀገር ግንባታ"

ሰኔ 12/2014 ዓም እሁድ 6ኛ ዓመት አለምገና ሰማይ ስር በአቶ ጌቱ በቀለ መኖሪያ ቤት ንባብ ዝክሯ ነው።

ተጋብዘዋል።

ማንባብ አለማወቅን ይገልጻል።
ከማማረር ማምረር።
በድንቁርና ላይ እናምጽ!
39 viewsጌቱ በቀለ, 06:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-15 04:58:01 ታላቅና እጅግ ውዱ የከተማ ወሬ


ሀገር አቀፉ የንባብ ቀን 5 ቀናት ቀሩት

ለቁርቁስ የሰነፈ ህዝበ-ሀገርትነ-ኢትዮጵያን ለማዋለድ ንባብን የተወዳጅ ትውልድ ያስፈልገናልን ምክረ ሀሳበ-ምሰሶው ያደረገው ብሄራዊው የኢትዮጵያውያን የንባብ ቀን በየዓመቱ ሰኔ 2ኛው እሁድ ይሁንን ጠያቂው የ6ኛው ዓመት ክብረ-ንባበ-ዝክር በመኖሪያ ቤት ደረጃ አለምገና በፈለገ ብርሃን ቤተመጽሃፍት በበዙ ንባባዊ ክንውናት ይዘከራል።

የዘንድሮው የ6ኛው ዓመት የ2014 ዓም ሙሉ ዓመት መሪ ቃላችን "አንባቢ ትውልድ ለሀገር ግንባታ" በሚል ሀሳብ ዓመቱን ሙሉ በየወሩ የወሩ የመጀመሪያውን እሁድ ፤የየወሩን ራዊ ቃሎች እያወጀ ለሰኔ ሁለተኛው እሁድ መዳረሻ በከፍ ባሉ ንባባዊ አጀንዳዎች በፈለገብርሃን ቤተመጽሓፍታችን ሲከበር ግዜውን በቁምነገራም በተግባራዊ ሁነታት አስውቦ አሳልፏል።

ከማማረር ማምረር።
በድንቁርና ላይ እናምጽ።
ከማማረር ማምረር።
0911878798
ጌቱ በቀለ/መራታ አባቡራ
39 viewsጌቱ በቀለ, 01:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ