Get Mystery Box with random crypto!

ISLAM IS UNIVERSITY

የቴሌግራም ቻናል አርማ islamisuniverstiy_public_group — ISLAM IS UNIVERSITY I
የቴሌግራም ቻናል አርማ islamisuniverstiy_public_group — ISLAM IS UNIVERSITY
የሰርጥ አድራሻ: @islamisuniverstiy_public_group
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.00K
የሰርጥ መግለጫ

⭐️ሰው የሚገነዘብ አእምሮና የሚያፈቅር ልቦና ባለቤት ነው።እነዚህ ሁለቱ ካልተመጣጠኑ ስብእናው አደጋ ውስጥ ነው።የሚያገናዝበው አዕምሮው፣የሚያፈቅረው ልቡ፣የሚንቀሳቀሰው አካሉናወደ ሰማይ የሚወነጨፈው መንፈሱ በውህደት ካልተንቀሳቀሱ ሰውየው ላይ ችግር አለ ማለት ነው
📨የፍቅር እና የጥላቻ ስሜቱ፣የፍላጎት እናየፍርሃት መንፈሱ በአዕምሮ ብስለት ካልተገራ አስቸጋሪ ነው
አስተያየት👇
T.me/Aisuu_bot

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 31

2022-08-30 21:06:52 የአቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረድየሏሁ ዐንሁ) ታሪክ

                ክፍል ስምንት

   ከርሱ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የሌለ በሆነው አላህ
ምዬ መናገር እችላለሁ፡፡ በዚህ ዓለም ውስጥ ከነቢያት በስተቀር እንደ አቡበክር ያለ ታላቅ ሰው እስከ አሁን ድረስ አልተፈጠረም።

    ብዙ ሙስሊም ወጣቶች ታላላቅ አድርገን የምንቆጥራቸው
ምን አይነት ሰዎችን ነው? እስኪ የአቡበክርን ታሪክ ለመመርመር ጥረት እናድርግ፡፡ ከተራራ የገዘፈ ታላቅነት ጎልቶ ይታየናል። የአስ-ሲዲቅን ሕይወት እንመርምር፡፡

           እስክጠግብ ድረስ እርሳቸው ጠጡ!

      አቡበክር አስ-ሲዲቅ ከነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ጋር ረዘም ላለ ጊዜ በዋሻው ተሸሽገው ቆዩ፡፡ ሁለቱንም ረሃብና ጥማት ያሰቃያቸው ጀመር፡፡ አንድ እረኛ ከዋሻው ወዲያ ማዶ ሲያልፍ ተመለከቱ፡፡ ጥቂት ወተት ካለው ይሰጣቸው ዘንድ ለመጠየቅ አቡበክር ወጣ አሉ፡፡ መጠነኛ ወተት ከእረኛው አገኙ፡፡ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲጠጡ አደረጉ፡፡ አቡበክር ይህን ሁኔታ በተመስጦ ሲተርኩ እንዲህ ይላሉ፦

  “ወተቱን እኔ እስክረካና እስክጠግብ ድረስ እርሳቸው ጠጡ፡፡” እንዴት ያለው ፍቅር ነው! የነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) እርካታ የርሳቸው እርካታ ሆነ፡፡ የነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) መጥገብ ለርሳቸውም ጥጋብ ሆነ፡፡ እንዲህ ያለ ፍቅር ታይቶም አይታወቅም! ከዚህ በኋላ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ)ና ወዳጃቸው ጉዙዋቸውን ወደ መዲና አቀኑ፡፡ አቡበክር በአካባቢው ታዋቂ ነጋዴ ስለነበሩ በየመንገዱ ያገኙዋቸው ሰዎች ሰላምታ
ያቀርቡላቸዋል።

    ስለ ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ማንነትም ይጠይቋቸው ነበር። አንዱን ሰላም ሲሉት ይህ ሰው ማነው አቡበክር በማለት ይጠይቃቸዋል ይህ መንገድ የሚመራኝ ሰው ነው በማለት ይመልሳሉ። ጠያቂው ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ለአቡበክር መንገድ የሚመሩት ሰው እንደሆነ እንዲገምት አድርገዋል። በእርግጥ አቡበክርን የሐቅ የእውነትና የጀነት መንገድ ይመሯቸው የነበሩት ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ናቸው። ዑመር ቢን አል-ኸጣብ የአቡበክር መዓዛ እንደሚስክ ሽቶ ያውዳል ይሉ ነበር፡፡

                     እኔ ተራ ሰው ነኝ
           እርሶ ግን የዚህ ዲን ዓርማ ነዎት!

አቡበክር ከረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ጋር ወደ መዲና አብረው በመጓዝ ላይ
እያሉ አንዴ ወደፊት አንዴ ደግሞ ወደኋላ ቆይተው ደግሞ ከግራና
ከቀኝ እየሆኑ ያጅቧቸዋል፡፡ በዚህ ጊዜ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) “ምን ሆነህ ነውአቡበክር” ይሏቸዋል። አቡበክርም “መጠበቅ እንዳለብኝ ሳስታውስ ከፊት እሆናለሁ። ከዛም የሚያሳድዱዎትን ሳስታውስ ከኋላ እሆናለሁ ከዚያም በግራዎ በኩል አንድ ነገር እንዳይጎዳዎ እልና በግራዎ እሆናልሁ፡፡" በቀኝ በኩልም ምንም ነገር እንዳያገኝዎ እሰጋና በስተቀኝ እሆናሉ፡፡ ‹‹አቡበክር ይህን ያህል ትወደኛለህ እንዴ?›› ይላሉ፡፡ ‹‹እጀግ በጣም ነው እንጂ ረሱልም (ሰ.ዐ.ወ) ‹‹በእኔ ቦታ ሆነህ ለመሞት ትፈልጋለህ ማለት ነው?›› ብለው ይጠይቃሉ ‹‹አዎና እኔ ብሞት እኮ ተራ ሰው ነኝ፡፡ እርሶ ግን የማይገኙ የዚህ ዲን አርማ ነዎት፡፡››

            አምሳያ የሌለው ሥነ-ምግባር

   አቡበክር አስ-ሲዲቅ ከላይ በተጠቀሰው መልኩ እያደረጉ መዲና
እስኪገቡ ድረስ አብረዋቸው ተጓዙ፡፡ ወደ መዲና ሲቃረቡ የመዲና ሰዎች (አንሷሮች) እየጠበቋቸው ነበር፡፡ ረሱልን (ሰ.ዐ.ወ) በመልክ ለይተው አያውቋቸውም። አቡበክር ለጥበቃ ከፊት ከፊት ይጓዙ ስለ ነበር አንሷሮች ሁሉ እርሳቸው መስለዋቸው ነበርና የተጫነበትን ግመል ይዘውላቸው ወደፊት ይመሩ ጀመር፡፡ ይሄን ጊዜ አቡበክር ሁኔታው ይገባቸውና ኩታቸውን ያወልቁና ጥላ ይሆናቸው ዘንድ ረሱልን (ሰ.ዐ.ወ) ይከልሉበታል፡፡ አንሳሮችም ወዲያው ነገሩ ይገባቸውና የረሱልን (ሰ.ዐ.ወ) ግመል መሳብ ይጀምራሉ።

              የውመል ፉርቃን

       ጊዜው ሄዶ ሙስሊሞች መዲና ላይ መሠብሰብ ጀመሩ። ታላቁ የበድር ጦርነት ተከሰተ፡፡ የአስ-ሲዲቅ ልጅ ዐብዱረህማን በወቅቱ ገና አልሰለመም ነበር፡፡ በውጊያው ዕለት ሰይፉን ከአፎቱ መዘዘና "ማነውየሚገጥመኝ?›› ብሎ ፎከረ፡፡ አቡበክር(ረ.ዐ) ተነሱና ««የአላህ መልዕክተኛ ሆይ እኔ እገጥመዋለሁ›› አሉ፡፡ ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) "ተወው እኔ እበቃዋለሁ" ብለው ተነሱ፡፡ ዐብዱረህማን ቢን አቡበክር ከሰለሙ በኋላ ለአባታቸው እንዲህ አሏቸው “ያኔ ካንተ ጋር ላለመግጠም ብዬ እየተደበቅሁ ነበር፡፡
አቡበክርም(ረ.ዐ) ‹‹ወላሂ ያኔ ባገኝህ ኖሮ አልምርህም ነበር›› አሉት፡፡

    አቡበክር ሰውነታቸው ለስላሳና ክብደታቸው ቀላል ቢሆንም
የቀልባቸው ጥንካሬ ግን ድንቅ ነበር፡፡ የአላህ (ሱ.ወ) ውሳኔ እርሳቸውን የመሰሉ ሰዎች በዓርአያነት ይከተሏቸው ዘንድ ገርና ለስላሳ ሆነው ተፈጠሩ፡፡ ህይወታቸውና ገንዘባቸው የአላህ (ሱ.ወ) ዲን የበላይ ይሆንዘንድ የማያወላውሉ ሰዎች አስ-ሲዲቅን በዓርአያነት መከተል ይኖርባቸዋል፡፡ እርሳቸውን ሞዴል ማድርግ አለባቸው፡፡

    የበድርን ውጊያ አቡበክር ጀብድ በተሞላበት ሁኔታ ነው ያሳለፉት፡፡ በወቅቱ ሶሃባዎች ከከህዲያኖች ይከላከልላቸው ዘንድ ለነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ዙፋን ሠርተውላቸው ነበር፡፡ ይህን ሠርተው ካበቁ በኋላ ከረሱል (ስ.ዐ.ወ) ጎን ሆኖ የሚከላከል ሰው ይመርጡ ጀመር፡፡ በወቅቱ የነበረውን ሁኔታ ዓልይ ቢን አቡጣሊብ(ረ.ዐ) ሲተርኩ እንዲህ ይላሉ ‹‹ይህንኑ ኃላፊነት ለመውጣት ሁላችንም አፈግፍገን ነበር፡፡ አቡበክር ሰይፋቸውን መዘው መጡና ‹‹የረሱልን ዙፋን እኔ እየጠበቅኩ እከላከላለሁ አሉ፡፡ እስከመጨረሻው የውጊያ ሰዓት ድረስም ከረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ሳይለዩ በተከላካይነት ቆዩ፡፡››

   አቡበክር የነበራቸው ወኔ እጅግ ከፍተኛና እንግዳ ነበር፡፡ ለጀነት
በተለይ ደግሞ ለከፍተኛው የፊርደውስ ጀነት የነበራቸው ጉጉት
አስገራሚ ነው፡፡ ይህንን ክስተት እስኪ እናስተውል።

   አንድ ቀን ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ሶሃቦቻቸውን (የዕምነት ጓዶቻቸውን)
ሰብስበው ስለጀነት ሰዎች ሁኔታ ይነግሯቸው ነበር፡፡ ‹‹ጀነት ውስጥ የተለያዩ የማዕረግ በሮች አሉ፡፡ እንደየሥራው በየበሩ የሚጠራ ሰው አለ፡፡ የሰላት ሰው በሰላት በር፤ የጾመ ሰው ረያን በሚባል በር፤ ሙጃሂድ ሆነ የሞተ ሰው የጂሀድ በር በሚባለው በኩል፤ የሶደቃ ሰው የነበረ በሶደቃ በር፣ በሚባለው በኩል እንደየሥራው እየተጠራ ይገባል›› ብለው ነገሯቸው፡፡

የጀነት ጉጉታቸው ወደር ያልነበረው አቡበክር እንዲህ በማለት ጠየቁ... ‹‹አንቱ የአላህ መልዕክተኛ በሁሉም በር እየተጠሩ መግባት የሚቻልበት ሁኔታ አለን?›› ነብዩም (ሰ.ዐ.ወ) «እንዴታ አቡበክር አንተ ከእንዲህ ዓይነት ሰዎች እንድትሆን እመኛለሁ፡፡» አሏቸው።

                  ሁለገብ ማንነት

  በአንድ ወቅት ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ሙስሊሞችን የፈጅር ሶላት ካሰገዷቸው በኋላ ወደ እነርሱ ተቀጣጭተው ተቀመጡና እንደሚከተለው ጥያቂያዎችን አቅረቡ፡፡ «ከናንተ ውስጥ ማነው ለዛሬ ጾምን ነይቶ ያደረው፡፡ ሁሉም ዝም ሲሉ ሰይድ ዑመር(ረ.ዐ) «አንቱ የአላህ መልእክተኛ! እኔ ለመጾም ነይቼ አላደርኩም›› አቡበክር(ረ.ዐ) ቀበል አደረጉና «እኔ ጾምን ነይቼ ነው ያደርኩት» አሉ፡፡ ረሱልም (ሰ.ዐ.ወ) ጥያቄዎችን እያከታተሉጠየቁ «ከእናንተ ውስጥ ታማሚን የጠየቀ ማነው?» «አንቱ የአላህ መልዕክተኛ እኛ በቀጥታ የመጣነው ፈጅር ለመስገድ ነው በዚህ ሰዓት እንዴት የታመመን ልንጠይቅ እንችላለን፡፡» በማለት ሰይድ ዑመር....
http://t.me//@arebgendamesjid
1.4K views18:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 10:27:05 የመራም ማስታወሻ የሚለዉ ታሪክ አልቋል

አስተያየት አልቀበልም ....ከትንሽ ቀን ቡሀላ የሆድ ዉስጥ ፉም እሳት የሚለዉን በ45 Part የቀረበዉን ለዩቲዩበሮች እና ለሌሎቻ ቻናሎች እንዲመች በመሀል የገቡ አባባሎች ሀዲሶች ተቀንሶ ወደ 25 part size አንሶ አቀርባለሁ...

መልካም ቆይታ

አሚር ሰይድ
2.0K views07:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 10:26:44 ግን ወንዶች ሆይ ለሴት ብቻ ማስጠንቀቂያ ሆነ አይደል እስኪ ለእናንተም አንድ የእንስሳ ተፈጥሮን እንድታስተዉሉ ላስታዉሳችሁ ሴት ዉሻ..
ሴት ዉሻ ወንድ ጋር ስትሆን ምን እንደሚያደርጋት አይታችሁ ታቃላችሁ??
እኔ በተደጋጋሚ አይቻለሁ አይታወቅም እናንተ ያላያችሁት ዉሻ እኛ ሰፈር ስለሚበዛም ይሆናል፡፡
አንድ ሴት ዉሻ ያነገር ሲያስፈልጋት አራት አምስት ወንድ ዉሾች እሷ ጋር እንትን ለማድረግ በጣም ይጣላሉ ይነካከሳሉ ከዛ ያሸነፈዉ ዉሻ ሁሉንም ያባርና ወደ ሴቷ ሲሄድ እሷ እምቢ ትለዉና ስትሄድ ሲከተል ጊዜዉን ፈጅቶ እዳዉን አሳይታ የፈለገዉን ሲያገኝ ..ከዛ ትቆልፍበታለች ..እኔ የሚያለቅስ ዉሻ ብዙ አይቻለሁ በቃ ተሰቃይቶ ተሰቃይቶ እሷ በሂደችበት እሩጦ እሩጦ የቀለፈችበትን ስትለቀዉ ልብ እርግት የሚል ነዉ የሚመስለኝ ...ግን የሚገርመኝ አምስት ዉሾችን አሸንፎ እንደገና እሷን በግድ ሳያገኝ እዛ ነገር ላይ ሳይረካ ዉሻዉ ማልቀሱ ያሳዝነኛል፡፡
ግን በሰዉ ሴት በዛ እንጂ ወንድ ቢበዛ ኑሮ ምን ይኮን ነበር???
እናም ወንድሜ ሆይ ለአንድ ሴት የሚዉጀበጀብ የሚያሳፈስፍ ሰዉ ከበዛ ተወት አድርግ ለምን እንደነዛ ዉሻ ተናክሶ ተናክሶ አንዱ ሀራም ላይ የወደቀባት አይጠፋምና .......እናም አደቧን የጠበቀች በዲነል ኢስላም ያደገች ..የጨዋ ቤተሰብ ልጅ ከሆነች ዉሻ አይቀርባትም ለምን ሀራም ፈልጋ ተቀባብታ የቱርክ ልብስ ለብሳ የተወጣጠረ ሂጃብ ለብሳ...ፋሽን ልብስ እየመረጠች የገዛችዉን ለብሳ አትሄድማ ..የሷ አለባበስ ጅልባብ ኒቃብ አንገቷን ደፊ ብዙ የሴት ጓደኛ የሌላት ከሆነች በትርፍ ጊዜዋ ቂርአት ጋር የምታሳልፍ ከሆነ ..ቤተሰቦቿን በስራ የምታግዝ ከሆነች ..ወዳጄ እሷ ጋር ክብር አለ ፣እሷ ጋር ሀያእ አለ፣ እሷ ጋር መዉደድ አለ ፣እሷ ጋር ቀይ የደም ሴል አለ ከሌለም ከቶበተች ችግር የለም እንዳታሳልፍ ...እሷ ጋር ነገ ለምወልደዉ ልጅ ዋስትና መሆን የምችል በተርብያ የማሳደጉ ብቃት አለ፣ እሷ ጋር ለስራ ምክንያት አገር ጥለህ ብትሄድ አማናህን ልጆችህን ንብረትህን የምጠብቅ ብቃት አለ ..እሷ ጋር ቆንጆ ያገባና በሬ ያረደ ብቻዉን አይበላም የሚባለዉ የጃሂል ተረት አይሰራም ..እሷ ነች የትዳር አጋር ምርጫ ማድረግ ያለብህ...
ለምን የዋሁ ትዳር ለማግባት በሚዲያዉ በስልክህ ባለ ፎቶ በምትመርጠዉ ሴት ብዛት የተወዛገብክ የቱን ላድርግ ብለህ ዉዝግብግብ ያልከዉ አንዷን ላግባ ብለህ ወስነህ ዘወር ስትል ከእሷ የተሻለ ሶስት አራቱን ስታይ ሀሳብ ለምቀይር ወዳጄ ሆይ!! እወቅ የአላህን ትዕዛዝ የማታከብር ሴት መቼም ቢሆን የኔን ትዕዛዝ ትቀበላለች ታከብራለች ብለህ አትሰብ!!!!!
አለባበሳ አነጋገሯ አካሄዷ አኗኗራ ከአላህ ትዕዛዝ ዉጭ ከሆነ የፈጠራትን ጌታ ትዕዛዝ ካላከበረች የአንተ አባወራዉን ትዕዛዝ ልታከብር አትችልም.. አደራህን ተጣላሁ እንዲህ ሆነች እያልክ እንደ ባቄላ ንፍሮ እንዳትነፋረቅ ..ወይም ሸይጧኑ አሟሙቆት በጥፊ በካልቾ ብለህ ተከሰህ በሴት መብት ወህኒ ቤት እንዳገባ ..ሸሪአ ፍርድ ቤት አፋቱኝ እያልክ ቡሀላ ጊዜ እንዳትፈጅ አሁን ባለህ ጠባብ ሰአት ጊዜህን ተጠቀምበት !!! ፈጦ የተቀመጠ አይንህን ግለጠዉና አእምሮህ ጋር አቆራኝተህ ዲነኛዋን ጀሊሉ የሰጣትን ዉበት ብቻ የያዘችዉን እንስት ነገ የማለድምበትን በእጅህ አድርግ!!!
ከስድብ ክፉ አቅሙን የማያቅ ነዉ!!!! እናም ሸርጥ መስፈርት ሳታበዛ በአቅምህ በአንተ አቅም የምትኖረዉን ሀዋህን በጊዜ በእጅህ አድርገህ የሙስሊም ኡማዉን ቁጥር አብዛዉ፡፡

ግን ሁላችንም ማወቅ መገንዘብ ያለብን ጊዜያዊ ደስታችን እና የእለት ከእለት ኑሯችን የቀበሮ ፈንጠዝያ እንዳይሆን መጠንቀቅ አለብን ...ቀበሮ አድኖ ከገደለ ቡሀላ ደስታዉ ወሰን የለዉም...የገደለዉን አስቀምጦ በደስታ እየሮጠ በጩሀት ያቀልጠዋል በደስታ ብዙ ስለሚጓዝ ተመልሶ ያደነዉን ሲፈልግ ያጠዉና በእጅጉ ያዝናል፡፡ እናም በሰዉ ልጅ የህይወት ዉጣ ዉረድ ለደስታም ለሀዘንም ልክ ይኑረን በመሶበር የማይገኝ ነገር የለምና፡፡

ማስታወሻየ እዚህ ላይ ጨርሻለሁ ምን ይታወቃል ወልጄ በተማርኩት ተመርቄ አስተማሪ የሕይወት ዉጣ ዉረድ ለወደፊት ካሳለፍኩ በማስታወሻየ ፅፌ ጀባ እላችሆለሁ ለዛሬ በዚሁ ፡፡
ማስታወሻየን ዘጋሁ ...

ተ..............ፈ.............ፀ................መ


@Islam_and_Science
1.9K views07:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 10:26:33 #የመራም_ማስታወሻ
        ክፍል ~➊➑ የመጨረሻዉ ክፍል
ፀሀፊ ☞አሚር ሰይድ


አንድ ቀን አብዲ የ12 ክፍል ያመጣሁትን ዉጤት ካርድ ይመለከተዋል
..... እህት ወንድሞችሽን ለማስተማር ብለሽ ያቋረጥሽዉን ትምህርት በዲግሪ መማር አለብሽ ብሎ በግል ኮሌጅ በኔዉ ምርጫ Acounting ተመዝግቤ እየተማርኩ ነዉ.....በቅርቡ ደግሞ የልጅ እናት መሆኔ ነዉ ነፈሰ ጡር ነኝ ..
የታገሰ መጨረሻዉ እንዴት አማረ!!! በህይወት ዘመናት የሚፈራረቁ ደስታና ሀዘን የህይወት ሁለት ገፅታዎች ናቸዉ ...ሁሌም ቢሆን ሀዘን በደስታ ሲተካ ደስታም በሀዘን ይቀየራል ሂወት እንደዚህ ነች ፡፡

አላህ ከታጋሽ እና ከአመስጋኝ ብራያዎቹ ያድርገን.....
ስኬት አጋጣሚ አይደለም ..ስኬት የአመለካከት ዉጤት ነዉ ..አመለካከት ደግሞ ምርጫ ነዉ፡፡ ስለዚህ ስኬት የምርጫ ጉዳይ እንጂ የዕድል ጉዳይ አይደለም...ስኬት በህወይወት ዉስጥ በደረስንበት ከፍታ ያህል አይለካም፡፡ ይልቅስ ስንወድቅ ምን ያህል ጊዜ ወድቀን ተነስተናል??በሚለዉ መልስ ያዘለ ጥያቄ ነዉ ስኬት የሚለካዉ ...ወድቆ የመነሳት ችሎታ ነዉ የኛን ስኬት የሚወስነዉ....

አንዳንድ ሰዎች እንዲህ ይላሉ፡-"" እንዲሳካልህ የምፈልግ ከሆነ የዉድቀትህን ቁጥር እጥፍ አድርገዉ ..ሽንፈት የስኬት ረጅም ጎዳና ነዉ ብለዋል፡፡""
የስኬት ብቸኛዉ መለኪያ የሆነ ነገር መስራት ብቻ ከሆነ ..መዉደቅ የሚገፋን ወደ ፊት ይሆናል ማለት ነዉ፡፡
ስኬትን ለማግኘት ብለዉ ብዙ ሴቶች ስኬት እየመሰላቸዉ ብዙ መጥፎ ሀራም ነገር ይሰራሉ ..በጭራሽ ይሄ የስኬት መንገድ ሊሆን አይችልም፡፡ ሴትነት በርካሽ መንገድ የሚረከስበት በሀራም መንገድ የሚሸቀልበት በአላማ በለለዉ ወንድ አላማዋን የምትስትበት አይደለም!!" ሴትነት ማለት በእሾህ የተከበበ እስር ቤት ነዉ..ማምለጥ የማይቻል ለመኖር ደግሞ አንዱ እሾህ ሲወጋ እየነቀሉ እያስታመሙ የሚኖርበት የስቃይ የፈተና ፆታ ነዉ ..ይሄን እስር ቤት በጣጥሰሸ ለመዉጣት መታገስ መሶበር በማስተዋል መራመድ እንጂ ያገኘሽዉ ጋር እነፍሳለሁ ካልሽ ...ያዉ ገለባ ንፋሽ ሁነሽ ትቀሪያለሽ ፡፡

እንደ እኔ ከችግር ጋር ከመከራ ጋር ማደግ ችግር እንዳይፈታ ያደረገ ስብዕና አልብሶ ያጠነክራል፡፡
አንድ ሰዉ በሆነ ነገር ከአንተ የተሻለ ከሆነ ምክንያቱ ሊሆን የሚችለዉ ከአንተ የበለጠ ብዙ ጊዜ የወደቀ እና ተስፋ ሳይቆርጥ ለሽንፈት ቦታ ሳይሰጥ ግቡ ላይ ደርሷል ማለት ነዉ፡፡ አንድ ሰዉ ከአንተ የባሰ ከሆነ ደግሞ ምክንያቱ አንተ ባለፍክበት የሚያሰቃይ የመማር ልምምድ ዉስጥ አላለፈም ማለት ነዉ፡፡
የዱንያ ኑሮ ሲኖር መኖራችን ካልቀረ ችግር የህይወት ጅራቱን ይዞ ወደሆላ ገትቶ የድህነት ጉረኖ ሊደፍቀን አይገባም እኛም ልንፈቅድለት መፍቀድ የለብንም ፡፡
እኔ ሳድግ በቤተሰብ ግጭት አእምሮ ተጨናንቆ ነበር
ከዛም እናቴ ስትሞት ያወረሰችኝ ጥንካሬን ተስፋ አለመቁረጥ ቅንነት እና የወንድም እህቴን ሀላፊነት ብቻ ነበር ከእናቴ መዉረስ የቻልኩት...ነገር ግን ተስፋ የቆረጠ ያገጠጠ የታረዘ የደከመ እኔነቴና ሰዉነቴ በጭራሽ እንዲታይ አላደረኩም እንደዉም የእህትና የወንድሞቼን አደራ ስለተቀበልኩ ብርታቱን ሰጠኝ
የጥንካሬ መለኪያ ሚዛን መሆን ያለበት ፊት ለፊት የገጠመን የህይወት ጥያቄ በአሸናፊነት መወጣት እንጂ ምክንያት በመደርደር በመሸሽና ተስፋ በመቁረጥ ለዚች ለማትረባ ዱንያ እጅ አልሰጥም ብየ በአላህ እገዛ ብዙዉን ያሳካሁ ይመስለኛል

ትናንት የነበረዉ ዛሬ የለም ..ዛሬ ያለዉ ችግሬ ጠንካራ ከሆንኩ ነገ የለም..ለመጣዉ ችግር ሁሉ በአላህ ተስፋ አርጎ አላህን ይዤ አልቸገርም አላህን ከያዝኩ ብቻ መሸሻ መንገድ እንዳለዉ ሁሌም እርግጠኛ ነኝ፡፡

ዉድ የተከበርሽዉ እህቴ ግን ክብርሽን ደረጃሽን እወቂዉ ሴትነት መልክሽን የሰዉነት ቅርፅሽን ችግር ያላየ የሚያምር እጅና እግርሽን ጠዋት ማታ በማጠብ በመዋዋብ ከቤት ስትወጪ የወንድ የሙገሳ ምላስ እና የመንገድ ላይ ፉጨት ፊሽካ ተጠባባቂ አትሁኝ ..ወይም በመኪና መንገድ በገበያ በሚዲያ ዉበትሽን የኔ ነዉ ብለሽ ስትበትኝም ዋዉ አምሮብሻል ስትባይ አመሰግናለሁ ..አይደል አልቀረብህም እያልሽ የወንድ የጫፍ ምላስ ኮመንት አንባቢ የአንቺ ዉበት መገለጫ ሲሆን ሊያሽሞነሙነሽ ልብሽ ጩቤ እንዲረግጥ መቼም አትፍቀጅለት ፡፡የሴት ልጅ ዉበት አላማዉን በረሳ ስራ በሌለዉ ወንድ የሚገለፅ አይደለምና...የአንቺን ዉበት የምወስኚዉ እራስሽ ነሽ አላማሽ የወንድ አድናቆት ከሆነ ኢነማል አእማሉ በኒያ ገና ከቤት ስትወጭ ጀምሮ ፊሽካ ይጀምርሻል በግ ሙቶ ተኩላ ቢያለቅስ ወይም አህያ ሙቶ ጅብ ለቅሶ ቢደርስ ጥቅም የለዉም ሲያደንቅ ፊሽካዉ ሁሉ አንድ ቀን መዘዝ ይዞብሽ ይመጣል፡፡ አባቶቻችን እንዲህ ይላሉ """አህያ ቢሰባ ምኑ ረባ ይቆያል እንጂ አህያ የጅብ ናት""" ተብሏል፡፡ እዉነት ነዉ...አህያ ቢሰባ ቢወፍር ቢያምር የኛ ማህበረሰብ መቼም ቢሆን ለምግብነት አይጠቀመዉም ..ጊዜ ይፈጃል ይቆያል አህያ ከልጅነት ጀምሮ እስከ እለተ ሞቱ ሲያገለግል ሲሸከም ሲገረፍ ይኖራል ከዛም ሲያረጅ ወይ ሲሞት አህያዋን የሚበላዉ ጅብ ነዉ ..እንደዉም አህያ ሲያረጅ ወደ ጫካ ማታ ተወስዶ ይጣላል ለምን ጅቦች እንዲበሉት፡፡ እናም እህቴ አንቺ የተከበርሽ ፍጡር ነሽ ግን በዉበትሽ የምትተማመኝ ከሆነ እንደዚህ እንደ አህያ ማንም የሚወጣብሽ ማንም አምሮብሻል እያለ ቸብ የሚረግሽ ማንም እየመጣ የስሜት ማብረጃ እንዳያደርግሽ ነገ ጂብ የሚበላዉ የአህያ ህይወት ለመኖር አትወስኝ...አህያስ የተፈጠረዉ ለዚሁ አላማ ነዉ ግድ የለም ተሸከመም ተመታም አርጅቶም ጅብ በላዉ እንስሳ ነዉ ነገ የዉመል ቂያማ አፈር ይሆናል ግን አንቺ ነገ የዉመል ቂያማ ተቀስቅሰሽ ለምትጠየቂዉ ጥያቄ ምን ብለሽ እንደምትመልሽ አስበሽ ታቂያለሽ???

በዉበትሽ ተጠቅመሽ ጥሩ አማች ለቤተሰብ ለማምጣት ብር ያለዉ ባል ላይ ለመዉደቅ ብለሽ የምሰሪዉ የመዋዋብ ስራ የሚገጥምሽ ከዉበት መራጭ ሴት አሳዳጅ የሆነ ወንድ ጋር እንደሆነ አዘንጊ..ዉበት አንቺ እንዳሰብሽለት ነዉ በዉበትሽ አድናቂሽ ከበዛ ከአንቺ ችግር አለ ማለት ነዉ ነገ
ይሄ የሚጨራመት የሚያሸበሽብ ዉበት የአንቺ እድሜ ሲገፋ በዉበት ብሎ የገባዉ አባወራ ሌላ ቆንጆ ሴት መፈለጉ አይቀርምና፡፡ ይልቅ ዉበት ይረግፋል የማያምር እጅሽን ፃፊበት ተማሪበት ስሪበት በዉበት ማሰብ አቁመሽ በጭንቅላትሽ አስበሽ ለሌሎች መድረስ ቻይ...የሚያምር እግርሽን ተራመጅበት ሂጅበት ባይሆን ሀራም ቦታ ሳይሆን ቂርአት ለመቅራት ዲነል ኢስላምን ለመማር ተራመጂበት የዛን ጊዜ የሚመጣልሽ የወደፊት አጋርሽ ዉበት ተመልካች ሳይሆን የአንቺን ዲን ስብዕና ጥሩ አመለካከት አይቶ ጎጆ ይቀልሳል የዘላለም ደስታ ነዋሪ ትሆኛለሽ..ካልሆነስ በዉበትሽ ያገባሽ ወንድ 90% የሚያስበዉ አለ ቆንጆ ያገባና በሬ ያረደ ብቻዉን አይበላም የሚለዉን አባባል መቼም ከአእምሮዉ ስለማይፍቀዉ ዉበት ብቻ አይቶ ካገባሽ ቤት ሁነሽ አያምንሽ ..ቤተሰቦችሽ ጋር ብትሄጅ አያምንሽ ..እሱ ሌላ ቦታ ቢሄድ አያምንሽም ለምን ሲያገባሽ ያገኘብሽ ፊትሽን እጅሽን እግርሽን አለስልሰሽ ቀብተሽ እንጂ ልብሽን በኢማን አጠንክረሽ አይደለምና ከዛስ ከዛማ
ካልተማመኑ ፍች ነዋ..የዉበት ወጥመዱ ቆንጆ ያገባና በሬ ያረደ ብቻዉን አይበላም በሚለዉ ፍች ይሆናል
1.6K views07:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 21:08:48 አቂደቱል ዋሲጥያ
ሸይህ ዑመር አሊ
  ክፍል-13-
http://t.me//@arebgendamesjid
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ
ዘርፍ
1.7K views18:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 21:08:39    የአቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረድየሏሁ ዐንሁ) ታሪክ

  "ከአቡበክር በስተቀር ማንኛውንም ሰው ወደ እስልምና ስጋብዘው ያላመነታና ያላንገራገረ የለም።..." ረሱል ﷺ
   
                    ክፍል ስድስት

    ለዚህ ነበር በወቅቱ ወደ እስልምና ገብተው የነበሩ አዳዲስ ሰዎች ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ያደረጉትን ይህንን ጉዞ አምኖ ለመቀበል የተሳናቸዉ፡፡ የቁረይሽ ሙሽሪኮችና ባላባቶች ይህንኑ ዜና በሰሙ ጊዜ ረሱልን (ሰ.ዐ.ወ) ለማሳጣትና ለማዋረድ የማይገኝ እድል ያገኙ ስለመሰላቸው ጮቤ ረገጡ፡፡ ክፍተትን ለስህተት ለመጠቀም ያላቸው አቋም ይገርማል፡፡

    በነገሩ ለመሳለቅና ለማሾፍም ወደ አቡበከር (ረ.ዐ) ዘንድ ሄዱ፡፡
እንደደረሱም ለአል ሲዲቅ እንዲህ አሏቸው፡- "አቡበክር ሆይ! ጓደኛህ የሚዘላብደውን ሰምተሀልን?” ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) በኢስራእና ሚዕራጅ ስላደረጉት ጉዞ የተናገሩትን ነገሯቸው፡፡ አቡበከርም(ረ.ዐ) "በእርግጥ እንዲህ ብሏል? አሉ፡፡“አዎ! ብሏል፡፡” አሏቸው፡፡ አቡበከርም (ረ.ዐ) "በእዉነት ይህንን ብሎ ከሆነ እውነትን ተናግሯል።” አሉ፡፡

   ቁረይሾቹም "ይህንን አምነህ ትቀበላለህ?” ሲሉ ደግመው
ጠየቋቸው፡፡ “ከዚህ የበለጠ ነገር ቢናገሩም አምናቸዋለሁ፡፡” ሲሉ
መለሱ..." ወደ እርሳቸው እንሂድ አሉ። ወደ ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ዘንድ
እንደደረሱም ስለ ኢስራእና ሚዕራጅ የተከተለውን ሁሉ በዝርዝር
ነገሯቸው፡፡ አቡበከርም እንዲህ አሉ፡- "እውነት ተናግረዋል! እውነት
ተናግረዋል! እርሶ የአላህ መልክተኛ መሆንዎን እመሰክራለው፡፡”
ረሱልም (ሰ.ዐ.ወ) "አቡበከር ሆይ! አንተ እውነተኛ ነህ፡፡” አሏቸው፡፡

       ከማንም የተሻለ ጉርብትና

  የመካ ከሓዲያን በረሱል (ሰ.ዐ.ወ) እና በተከታዮቻቸው ላይ
የሚያደርሱት ስቃይና ግፍ በጣም እየበረታ ሲመጣ! ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ለአቡበከር ወደ ሐበሻ ይሰደዱ ዘንድ ፈቀዱላቸው፡፡ ከቁረይሽ ጎሳዎች ዉስጥ በጣም የተከበረ ሰው የነበረው ኢብኑ ዱግና ይህንን ይሰማና፤ የሚሻለው የርሱ ጎረቤት ሆነው መኖር ከቻሉ ማንም ሊነካቸዉ እንደማይችል ለአቡበክር ይመክራቸዋል፡፡

    ሰይድ አቡበክር በኢብን ዱግና ምክር ይስማማሉ፡፡ አቡበክር (ረ.ዐ) የዚህ ሰውዬ ጎረቤት ሆነው በመኖር ብዙ ጊዜ ቁርኣን እየቀሩ ያለቅሱ ነበር። እንዲህ ሲያደርጉ ሴቶችና ህፃናት ከበዋቸው ያዳምጡ ስለነበር በጣም ይማረኩና ተፅዕኖ ያድርባቸው ነበር፡፡

     ቁረይሾች በዚህ ሁኔታ ብዙም ስላልተደሰቱ፤ ከዚህ ተግባር
እንዲታቀቡ ይነግሯቸው ዘንድ ኢብን ዱግናን ይልኳቸዋል፡፡ ኢብን
ዱግናም በተላኩት መሰረት አቡበክር በቤታቸው ሆነው እንዲቀሩ
ይነግሯቸዋል። አቡበክርም በመንገድ የሚያልፉ ሰዎች እንዲሰሟቸው በሚል በቤታቸው መስኮት አቅጣጫ ሆነው መቅራት ይጀምራሉ፡፡

     የመካ ቁረይሾች ይኸኛው ሁኔታም ቢሆን ስላልተስማማቸው ጎረቤታቸው ወደሆኑት ሰው (ኢብን ዱግና) ስሞታ ያቀርባሉ፡፡ ኢብን ዱዓናም ቁርአኑን መቅራት እንዲያቆሙ ለአቡበክር ይነግሯቸዋል።
አቡበክር ግን ቁርኣን መቅረቱን ማቆሙ በጭራሽ እንደማይችሉ
ይነግሯቸውና እንዲህ ይላሉ፡- "ወላሂ ሰዎች ቁርኣን እንዲሰሙ
ማድረጌን አላቆምም፡፡ ከፈለክ ጉርብትናህ ይቅርብኝ፡፡ ካንተ የተሻለና የበለጠ ጎረቤት አግኝቻለሁ፡፡” (ቁርኣንን ማለታቸው ነው፡፡)

                    ለቅሶ
      አቡበክር አስ-ሲዲቅ ቁርኣን በሰሙ ቁጥር እንባቸውን
አይቆጣጠሩም ነበር፡፡ በጣም ስቅስቅ ብለው ያለቅሳሉ፡፡ በተለይ ሱረቱል ዘልዘላን በቀሩ ቁጥር ማልቀስ የዘውትር ልማዳቸው ነበር፡፡

     ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) በመሞቻቸው ዕለት ታመው ነበርና ሶላት
እንዲያሰግዱ አቡበክርን ያዟቸዋል፡፡ ይሄኔ እሜቴ ዓኢሻ (ረ.ዐ) እንዲህ ይላሉ፡- “አንቱ የአላህ መልእክተኛ! አቡበክር እኮ ለስላሳ ስው ነው። ቁርኣን ሲቀራ እምባውን መቆጣጠር ስለማይችል ሰፉዋን ምን እንደሚል መስማት አይችሉም፡፡ ስለዚህ ዑመርን ይዘዟቸው...”

    በአንድ ወቅት ከየመን የመጣ ልዑክ ወደ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ዘንድ
ይመጣና ለእስልምና ቃል ኪዳን (ሙባየዓ) ይገባል፡፡ ልዑኩ ቁርኣን
ኢስማም ያለቅሳል፡፡ ይሄኔ አቡበክር እንዲህ ይላሉ..“ቀልቦቻችን
ሳይደርቁ በፊት እኛም እንዲህ ነበርን፡፡” ወዲያዉም ማልቀስ ይጀምራሉ፡፡

       እስኪ የታላቁን አቡበክር (ረ.ዐ) ሁኔታ ከራሳችን ሁኔታ ጋር
እናነፃፅረው፡፡ ለመሆኑ እኛ አላህን ፈርተን፣ ቁርኣን ሰምተን
ያለቀስነበትን ጊዜ እናስታውሳለን? ለምን ይሆን ቀልባችን እንዲህ
የደረቀው? ለምንስ ይሆን ከዓይናችን እንባ የጠፋው? መጠያየቅ አለብን!

      ስባት ባህሮችን የፈጠረው ኃያሉ አላህ (ሱ.ወ) እርሱን በመፍራት የሚወርድ እንባን ከእኛ መመልከት ይወዳል፡፡ ነገር ግን የእኛ ዐይን ይህን ከማድረግ ሰስቷል፡፡

          በአላህ ቃል ኪዳን ላይ የነበራቸው ፍጹም እምነት

ፋርሶች ሮሞችን በጦርነት ባሸነፉ ጊዜ፤ አላህ(ሱ.ወ)
የሚከተሉትን የቁርኣን አንቀጾች አወረደ....

{ الۤمۤ (1) غُلِبَتِ ٱلرُّومُ (2) فِیۤ أَدۡنَى ٱلۡأَرۡضِ وَهُم مِّنۢ بَعۡدِ غَلَبِهِمۡ سَیَغۡلِبُونَ (3) فِی بِضۡعِ سِنِینَۗ لِلَّهِ ٱلۡأَمۡرُ مِن قَبۡلُ وَمِنۢ بَعۡدُۚ وَیَوۡمَىِٕذࣲ یَفۡرَحُ ٱلۡمُؤۡمِنُونَ (4) بِنَصۡرِ ٱللَّهِۚ یَنصُرُ مَن یَشَاۤءُۖ وَهُوَ ٱلۡعَزِیزُ ٱلرَّحِیمُ (5) }    الروم: ١-٥

አሊፍ ላም፣ ሚም፡፡ ሩም ተሸነፈች። በጣም ቅርብ በኾነችው ምድር፡፡ እነርሱም ከመሸነፋቸው በኋላ በእርግጥ ያሸንፋሉ። በጥቂት ዐመታት ዉስጥ (ያሽንፋሉ) ትእዛዙም በፊትም በኃላም የአላህ ነዉ። በዚያ ቀንም ምእመናን ይደሰታሉ፡፡ በአላህ እርዳታ (ይደሰታሉ) የሚሻውን ሰው ይረዳል እርሱም አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡ (አል-ሩም 1-5)

     እነዚህ አናቅጽ ከወረዱ በኋላ አቡበክር አስ-ሲዲቅ በቁረይሽ
ወደ ሙሽሪኮች መሰብሠቢያ እየሄዱ "ሮሞች እንደሚያሸንፏቸው አርግጠኛ ነኝ፡፡” ማለት ጀመሩ፡፡ አቡበክር እንዲህ እርግጠኛ የሆኑት ከላይ የተገለጸዉን የአላህ (ሱ.ወ) ቃል ኪዳን መሠረት አድርገው ነዉ። ኡመያ ኢብን ኸለፍ ይህንን ሲሰማ “እስኪ እዉነተኛ ከሆንክ እንወራረድ” አላቸው፡፡ አቡበክርም ተስማሙ። ኡመያም “መቼ ነው ድል የሚያደርጉት” ሲል አቡበክርን ጠየቃቸው፡፡ እርሳቸውም “ከሶስት ዓመታት በኋላ” አሉት።

   ▻▻ኢንሻአላህ ይቀጥላል◅◅
http://t.me//@arebgendamesjid

  
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ
1.6K views18:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 06:41:11 አካባቢ ኮንቲነር ተከራይቶ እቃ አሟልቶለት የቤት ሰራተኛ ልጆቹን የምትንከባከብለት ይዞለት እሱም እየሰራ ልጆቹን የሚያሳድግበትን የእርዚቁን ማገኛ አመቻቸለት....

አሁን የቀረን አዲስ አበባ መሄድ ነዉ
....ከአላህ ጋር እዚህ ያለዉን ነገሮች ቦታ ቦታቸዉን የያዙ መሰለኝ አለ አብዱ
...እኔም አዎ አብዲ አላህ ኸይር ጀዛህን ይክፈልህ ምንም የምለዉ ቃላት የለኝም አላህ እኔና ቤተሰቦችን አይቶ እንድደርስልን የላከህ ነዉ የመሰለኝ አልኩት
....እሱም አደራ እንደዉለታ ቆጠረሽ ከአሁን ቡሀላ እንዳታነሺብኝ ለአላህ ብየ ነዉ የሰራሁት ደግመሽ እንደዚህ አረክልኝ ብለሽ አንድ ቃል ለራሱ እንዳታነሺ አለኝ

አብዱ ጋር በራሱ መኪና አዲስ አበባ አብረን ሄድን....አዲስ አበባ በስም የኢትዮጲያ ዋና ከተማ ተብየ ስንማር እንጂ መጥቼም እመጣለሁ ብየ አስቤዉም በጭራሽ አላዉቅም ...እኔ ያሳለፍኩት የድህነትና የስቃይ ኑሮ ስለሆነ አዲስ አበባ እኖራለሁ የሚል በህልሜም ስቶኝ ታይቶኝም አያቅም ነበር..

ወሎ ሰፈር አካባቢ የተንጣለለዉ አፓርታማ ቤቱ ላይ መኖር ጀመርን ፡፡ አብዲ ጋር ያለን ፍቅር ይሄ ነዉ ለማለት ይከብዳል በጣም እንዋደዳለን ሳልሰስት ፍቅር እሰጠዋለሁ እሱም ይለግሰኛል...ፍቅር ማለት ከትዳር ቡሀላ ነዉ ከትዳር በፊት ፍቅር ከተጀመረ የትዳሩ ቀን ያበቃል ትዳር ከጀመሩ ቡሀላ ትዳር መሆኑ ቀርቶ እንደ ወንድም እህት ይሆናሉ በመሰለቻቸት የፍች ቀጠሮ የበዛባቸዉ ብዙ አሉና ..


አንድ ቀን አብዲ የ12 ክፍል ያመጣሁትን ዉጤት ካርድ ይመለከተዋል ...,ከዛም

#ክፍል ➊➑
ይቀጥላል......

Join
https://t.me/Islam_and_Science
2.0K views03:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 06:41:01 #የመራም_ማስታወሻ
           ክፍል ~ ➊➐
ፀሀፊ ☞አሚር ሰይድ


...ቤታችን አብሮኝ እንዲሄድ ብዙ ለመንኩት አሻፈረኝ አለ እሺ ልጆቹን ይዘህ ወዴት ነዉ የምትሄድ?? ስለዉ መሄጃዉን አያቀዉም ብቻ"እግሬ ወደመራኝ ቦታ እሄዳለሁ ቤቴን እንደሆነ ሚስቴ ሽጣ በመጠጥና በጫት ጨርሰዋለች"አለኝ

...ከልቤ አዘንኩ አባቢ ግድ የለም አብረን እንሂድ ከበላነዉ ትበላላቹህ፤ ከምንጠጣዉ ትጠጣላቹህ፤ ደስታቹህ ደስታየ ሀዘናቹህም ሀዘኔ ነዉ።
አንተ የወለድካቸዉ ልጆች ለኔ የሞተዉን ወንድሜን ማስታወሻ እና የሞተችዉ እናቴ ቅሪት ናቸዉ ..ወንድም እና እህቴችን መልሰህ አትንጠቀኝ !!!እናንተ አብራቹህን መኖር ከጀመራቹህ ቤታችን ይደምቃል የሰዉ መድሀኒቱ ሰዉ ነዉ ደሞ እነሪምን አስብ አልናፈቁህም እንዴ???.....አባቢ አብሮኝ ቤት እንዲሄድ በስንት መከራ አሳመንኩት ...ከተወሰነ ደቂቃ ቡሀላ አብደል ከሪም ከአዲስ አበባ በመኪናዉ የምሰራበት ቦታ ደረሰ ... አባቴን አገኘሁት አብደል ከሪም ብየ በደስታ አስተዋዉቄዉ አብረን ወደ ቤት ሄድን

ቤት እንደደረስን የቤቱን በር ስናኳኳ ሪም የአብዲን መምጣት በጉጉት እየጠበቀችኝ መሆኑ ያስታዉቃል ፊቷ በፈገግታ ተዉቦ በሩን ከፈተችልን።

....አባቢ ሪምን ሲያያት ደነገጠ ሪምም ያ ፈገግ ያለ ፊቷ ሆምጣጣ ሎሚ የመጠጠች ይመስል በአንዴ ኩስትርትር ብሎ ቲማቲም መሰለ ደነገጠች "አአአአ... "ምን ብላ ትጥራዉ ??አባቢ ሪምን ይዞ ልቅሶዉን ቀጠለ ጩኸቱን የሰሙ እማማየ በፍጥነት ወደኛ መጡ "ምንድን ነዉ? ምን ተፈጠረ..."አሉን አባቢን ሲያዩ እማማየም ..አልሀምዱሊላህ እንኳን ደህና መጣህ ያልሞተ ሰዉ ይገናኛል ብለዉ እቅፍ አደረጉት

..ከዘም አዩብ መጣ አባቢ በናፍቆት ሪምንና አዩብን አቅፎ የደስታ አይሉት የሀዘን ለቅሶ ያለቅሳል "እማማየ ኑ ወደዉስጥ ግቡ"ስትል ነበር ሪም" ጮክ ብላ ምን እንደተከየለባት አላዉቅም...አንተ ማን ነህ? "ብላ ከአባቢ እቅፍ ወጣች

ሪም አባቢ መሆኑን አላዉቅ ብላ ሳይሆን ይሄን ያህል ጊዜ ስለጨከነብን አባቴ ብሎ ለማለት ከብዷት ነበር ማን ነህ ያለችዉ.....
---->>>>> አባቢ ደነገጠ ምን ይበል "ሪሪሪሪሪ"ስሜን እንዳትጠራዉ ብላ ወደ ቤት እየሮጠች ገባች፡፡ እኔም ተከትያት ከገባሁ ቡላት እያለቀስኩ ሪምየ የኔ ዉድ አባታችን ነዉ አልመቸዉ ብሎ እንጂ በኛ ጨክኖብን አይደለም ያን ያህል ጊዜ ስንሰቃይ አይዟቹህ ያላለን አታይዉም ሰዉነቱን ያግርማ ሞገስ የነበረዉ አባታችን እንዴት እንደሆነ እና ተመችቶት ይመስልሻል ከኛ የራቀዉ??? ደሞ አባት ምንም ቢሆን አባት ነዉ፡፡ እዉጭ ያየሻቸዉ አንድ ወንድ እና ሴቷ ልጆች ወንድምና እህቶቻችን ናቸዉ፡፡ አባቴ ስም ያወጣላቸዉ ፈይሰል እና ለይላ ብሎ ነዉ... አየሽ እህቴ የቤተሰብ ፍቅሩ ልቡ ላይ አለ ግን አላህ ሁን ያለዉ ሁኗል ... በአላህ ሪምየ እኔ አዉፍ ብየዋለሁ አንችም አዉፍ በይዉ....... ብየ በስንት መከራ አሳምኘ ይቅር እንድትለዉ አደረኳት
ሪምና አባቢ አዉፍ ተበባሉ በጣም ደስ አለኝ አዩብም ያለ አባት ፍቅር አድጎ የአባቱን ፍቅር አሀዱ ብሎ እየጀመረ ነዉ .....አንዴ አባቢ ጋር አንዴ አብዱ ጋር
ታናሽ ወንድም እህቶቹ ጋር ሲጫወት ቤቱ የሌለ ፍቅር በፍቅር ሆነ

....በዛሬዋ ቀን አብዱንና አባቢን አገኘሁ ያ!የቀዘቀዘ ቤት በሳቅ ደመቀ ቤተሰባችን ከድሮዉ በጥፍ ጨመረ
.... ለአላህ! ክብር ምስጋና የተገባ ይሁን።
ምንም ነገር ቢሆን እንደነበረ የሚቀጥል የለም ሁሉም በጊዜ ዉስጥ ይቀየራል ያጣዉ ሲያገኝ ያገኘዉ ሲያጣ፤ ከተከፋዉ ሲደስት የተደሰተዉ ሲከፋ፤ የታመመዉ ሲድን የዳነዉ ሲታመም፤ ሂወት ስትመር አንዴ ስትጣፍጥ፤ መወለድ፤ መሞት፤ማግኘት፤ማጣት፤ማልቀስ፤መሳቅ.....በቃ ሂወት እንዲህ ናት ዝብርቅርቅ ብላ ለመግለፅ የማትመች!
አብዱም ግን መራም ልጆች እንደዚህ ሲንጫጩ ደስ አይልሽም? አለኝ
...አዎ በጣም ደስ ይለኛል
........ግን ምን እንደተመኘሁ ታቂያለሽ መራም?
.....ምንድን ነዉ??
...........የኮምቦልቻ ልጅ የነለይላ ቤተሰብ የሆነችዉን ልጅ ጋር በትዳር ተጣምሮ ደስታ የሆነ የትዳር ሂወት መስርቶ መኖር አለኝ
.....እኔም ኢንሻ አላህ ሁን ያለዉ ይሆናል አብዱ አልኩት


አሁን የምንኖርበት ቤት ጠባብ ስለሆነ አብዱ ሀሳብ አመጣ ...ኮምቦልቻ ላይ ቤት ተከራይቶ አባቴ ልጆቹን እንዲያሳድግ አዩብም አባቱ ጋር ከታናሽ ወንድም እህቶች ጋር አብሮ መኖር ጀመረ ...ሶስት ልጆች ነበርን አሁን አምስት ልጆች ሁነናል...የሞተዉ ፋይሰል እና እናቴ አሁን በተወለዱት ወንድምና እህቶች ማስታወሻ አገኘን ....
ሪም እነሱ ጋር እየሄደች መንከባከብ የሷ ስራ ሆነ

...ከተወሰነ ጊዜያት ቡሀላ እኔና አብዱ ለመጋባት ወስነን ደስ በሚል በኒካህ ፕሮግራም አድርገን አልሀምዱሊላህ አብረን የመኖር ጎጆ መሰረትን .. እንደአጋጣሚ ከአብዱ ጋር አላህ አገናኘን ለኔም ለቤተሰቦቼም ከአላህ ቀጥሎ የዱንያየ መከታ የችግሬ መፍቻ መፍትሄ ሆነን ቤታችን በድጋሚ አሸበረቀ
ግን ምን ይደረጋል የኔ ደስታ ሁሌ አትጨምር የተባለ ይመስል እኔና አብዲ ከተጋባን ከአንድ ሳምንት ቡሀላ ሁሉም ነፍስ ሞትን ቀማሽ ናትና እማማየ ሳይታመሙ ድንገት ሞቱብን አለቀስኩ ወደኩ ተነሳሁ... ነገር ግን በኛ ለቅሶ ከሞት የሚመለስ ሰዉ ቢኖሮ በተመለሰ ነበር
..እማማየን እንደናቴ ነበር የማያቸዉ ቤት ስገባ የሚቀመጡበትን ወንበር ሳይ ማልቀስ የሁል ጊዜም ስራየ ሆነ


ከአምስት ወር ቡሀላ አብዲም አዲስ አበባ ነዉ የምንኖረዉ ስላለኝ ወደ አዲስ አበባ ለመሄድ እየተዘጋጀን ነዉ..የሪም አብሮ አደግ የሰፈር ልጅ የሆነዉ ሀቢብ ሀራም ከመጀመሩ በሀላል ማሸብረቁ የተሻለ ስለሆነ መጥቶ ሀቢብ እህትሽን ዳሪኝ ብሎ ጠየቀኝ...ሀቢብ ሪምን ይወዳታል የእሱ ታናሽ ነች ከልጅነት ጀምሮ አሳድጓታል ግን ለመጥፎ ነገር መቼም ተመኝቷት አያቅም ..እናም ሪምን አማከርኳት
እሷም እኔ የእህቴን አምር አልጥስም ሀቢብም አብሮ አደጌ ነዉ ጥሩ ልጅ ነዉ መርሀባ ተቀብያለሁ አለችኝ

እኔም ሀቢብ ቀጥታ እህቴን ሳያወራት እኔዉ ለእሷ ብዙ ነገር አድርጌ ማሳደጌን ስለሚያቅ እኔን መጠየቁ አስደስቶኝ ሀቢቤ እስከ ዛሬ እኔ ከእናቴ ሀላፊነት ተቀብየ እዚህ ደረጃ አድርሻለሁ መቼም ታቃለህ ..ከዛሬ ጀምሮ እኔ ደግሞ እናቴን የሰጠችኝን ሀላፊነት ለአንተ ሰጥቸሀለሁ አደራ!!!! ሪምን እንደሚስት አርገህ ሳይሆን እንደ እህትህ እንደ እናትህ አድርገህ ተንከባክብልኝ...ሰዉ ነንና ስህተት አይጠፋም..ሪም ካጠፋች አደራ ሽማግሌ አስታራቂ እንዳትጠራ ለምን እኛ ዘመድ የለንም ሪም ሊከፋት ይችላልና ...አንተዉ ወንድም አባት ሁነህ በመመካከር ሀሳባችሁን የተፈጠረዉን ችግር በወያየት ተግባባታችሁ ኑሩ፡፡
በዚህ የማይፈታ ችግር ከገጠመህ ለሌላ ሰዉ ሳታወራ ቀጥታ ደዉለህ ለኔ ንገረኝ እንደዚህ የምልህ ሪም ታጠፋለች ብየ ሳይሆን ሸይጧን በመሀከላችሁ ከገባ ምን እንደሚፈጠር እርግጠኛ መሆን ስለማልችል ነዉ እንጂ እኔ በሪም ከራሴ በላይ እመሰክርላታለሁ
ስለዉ ሀቢብም በደስታ መርሀባ ቃል እገባለሁ መራም ብሎኝ ሪምም ከሀቢብ ጋር አብሮ የመኖር ዋስትና የሆነዉን ኒካህ አሰሩ..አልሀምዱሊላህ

ለአባቴና ለታናሽ ወንድም እህቶቼ ደግሞ አብዱ አላህ ኸይር ስራዉን ይጨምርለት ኮምቦልቻ በርበሬ ወንዝ ሰፈር ቤት ገዝቶ መናሀሪያ
1.7K views03:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ