Get Mystery Box with random crypto!

ISLAM IS UNIVERSITY

የቴሌግራም ቻናል አርማ islamisuniverstiy_public_group — ISLAM IS UNIVERSITY I
የቴሌግራም ቻናል አርማ islamisuniverstiy_public_group — ISLAM IS UNIVERSITY
የሰርጥ አድራሻ: @islamisuniverstiy_public_group
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.00K
የሰርጥ መግለጫ

⭐️ሰው የሚገነዘብ አእምሮና የሚያፈቅር ልቦና ባለቤት ነው።እነዚህ ሁለቱ ካልተመጣጠኑ ስብእናው አደጋ ውስጥ ነው።የሚያገናዝበው አዕምሮው፣የሚያፈቅረው ልቡ፣የሚንቀሳቀሰው አካሉናወደ ሰማይ የሚወነጨፈው መንፈሱ በውህደት ካልተንቀሳቀሱ ሰውየው ላይ ችግር አለ ማለት ነው
📨የፍቅር እና የጥላቻ ስሜቱ፣የፍላጎት እናየፍርሃት መንፈሱ በአዕምሮ ብስለት ካልተገራ አስቸጋሪ ነው
አስተያየት👇
T.me/Aisuu_bot

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 29

2022-09-07 11:54:43   ከአንደኛ ክፍል ጀምሬ አንዲት ጓደኛ ያዝኩኝ ልጅቱም ፌሩዛ ትባላለች ...ፌሩዛ በትምህርቷ ጎበዝ ነች እኔም እንደ እሷ ጎበዝ መሆን የኔም የአባቴም ምኞት ነዉ  ጓደኛየ ማድረግ ወሰንኩ ፡፡ ክፍላችን ዉስጥ ተሰሚነት ነበረኝ እኔ ከክላስ ልጅ አንድ ልጅ ጋር ከተጣላሁ የተጣላሇትን እሷን እንዳታወሩ ካልኩኝ የሚያወራት የለም ፡፡ እኔ የወደድኩትን ይወዳሉ የጠሉትን ይጠላሉ....እኔ የምጫወትዉን ይጫወታሉ እኔ የማይመቸኝን ጨዋታ አይጫወቱም ፡፡

   ቁርአን ደግሞ መቅራት የጀመርኩት KG ተማሪ በነበርኩበት ሰአት ሲሆን ቁርአን የገባሁትም ጅማ ኑር (አጅፕ)መስጊድ ያለዉ ቁርአን ቤት ነዉ ..ገና አፌ መናገር ሲጀምር አባቴ ቁርአን እንድቀራ በቁርአን ጎበዝ እንድሆን ይመክረኝ ያበረታታኛል..ግን ምን ዋጋ አለዉ በአንድ ሰዉ ጥረት አይሆን..ቁርአን እንድቀራ እናቴ ትኩረት ስላልሰጠችኝ መድረሳ ቁርአን ለመቅራት እመላለሳለሁ እንጂ አሊፍ ባታ ሳ ጂም ብሎ ሁሉንም ፊደል ለመለየት  ሶስት አመታት ፈጅቶብኛል፡፡
   
    ቀን ማታ መሽቶ ነግቶ ሁሌ ሀሳብ የሆነብኝ ነገር የሰፈር ልጆች ልጫወት እነሱ ጋር ስሔድ አንቺ ጋር አንጨዋትም እያሉ እኔን ለብቻየ የሚያገሉኝ ነገር ሚስጥሩን ምክንያቱን ላዉቀዉ አልቻልኩም  ..እንደ ልጅነቴ የሰፈር ልጆች ጋር የመጫወት እድል ላገኝ አልቻልኩም....እኔ ከእነሱ ጋር የማልጫወትበት ምክንያት ምንድን ነዉ ??? እያልኩ እራሴን ብጠይቅ መልስ ሊመጣልኝ አልቻለም..

    አባቴንም ሁሌ ቀን በቀን እኔ ጋር አልጫወትም አሉኝ እያልኩ እነግረዋለሁ የአባቴ መልስ ግን ምንም ሊቀየር አልቻለም ...
....ተያቸዉ ልጆቹ ጋር አትጫወች የምትለዉ መልስ ብቻ ነዉ የሚመልስልኝ...ተለዋጭ መልስ ሊሰጠኝ አልቻለም
   

    አንድ ቀን የሰፈር ልጆች ተሰብስበዉ ሲጫወቱ የሚጫወቱት ጨዋታ በጣም ደስ አለኝና ...እኔም  በግድም ቢሆን ሂጄባቸዉ የሰፈር ልጆች ጋር ጨዋታ ጀመርን ....ልጅነት መቼም ጨዋታዉ ፈረሰ ዶቦዉ ተቆረሰ ከተባለ መጣላታችን አይቀርም አይደል...አንዲት የጎረቤታችን ልጅ ጋር ተጣላን ...ከዛም ከልጅቱ ጋር ሲያገላግሉን መሰዳደብ ጀመርን ....
........ተጣልተን ስንሰዳደብ እኔ የልጅነት አንቺ ማስጠሌ አይጥ እያልኩ ስሳደብ እሷ ግን የሰፈር ሰዉ በተሰበሰበት መሀል ከአእምሮ የማይዋጥ የሚዘገንን በልጅ አቅሜ መሸከም የማልችለዉ ስድብ ሰደበችኝ
....እኔም ይሄን ስድብ እንደሰደበችኝ ደነገጥኩ ... እሷ ጋር ስድብ መመላለስ አፍ መካፈቴን አቁሜ ስድቡን እያብሰለሰልኩ እየተገረምኩ እንዴት እንዲህ ብላ ትሰድበኛለች???እያልኩ ወደ ቤቴ ሄድኩኝ..

እቤት ስገባ የአላህ ነገር አባቴ ቁጭ ብሎ አገኘሁት...
ፊቴ መቀያየሬ መናደዴን ያየዉ አባቴ ምን ሁነሽ ነዉ ልጄ ፊትሽ ተቀያይሯል ሰዉ ጋር ተጣልተሻል እንዴ???? አለኝ
......እኔም አባቴ የጎረቤታችን ልጅ""" ........."""ብላ ሰደበችኝ እኮ አልኩት ..
.......ወዳዉ አባቴ ፊቱ ተቀያየረ ተናደደ እና ቁጭ ካለበት በመነሳት መኝታ ክፍል ገብቶ ሽጉጡን ከአስቀመጠበት አንስቶ ወዳዉ አቀባብሎ ከመኖሪያ ቤት ወጥቶ የሰደበችኝን ህፃኒቱን የኔኑ እኩያ በሽጉጥ ሊገላት ይፈልጋት ጀመር፡፡ 


አባቴ በጣም ተናዷል ጅማቱ ዉጥርጥር ብሏል....ልጅቱ መኖሪያ ቤት ሂዶ ነይ ዉጪ የት ነሽ ዛሬ እገልሻለሁ እያለ እየፈለጋት ነዉ...

ሰፈሩ በአንድ እግሩ ቆመ ..የኛ ጎረቤቶች በኛ ቤት አቅራቢያ የሚገኙ ዘመድ አዝማዶች ተሰብስበዉ ንዴት አብርድ እያሉ እየለመኑት ነዉ ...

አባቴን ተረጋጋ እባክህ ተብሎ በጓደኞቹ በዘመድ አዝማዶች በስንት ጉድ ተለምኖ ተመልሶ እቤቱ ገባ፡፡ ግን አባቴ ልጅቱን አለቃትም ሌላም ቀን ቢሆን በዚህ ሽጉጥ አናቷን ብየ ነዉ የምገላት እያለ ይደነፋል............

  ማታ ተኝቼ ብቻየን ማሰብ ማሰላሰል ጀመርኩኝ አብረን የምንጫወት የሰፈራችን ልጅ እንዴት ልሰድበኝ ቻለች ???ይሄን ለጆሮ ለመስማት የሚዘገንን ስድብ እንዴት ሰደበችኝ ???አባቴስ ስነግረዉ ለምን እገላታለሁ ብሎ ደነፋ ???? እያልኩ ብቻየን ሳስብ አደርኩኝ....ግን ይሄን ስድብ እዉነት ነዉ ወይስ ዉሸት?? ማጣራት አለብኝ ብየ ወሰንኩ ...ግን ማንን ልጠይቅ ???
   
የምጠይቀዉ ሳጣ ሲጨንቀኝ አንድ ሀሳብ መጣልኝ ለምን የቤት ሰራተኛችንን አልጠይቃትም???ብየ አሰብኩኝ...እሷን ለመጠየቅ ወሰንኩ

የቤት ሰራተኛችንን ልጅቱ ለምን"""""""____"""""እንደዚህ ብላ እንደሰደበችኝ ጠየኳት ...ሰራተኛችን ለመንገር ፍቃደኛ አልሆነችም ... ግን እኔ ንገሪኝ እያልኩ አፋጥጬ ስይዛት የቤትሰራተኛችን እያለቀሰች ....,እንደዚህ አለችኝ.........


ልጅቱ የሰደበቻት ምን ብላ ነዉ ????  የተደበቀዉ ...ማንነት ምንድን ነዉ ???ለምን አባትየዉ ገና ነፍስ ያላወቀችን ልጅ አገላለሁ ብሎ ለምን ተነሳ ??? የተቆለፈዉ ሚስጥር ምንድን ነዉ ???
በሚቀጥለዉ ክፍል እናያለን


#ክፍል
ይ....ቀ...ጥ.....ላ....ል

t.me/Islam_and_Science
392 views08:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-07 11:54:18 አሳዛኝ እዉነተኛ ታሪክ
 
የታሪኩ ርዕስ
#የሆድ_ዉስጥ_ፉም_እሳት
      #ክፍል ☞  አንድ

ፀሀፊ ☞ #አሚር_ሰይድ



    በሰዎች ዉሳኔና ፍላጎት ምኞት እና ጉጉት ብቻ ተፈፃሚ የሚሆን ነገር የለም የአሏህ ፍቃድ እስካልታከለበት ድረስ.. አንዳንዴ በሰዉ በዘመድ ተከበህ ሰዉ ይናፍቃል. እዉነት ነዉ በአለም ላይ በቢሊየን የሚሆን ህዝብ እያለ የዉስጡን የሆዱን የታፈነ ነበልባል አንድ ሰዉ ላይረዳህ ይችላል...የዚህን ጊዜ ብቸኝነት ማለት ምን ማለት እንደሆነ መረዳት ይቻላል ፡፡

     ዉሀ ላይ ሁኜ ዉሀ ይጠማኛል
     እሰዉ ጋር ሁኜ ሰዉ ይናፍቀኛል
      የያዘኝ በሽታ ወንድም ያሰኘኛል
አንድ መንዙማ ላይ የሰማሁት ነዉ . እዉነት ነዉ ዉሀ ጠምቶህ ጠጥተሀዉ ሆድህ ቢገባም ዉሀዉ ጥምህን የማይቆርጥ ከሆነ
በሰዉ መሀል ተከበህ ሰዉ ሲያስፈልግህ ሰዉ ግን አንተን ለመረዳት ሳይፈልግ በአንተ ላይ የሚሳለቅ ከሆነ ሰዉ መሀል ተከበህ ጥቅሙ የሚሆነዉ የሰዉ ቆጠራ ጊዜ አብሮ ተቆጥሮ አለ ይሄን ያህል አለ ለማለት ያህል ካልሆነ በቀር ....

የተፈጠርንበት ማንነት ዲነል ኢስላም በወንድምነት በእህትነት አስተሳስሮን ነገር ግን ዛሬ ጓደኛ ነገ ደግሞ ጥላት እየሆነ የመጣ ይመስላል. ታዳ መቼ ይሆን ለሰዉ እዉነተኛ ሰዉ የምንሆነዉ???..ለሰዉ ልጅ በሽታዉም ህመሙም ያዉ አላህ እንደቀደረዉ ሁኖ ታንቆም መርዝ ጠጥቶም የሚሞተዉ ያዉ በሰዉ ምክንያት ነዉ ..ምክንያቱም ይህን ዉሳኔ የወሰነዉ መቼም ሰዉ ነዉ እና ጥፋት አይቀርም..አጥፍቶ መሄጃ ሲያጣ በአማከረዉ ሰዉ ወይም ለልብ ጓደኛዉ የልቡን ነግሮት ግን የተናገረዉን ከጆሮ ባልዘለለ ከልቡ ሳያስቀምጠዉ ሲቀር ያኔ ከሰዉ በላይ አላህ ይጠብቀን ሸይጧን ይቀርበዋል ይሳሳታል ይታነቃል ወይ መርዝ ይጠጣል ..ይሄን ዉሳኔ የሚወስነዉ ዱንያን መሮት እንጂ ተመቸቶኝ ብሎ ራሱን የሚያጠፋ የለምና...

በጥናት ዉጤት ስናየዉ አሜሪካ በአንድ አመት ብቻ 25,000 ሰዎች ራሳቸዉን ያጠፋሉ ቻይና በየዓመቱ 30,000 ሰዉ ራሱን ያጠፋል በአለም ላይ በየ20 ሰከንዱ ሰዎች ራሳቸዉን ያጠፋሉ ይህ ማለት በአለም ላይ ወደ በአንድ አመት ሁለት ሚሊየን ህዝብ እራሳቸዉን ያጠፋሉ ማለት ነዉ፡፡

ሁሉም ሰዉ ሊያወቀዉ የሚገባ የማይካድ ሀቅ ደስታ በዲነል ኢስላም አላህ ጋር ባለን ግንኙነት እንደሚወሰን መገንዘብ አለብን..የቁርአንን መመሪያ መከተል ለዚህ ያለእድሜዉ እራሱን ለሚያጠፋዉ እና በሂወት እያለ ሒወት እንደ ዥዋ ዥዌ ጨዋታ ለሆነችበት ቁርአን መፍትሄ እንደሆነ እርግጥ ነዉ .... አሁን ጊዜ ላይ ያለነዉ የሁላችንም ጥፋት የቁርአን መመሪያ እኛ መከተሉን ትተን በእኛ መስመር እንዲከተለን መፈለጋችን ነዉ፡፡

ታዳ ለዚህ ሁላ ራሱን ላጠፋዉ ተጠያቂዉ ሰዉ አይደለም ብላችሁ ታስባላችሁ??? ሰዉ ከሚሳሳትባቸዉ ምክንያቶች ዋናዉ እና አንደኛዉ ባለፈዉ ጊዜ ምን ምን ነገሮች ነበሩ??ዛሬ ምን ይደረጋል?ነገስ ምን ይመጣ ይሆን? የሚሉትን ጥያቄዎች ሳያስተዉሉ ሁሉንም ነገር ለዛሬ ብቻ ሲሰጡ ነዉ፡፡

አንዳንድ ሰዎች ደስታ የሚገኘዉ በብር ብቻ ነዉ ብለዉ የሚያምኑ አሉ... ስህተት ነዉ ደስታ የሚገኘዉ በዲነል ኢስላም ነዉ :: ዲነል ኢስላምን አዉቆ ያልሰራበት ደስታ በጭራሽ አያገኝም..ለምሳሌ አሜሪካንን እንዉሰድ የአለም ኢኮኖሚ 50% በአሜሪካ እጅ ይገኛል ነገር ግን በአለም ላይ በደስታ የሚኖሩ አገሮች ቁጥር ተርታ ስትሰለፍ 116 ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡በተዘዋዋሪ ደግሞ በአለም ላይ በደስታ የሚኖሩ ሀገሮች የመሪዎችን ደረጃ የያዙት ሙስሊም ሀገራት ሲሆኑ.....ቁጥር 1 ናይጀሪያ ናት ..ናይጀሪያ እንደምናዉቀዉ የሙስሊም ሀገር ናት በኢኮኖሚዋ ዝቅተኛ ብትሆንም ግን የመጀመሪያ አላማቸዉ አላህን ማስደሰት ስለሆነ በአላቸዉ ተብቃቅተዉ በደስታ ይኖራሉ

የሰዉ ልጅ ብር ደስተኛ እንደማያረግ የጃፓኑን ትልቅ ድልድይ በቀን ከ300 መኪና በላይ የሚተላለፍበትን የገነባዉ ኢንጅነር በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር ገቢ ያገኘ ቢሆንም ተመርቆ አገልግሎት በሚሰጥበት ቀን በትንሽ ቁራጭ ወረቀት ኑዛዜ አስቀምጦ ራሱን ከድልድይ ላይ በመጣል ራሱን አጥፍቷል...በኑዛዛዉ እንዳስቀመጠዉ """"እኔ የገንዘብ ችግር አላጋጠመኝም ደስታ በማጣቴ ብቻ ከዚህ አለም ለመሰናበት ፈልጊያለሁ"""" ነበር ያለዉ ፡፡

በአለም ላይ የሰዉ ልጅ ራሱን ለመቀየር 24ቢሊዮን ዶላር/ ሴቶች ለኮስሞቲክስ 18ቢሊዮን ዶላር /ፀጉርን ለመንከባከብ 38ቢሊየን ዶላር /ለሽቶ ደግሞ 15ቢሊዮን ዶላር በአመት ያወጣሉ... ታዳ ሰጥቶን ስጡ ለተባልነዉ ዱንያ የአላህ ወዴታን ለማግኘት ስንት አዉጥተናል?? ለተቸገረ ሰዉ ስንቶቻችን የችግሩ መፍትሄ ሁነናል??ስንቶቻችን ነን ደሀ እና ሀብታምን ሳንለያይ በአንድ አይን የምናየዉ???
ነብዩ ሙሀመድ ሰ.ዐ.ወ አንድ ሰዉ ጀሀነም እሳት ዉስጥ ለመግባት ሙስሊም ወንድሙን በዝቅተኛ አይን ማየቱ በቂ ነዉ ብለዋል..እስኪ ሆድ ይፍጀዉ

    የኔ ታሪክ ስለ ሁላችንም የሰዉ ማንነት ላይ ዱንያ የደስታ ህይወት አለመሆኗን  ያተኮረ ሲሆን እስኪ ሳይረፍድ ወደ ታሪኩ እንግባ
    ቅድሚያ መተዋወቅ ይቀድማል እንተዋወቅ የእናንተን ባለቅም የእኔ ስም ነዋል እባላለሁ አሁን ላይ የኔ እድሜ አስራ ዘጠኝ ሲሆን ፡፡ እኔ የመጀመሪያ ልጅ ነኝ ከእኔ በታች በሶስት አመት የምበልጠዉ አንድ ታናሽ ወንድም እና በጣም ታናሽ እህት አለችኝ..በጠቅላላ ለቤተሰቦቻችን ሶስት ልጆች ነን፡፡
ተወልጄ ያደኩት የፍቅር የመከባበር ሀገር በሆነችዉ የአባጅፋር ሀገር ጅማ ከተማ በአጂፕ ሰፈር አዲሱ ገቢዎች ግምሩክ አካባቢ ነዉ፡፡

   አባቴ  ጅማ ከተማ ላይ ታዋቂ ኮንትራከተር ህንፃ ተቋራጭ ሲሆን በዚህም የተነሳ ዉብ የሆነ ቤት እና ወደ ሰባት የሚሆን መኪና ያለን ሲሆን ጅማ ላይ እስኪ ብር ያለዉ ባለሀብት ጥሩ ቢባል ቁጥር አንድ የሚጠራዉ የኔ አባት ነዉ፡፡ እንደ መጀመሪያ ልጅ በመሆኔ ምንም ሳይጎልብኝ የፈለኩትን በልቼ የፈለኩትን ጠጥቼ ነዉ ያደኩት ፡፡ አባቴ በጣም ተንከባክቦ ነዉ ያሳደገኝ ፡፡

መቼም ማንኛዉ ሰዉ እድሜዉ ከትምህርት ከደረሰ ትምህርት ቢያነስረዉ መመዝገቡ አይቀርም  ...እኔም ጅማ የሚገኘዉ ኮምዪኒቲ ትምህርት ቤት--KG1 ተመዘገብኩ፡፡ KG ትምህርቴን እንደ ጨርሼ አንደኛ ክፍልም እዛዉ ኮምዩኒቲ ትምህርት ቤት ተመዘገብኩ፡
  
የሰፈር ልጆች ጋር ከልጅነቴ ጀምረን ስጫወት እነሱ ግን እኔ ጋር መጨዋት አይፈልጉም ነበር
.....ለምን እኔ ጋር አትጫወቱም ስላቸዉ ??
....እናት አባቶቻችን አንቺ ጋር እንዳትጫወቱ ተብለናል ይሉኛል፡፡
እኔም ልጆቹ ያሉኝን ለአባቴ ሂጄ እነግረዋለሁ
...አባቴም አንጫወትም ካሉሽ አትጫወቺ ምን ያረጉልሻል እቤትሽ አድበሽ ተጫዋቺ ይለኛል


     አንደኛ ክፍል እየተማርኩ የኔ ጓደኛ ለመሆን የማይጥር የለም ... ትምህርት ቤት ስሄድም ስመጣም መኪናዉ የራሳችን ስለሆነ አባቴ በያዘልኝ ሹፌር ነዉ የምመላለሰዉ ፡፡ የሀብታም ልጅ ስለሆንኩ ነዉ መሰለኝ ብዙ ሴት ልጆች እኔን ጓደኛ እንድሆናቸዉ ይቀርቡኛል
340 views08:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-07 11:51:44 አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱሏሂ ወበረካትሁ፡፡
አንዳንድ የቻናል admin እና ዩቲዩበሮች የሆድ ዉስጥ ፉም እሳት እዉተነኛ ታሪክ በ45 part የተቀረበዉን በአጭር part አርግልን ስላላችሁ በዉስጡ ያሉትን አባባሎች እና አጭር ምክሮች ተቀንሰዉ እና ሁለቱን part በአንድ በማድረግ ከዛሬ ጀምሮ ይቀርባል መልካም ንባብ፡፡

በአስተያየት መስጫ ማንኛዉንም ሀሳብ አስተያየት አልቀበልም

አሚር ሰይድ
364 views08:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-06 21:57:05 የአቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረድየሏሁ ዐንሁ) ታሪክ

የመጨረሻ ክፍል
  
የአል-ፋሩቅ መተካት

የአቡበክር አስ-ሲዲቅ ሞት ምክንያት ላይ የተለያዩ አስተያየቶች ተሰንዝረዋል፡፡ የሞቱት ከፍተኛ ቅዝቃዜ ባለው ውሃ በመታጠባቸው ምክንያት ብርድ በሽታ ታመው ነው የሚሉ እንዳሉ ሁሉ የለም እርሳቸው የሞቱት አንድ አይሁዳዊ የተመረዘ ምግብ አብልቷቸው ለአስራ አምስት ቀናት ያህል ታመው ነው የሚሉም አሉ፡፡ ..

ይህ በእርግጥ ለአይሁዶች አዲስ አይደለም፡፡ ብዙ ነብያትን የመግደል ልምድ አካብተዋል፡፡ ሰይድ ኢሳን (ዐ.ሰ) ለመግደል ሞክረዋል፡፡ ነብዩን (ሰዐ.ወ) ሶስት ጊዜ ለመግደል ሞክረው አልተሳካላቸውም፡፡ ሁከትና ብጥብጥ እንዲፈጠር አድርገው ለዑመር ቢን አል ኸጣብ፣ ለዑስማን ቢን ዓፋን ለጦልሃና ለዙበይር መገደል ምክንያት የሆኑት አይሁዳዊያን ናቸው፡፡

ሰይድ አቡበክር ላይ ሕመም በጠናባቸው ጊዜ ሶሃቦች በርሳቸው ቦታ ላይ ሰይድ ዑመርን እንዲተኩ እያማከሯቸው ነበር፡፡ አስ-ሲዲቅ ዓብዱራህማን ቢን ዓውፍን ስለ ዑመር ሲጠይቋቸው እንዲህ ሲሉ መለሱ፡፡ «አንቱ የረሱል ኸሊፋ ሆይ ዑመር ከምናስባቸው በላይ ጥሩ ሰው ናቸው።››

ዑስማንን ሲጠይቋቸው ደግሞ እንዲህ አሉ... “ከላያቸው በተሻለ ውስጣቸው ጥሩ እንደሆነ አስተምረውኛል፡፡” አቡበክር ሌሎችንም ታላላቅ ሶሃባዎችን ሲያማክሯቸው በጉዳዩ ላይ ተስማሙ።

አንዳንድ ስዎች ደግሞ እንዲህ አሏቸው “ዑመር ኃይለኛነት አለባቸው፡፡ አላህ እንዴት ኸሊፋ አደረግካቸው ብሎ ቢጠይቅዎ ምን ሊመልሱ ነው” አቡበክርም ተቆጡና እንዲህ አሉ... “ደግሞ በአላህ ታስፈራሩኛላችሁ... ወላሂ አላህ ቢጠይቀኝ ከምርጥ ሰዎችህ ምርጥ የሆነውን በእኔ ቦታ ተክቼዋለሁ ብዬ እመልስለታለሁ፡፡”

ከዚያም አቡበክር ዑስማን ቢን ዓፋንን(ረ.ዐ) አስጠሯቸውና እንደሚከተለው እንዲጽፉ አዘዟቸው፡፡... “ይህ ኑዛዜ ከዱኒያ ለመጨረሻ ጊዜ ሲሰናበት ወደ አኼራ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲሄድ አቡበክር ቢን አቢ ቁሃፉ ያስተላለፈው ትዕዛዝ ነው። ሐሰተኞች እውነት እንዲናገሩ፣ አመጸኞች አደብ እንዲገዙ፣ ከሃዲዎች እንዲያምኑ ስል ይህን ትዕዛዝ አስተላልፌያለሁ... ተክቼላችኋለሁ...” የተኩትን ሰው በስም ሳይጠቅሱ ራሳቸውን ይስታሉ።

ሰይድ ዑስማን “ዑመር ቢን አል-ኸጧብን ተክቼላችኋለሁ...” የሚል ዓረፍተ ነገር ጻፉ። ዑስማን ይህን ያደረጉት አስ-ሲዲቅ የተኩትን ስው በግልጽ ሳይናገሩ ካለፉ በሙስሊሞች መካከል ውዝግብ ይፈጠራል ብለው ሰግተው ነው። በተጨማሪም አቡበክር( በርሳቸው ቦታ መተካት ያለበት ሰው ማን እንደሆነ መወሰናቸውን ዑስማን(ረ.ዐ) ስለሚያውቁ፡፡

አስሲዲቅ(ረ.ዐ) ትንሽ መለስ እንዳሉ ዑስማን(ረ.ዐ) የጻፉትን እንዲያነቡላቸው አዘዟቸው... “በእኔ ቦታ ዑመር ቢን አል-ኸጣብን ተክቼላችኋለሁ፡፡” የሚለውን አነበቡ። በዚህ ጊዜ ሰይድ አቡበክር እንዲህ አሉ... “አሏሁ አክበር! የተካሁትን ሰው በስም ሳልናገር ሕይወቴ ብታልፍ ሙስሊሞች ይጨቃጨቃሉ ብለህ ስግተህ ነበር ማለት ነው? ለእስልምና እና ለሙስሊሞች ለዋልከው ውለታህ አላህ መልካም ምንዳ ይክፈልህ ዑስማን”

ከዚያም አስ-ሲዲቅ ሶሃቦች እንዲሰባሰቡ አደረጉና እንዲህ አሏቸው... “እናንተ ሰዎች ሆይ! እኔ ዱኒያን ተሰናብቼ ወደ አኼራ መጓዜ ነው፡፡ በዚህ ወረቀት ውስጥ እኔን የሚተካ ሰው ገልጬላችኋለሁ፡፡ እርሱን ስሙት ታዘዙትም፡፡ እኔ ለእናንተ የመረጥኩላችሁን ስው ትቀበሉታላችሁን?” ብለው ሲጠይቁ ሁሉም በህብረት “ተደስተናል” አሉ።

ዓሊይ ቢን አቢ ጧሊብ(ረዐ) ተነሱና እንዲህ አሉ... "ዑመር ካልተሾሙ በቀር አንደሰትም...” አስ-ሲዲቅ ፈገግ አሉና "የተሾመው ዑመር ቢን አል-ኸጣብ ነው፡፡ ስሙት ታዘዙትም። ወላሂ ስለርሱ መልካምን እንጂ ሌላ የማውቀው ነገር የለኝም”

     የወዳጆች መመሳሰል

አቡበክር ዛሬ ቀኑ ማነው” ሲሉ ጠየቁ፡፡ “ሰኞ ነው” አሏቸው “ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) በምን ቀን ነበር ያለፉት" ሲሉ አከሉ፡፡ ሰኞ ቀን፡፡ አቡበክርም እንዲህ አሉ “እላህ ሆይ ሞቴን በዚችው ሌሊት አድርግልኝ ከዚያም እንዲህ ጠየቁ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) የተከፈኑት በምን ዓይነት ከፈን ነበር” የተከፈኑበትን ነገሯቸው፡፡ “እኔንም በዚያው ዓይነት ከፍኑኝ፡፡ አስክሬኔንም ባለቤቴ አስማእ ቢንት ዑመይስ ትጠበኝ...”

      የአስ-ሲዲቅ ጉዞ
እሜቴ ዓኢሻ ወደ ቤት ገብታ ማልቀስ ስትጀምር አስ-ሲዲቅ ከለከሏት። ከዚያም አጠገባቸው ተቀምጣ ግጥሞችን ትገጥም ጀመር፡፡ አቡበክርም ዓኢሻን እሱን ተይና እንዲህ የሚለውን የቁርኣን አንቀጽ አንብቢ

وَجَاءَتْ سَكْرَةُ الْمَوْتِ بِالْحَقِّ ۖ ذَٰلِكَ مَا كُنتَ مِنْه تَحِيدُ (١٩) وَنُفِخَ فِي الصُّورِ ۚ ذَٰلِكَ يَوْمُ الْوَعِيدِ (٢٠)
"የሞትም መከራ እውነቱን ነገር ታመጣለች፡፡ (ሰው ሆይ)፡- «ይህ ያ ከርሱ ትሸሸው የነበርከው ነው» (ይባላል)፡፡ በቀንዱም ውስጥ ይንነፋል፡፡ ያ (ቀን) የዛቻው (መፈጸሚያ) ቀን ነው፡፡" (ቃፍ 19-20)

አስ-ሲዲቅ በመሞቻቸው ዕለት የተናገሯት የመጨረሻዋ ንግግር እንዲህ የምትል ነበረች... "ሙስሊም አድርገህ ግደለኝ፣ ከመልካሞቹም ጋር አስጠጋኝ፡፡" አቡበክር የሞቱት ሰኞ ሌሊት ነበር፡፡ በጀናዛቸው ላይ ያስገዱት ዑመር ቢን አል-ኸጣብ(ረ.ዐ) ናቸው፡፡ መላው የመዲና ከተማ በአቡበክር ሞት ምክንያት ስታነባ ዋለች፡፡ ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ካረፉበት መካነ መቃብር አጠገብ ተቀበሩ፡፡ ዓሊይ ቢን አቢጧሊብ(ረ.ዐ) ወደ መቃብሩ ተጠጉና እንዲህ አሉ። “አቡበክር ሆይ አላህ ይዘንልህ፡፡ ወላሂ ከሙስሊሞች አንደኛ አንተ ነበርክ፡፡ በኢማን ጥልቀትና ጥንካሬ አንተን የሚያክል የለም፡፡ ረሱልን (ሰ.ዐ.ወ) በመንከባከብ፣ እስልምናን በመጠበቅ ወደር አልነበረህም፡፡ ለሙስሊሞች ሩህሩህ ነበርክ፡፡ ከረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ጋር በአፈጣጠርም፣ በስነምግባርም፣ በግርማ ሞገስም ተመሳሳይ ነበርክ፡፡ ለእስልምና እና ለረሱል (ሰ.ዐ.ወ) የከፈልከውን ውለታ አላህ በመልካም ይመልስልህ። ስዎች ረሱልን (ስ.ዐ.ወ) እምቢ ሲሏቸው ኣንተ አስተናገድካቸው። ተቀበልካቸው፡፡ ሲያገሏቸው አንተ አቀረብካቸው፡፡ ምን ጊዜም ከጎናቸው ነበርክ፡፡ አላህ (ሱ.ወ) በመጽሐፉ እውነተኛ ብሎ ጠርቶሃል. “ያም በእውነት የመጣው በርሱ ያመነውም” ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ያመጡትን እውነት እውነት ብለህ የተቀበልከው አንተ ነህ፡፡ ወላሂ ለእስልምና ጋሻና መከታ፣ ለከሓዲያን ደግሞ ቅጣት ነበርክ፡፡ ጎርፍም ሆነ አውሎ ንፋስ የማያናጋው ተራራ ነበርክ፡፡ ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ስለ አንተ እንደተናገሩት ሰውነትህ ለስላሳ ቢሆንም በአላህ ትዕዛዝ ላይ ግን ጠንካራ ነበርክ፡፡ ለራስህ የምትተናነስ ብትሆንም አላህ ዘንድ ግን ከፍ ያልክ ነህ፡፡ በምድር ላይ ኃያል፣ ሙስሊሞች ዘንድ ደግሞ ታላቅ ነበርክ፡፡ ለእኛ የዋልከውን ውለታ አላህ በመልካም ይመልስልህ፡፡ ባንተ ላይ ቂምም ሆነ ብሶት ያለበት ሰው የለም፡፡ ደካማ የድርሻውን እስካላገኘ ድረስ አንተ
ዘንድ ኃያል ነበር፡፡ ኃያሉ የሌሎችን ድርሻ እስኪሰጥ ድረስ አንተ ዘንድ ደካማ ነበር፡፡ ምንዳህን አላህ አይከልክለን፡፡ ካንተ በኋላም አያጥምመን፡፡”

  ረ ዲ የ ሏ ሁ  ዐ ን ሁ

ምስጋና ይገባው ለአሏህ ﷻ ይህን ታሪክ አስጀምሮ ላስጨረሰን
http://t.me//@arebgendamesjid
        እዚጋ  ተጠናቀቀ

የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ
320 views18:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-06 11:22:31 #ተውበት (ወደ አላህ መመለስ)
ተዉበት በሠራነዉ ስራ ተፀፅተን ወደአላህ መመለስ ከፈጣሪ ምህረትን መጠየቅ
ነው ይችን ዱኒያ ዛሬ ይሁን ነገ መቸ እንደምንለያት አናቅምና ሁሌም መች እና
እንደት እንደሚመጣብን ለማናዉቀዉ ሞት ማስታወስ ግድ ነው በየትኛዉ ሠከንድ
እንደሚመጣ የአላህ ቀጠሮ አናዉቅምና
ተውበት (ወደ አላህ መመለስ)

#ተውበት፡- በአላህ ትእዛዝ ላይ ከማመፅ ለህግጋቱ ወደ መታዘዝ. መመለስ ነው፡፡

#ተውበት፡- ተውበት አላህዘንድ በጣም የተወደደ ነው።
‹‹… ﺇِﻥَّ ﺍﻟﻠَّﻪَ ﻳُﺤِﺐُّ ﺍﻟﺘَّﻮَّﺍﺑِﻴﻦَ ﻭَﻳُﺤِﺐُّ ﺍﻟْﻤُﺘَﻄَﻬِّﺮِﻱﻥَ
‹‹ ....አላህ (ከኃጢኣት) ተመላሾችን ይወዳል፤ ተጥራሪዎችንም ይወዳል
በላቸው፡፡››
አል በቀራህ 222
ተውበት በእያንዳንዱ አማኝ ላይ ግዴታ ነው፡፡
አላህ እንድህ ይላል:-
ﻳَﺎ ﺃَﻳُّﻬَﺎ ﺍﻟَّﺬِﻳﻦَ ﺁﻣَﻨُﻮﺍ ﺗُﻮﺑُﻮﺍ ﺇِﻟَﻰ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﺗَﻮْﺑَﺔً ﻧَّﺼُﻮﺣًﺎ ﻋَﺴَﻰٰ ﺭَﺑُّﻜُﻢْ ﺃَﻥ ﻳُﻜَﻔِّﺮَ ﻋَﻨﻜُﻢْ ﺳَﻴِّﺌَﺎﺗِﻜُﻢْ
ﻭَﻳُﺪْﺧِﻠَﻜُﻢْ ﺟَﻨَّﺎﺕٍ ﺗَﺠْﺮِﻱ ﻣِﻦ ﺗَﺤْﺘِﻬَﺎ ﺍﻟْﺄَﻧْﻬَﺎﺭُ ﻳَﻮْﻡَ ﻟَﺎ ﻳُﺨْﺰِﻱ ﺍﻟﻠَّﻪُ ﺍﻟﻨَّﺒِﻲَّ ﻭَﺍﻟَّﺬِﻳﻦَ ﺁﻣَﻨُﻮﺍ ﻣَﻌَﻪُ ۖ
ﻧُﻮﺭُﻫُﻢْ ﻳَﺴْﻌَﻰٰ ﺑَﻴْﻦَ ﺃَﻳْﺪِﻳﻬِﻢْ ﻭَﺑِﺄَﻳْﻤَﺎﻧِﻪِﻡْ ﻳَﻘُﻮﻟُﻮﻥَ ﺭَﺑَّﻨَﺎ ﺃَﺗْﻤِﻢْ ﻟَﻨَﺎ ﻧُﻮﺭَﻧَﺎ ﻭَﺍﻏْﻔِﺮْ ﻟَﻨَﺎ ۖ ﺇِﻧَّﻚَ ﻋَﻠَﻰٰ
ﻛُﻞِّ ﺷَﻲْﺀٍ ﻗَﺪِﻳﺮٌ
‹‹እናንተ ያመናችሁ ሆይ ንፁህ የኮነችን ፀፀት በመፀፀት ወደ አላህ
ተመለሱ…..››
አል ተህሪም 8
‹‹… ﻭَﺗُﻮﺑُﻮﺍ ﺇِﻟَﻰ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﺟَﻤِﻴﻌًﺎ ﺃَﻳُّﻪَ ﺍﻟْﻤُﺆْﻣِﻨُﻮﻥَ ﻟَﻌَﻠَّﻜُﻢْ ﺗُﻔْﻠِﺤُﻮﻥَ
‹‹ ... ምእመናኖች ሆይ! ትድኑ ዘንድ ሁላችሁም ወደ አላህ (በመመለስ)
ተጸጸቱ፡፡››
ሱረት አል-ኑር 31
መድህን (ፈላህ) ማግኘት ማለት አንድ ሰው የፈለገውን ማግኘት የሚፈራውን
ነገር መዳን ነው፡፡
ፍፁምና እውነተኛ የሆነ ተውበት፡- ኃጢአቱ የፈለጉትን ያህል ቢከብድና ቢበዛም
እንኳን አላህ # ፍፁምና_እውነተኛ ከሆነ ተውበት ኃጢአቶችን ሁሉ ይቅር ብሎ
ምህረት ያደርጋል፡፡
۞ ﻗُﻞْ ﻳَﺎ ﻋِﺒَﺎﺩِﻱَ ﺍﻟَّﺬِﻳﻦَ ﺃَﺳْﺮَﻓُﻮﺍ ﻋَﻠَﻰٰ ﺃَﻧﻔُﺴِﻬِﻢْ ﻟَﺎ ﺗَﻘْﻨَﻄُﻮﺍ ﻣِﻦ ﺭَّﺣْﻤَﺔِ ﺍﻟﻠَّﻪِ ۚ ﺇِﻥَّ ﺍﻟﻠَّﻪَ ﻳَﻐْﻔِﺮُ
ﺍﻟﺬُّﻧُﻮﺏَ ﺟَﻤِﻴﻌًﺎ ۚ ﺇِﻧَّﻪُ ﻫُﻮَ ﺍﻟْﻐَﻔُﻮﺭُ ﺍﻟﺮَّﺣِﻴﻢُ
በላቸው «እናንተ በነፍሶቻችሁ ላይ ድንበር ያለፋችሁ ባሮቼ ሆይ! ከአላህ እዝነት
ተስፋ አትቁረጡ፡፡ አላህ ኃጢኣቶችን በመላ ይምራልና፡፡ እነሆ እርሱ መሓሪው
አዛኙ ነውና፡፡
አል-ዙመር - 53
http://t.me//@arebgendamesjid
SHARE SHARE
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ
989 views08:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-05 21:21:16 አቂደቱል ዋሲጥያ
ሸይህ ዑመር አሊ
  ክፍል-21-
http://t.me//@arebgendamesjid
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ
ዘርፍ
387 views18:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 20:53:25 አቂደቱል ዋሲጥያ
ሸይህ ዑመር አሊ
  ክፍል-20-
http://t.me//@arebgendamesjid
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ
ዘርፍ
588 views17:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 16:45:45

181 views13:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ