Get Mystery Box with random crypto!

ISLAM IS UNIVERSITY

የቴሌግራም ቻናል አርማ islamisuniverstiy_public_group — ISLAM IS UNIVERSITY I
የቴሌግራም ቻናል አርማ islamisuniverstiy_public_group — ISLAM IS UNIVERSITY
የሰርጥ አድራሻ: @islamisuniverstiy_public_group
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.00K
የሰርጥ መግለጫ

⭐️ሰው የሚገነዘብ አእምሮና የሚያፈቅር ልቦና ባለቤት ነው።እነዚህ ሁለቱ ካልተመጣጠኑ ስብእናው አደጋ ውስጥ ነው።የሚያገናዝበው አዕምሮው፣የሚያፈቅረው ልቡ፣የሚንቀሳቀሰው አካሉናወደ ሰማይ የሚወነጨፈው መንፈሱ በውህደት ካልተንቀሳቀሱ ሰውየው ላይ ችግር አለ ማለት ነው
📨የፍቅር እና የጥላቻ ስሜቱ፣የፍላጎት እናየፍርሃት መንፈሱ በአዕምሮ ብስለት ካልተገራ አስቸጋሪ ነው
አስተያየት👇
T.me/Aisuu_bot

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 26

2022-09-22 13:52:52 #ዑስማን #ኢብን #ዐፋን ( ረዲየሏሁ ዐነሁ) የዒባዳን ጥፍጥና በአራት (4 ) ነገሮች አግኘው አሉ :-

➊አላህ ያዘዘውን ግዴታ በመፈፀም ::

➋ #አላህ ከከለከለው ሐራም ካደረጋቸው ነገሮች
በመራቅ ::

➌ #አላህ በመልካም ያዘዘውን በመፈፀም ::

➍አላህ የሚጠላውን ነገር መሥራት የአላህን ቁጣ
ስሊሚያመጣ ፈርቶ በመተው ናቸው ::

#ኢብኑ #ዑመር የአላህ መልዕክተኛ :
( ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ) ትከሻዬን ያዝ በማድረግ " በዚህች ዓለም ስትኖር እንደ መንገደኛ ሁን " አሉኝ ማለቱ ተዘግቧል ::

#አራት #ነገሮች አሉ ላዩን ስናያቸው ምንዳ ያላቸው ውስጡን ስንመለከታቸው ግን ግዴታ መሥራት ማድረግ ያለብን ነገሮች ናቸው :: እነሱም :-
➊ከአላህ ሰዎች ጋር አብሮ መኖር

➋ #ቅዱስ #ቁርአንን መቅራት

➌ቀብርን መጎብኘትና

➍የታመመ ሰው መጠየቅ ናቸው ።

ሼር ሼር ሼር ሼር ሼር ሼር ሼር
http://t.me//@arebgendamesjid
SHARE SHARE
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ
1.4K views10:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-22 09:14:31 አባቴም:- ኡስታዝ እናንተ መጥታችሁ እንዴት እምቢ እላለሁ ??? እሺ ተስማማቻለሁ ነገር ግን ነዋል የሁለተኛ አመት ተማሪ ናት ዘንድሮን ትማር ከዛም ሶስተኛ አመቷ ላይ ኒካህ ያስራሉ ከዛም ትምህርት ስጨርስ ቀጥታ ይጋባሉ ብሎ አባቴ አስተያየት አቀረበ .
...የሚፍታህ አባትም መርሀባ ተስማምተናል ብለዉ የኔ እና የሚፍታህን ወደ ትዳር የምንገባበት ፈትል መፈተል ተጀመረ፡፡

ሰዉ ሁሉ ጆሮ ደረሰ ሚፍታህ እና ነዋል ሊጋቡ ነዉ ተብሎ በእኛ ሰፈር በአንዴ ተናፈሰ፡፡ ካሊድም ይሄዉ ወሬ ጆሮዉ ደረሰ
ካሊድም በtelegram እንዲህ ብሎ ላከልኝ
""' ወሬዉን ሰምቻለሁ አንቺ ደስተኛ ከሆንሽ ጥሩ ነዉ ..ግን አንድ ነገር እወቄ ልታገቢ ነዉ ተብሏል ነገር ግን መቼም ቢሆን እኔ ከአንቺ ተስፋ አልቆርጥም.. #ከአሏህ_ጋር_የኔ_እንደምትሆኝ_ተስፋ_አልቆርጥም አለኝ """"
   የሚፍታህ ጓደኛ የሱፍ ይሄን ወሬ ሲሰማ ከባድ ፀብ ተፈጠረ ....ሚፍታህን እገለሀለሁ አንተ ከሀዲ ጓደኛየ ነህ አምንሀለሁ ነዋልን እወዳታለሁ አንተ ጠይቅልኝ ብልህ እኔን አብሮ አደግ ጓደኛህን አሞኝተህ ሸዉደህ ለራስህ ልታገባት ነዉ አይደል ...አማናሀን በላህ ቃልህን በላህ አንተ ከሀዲ መቼም ቢሆን አንተን አለቅህም ብሎ ዝቶበት ከቤተሰብ ድረስ የደረሰ ከባድ ፀብ ተጣሉ፡፡
   
ከአሁን በፊትም እኔ ሚፍታህ በስልክ በምናወራበት  ጊዜ የሱፍ መረጃዉ ደርሶት ብዙ ጊዜ ተጣልተዋል፡፡ ጂማ ሲመጣ እና በአካል ሲገናኙ ደግሞም የትዳር ወሬዉን ሲሰማ የሱፍ መቋቋም አልቻለም፡፡ 

   እኔና ሚፍታህ የየሱፍ ፉከራ ድንፋታና እገልሀለሁ ቢልም በስልክ ማዉራታችን ተያይዘንዋል...እንደዉም ከበፊቱ በበለጠ መልኩ ስለወደፊቱ የትዳር ሒወታችን እያወራን ነዉ ...በስልክ ስንደዋወል ነዋል ስንት ልጅ ከኔ መዉለድ ትፈልጊያለሽ???ይለኛል
...እኔም አንተን ደስ የሚልህን ያህል እወልድልሀለሁ እለዋለሁ
..እኔም በተራየ ሚፍታህ ስንት ልጅ መዉለድ ትፈልጋለህ??? እለዋለሁ...
...እሱም አንቺ መዉለድ እስከምታቆሚ እወልዳለሁ ይሄን ያህል ማለት አልፈልግም ይለኛል ..

    የብዙ ቀን የደስታ ህይወት በሰከንዶች ወደ ሀዘን የሚቀይረዉን ጌታ ኩን በሚለዉ ቃሉ ዱንያ የደስታ ህይወት መኖሪያ ስላልሆነ የሀዘን ማቅ ያኮናንባል .. በቀናት በሰከንድ በደቂቃ ምን እንደሚፈጠር አናቅም ..በሀያሉ አሏህ ትዕዛዝ በአንድ ሰከንድ የስንት አመት ደስታን ማደብዘዝ ሲችል. በተዘዋዋሪ ደግሞ በአንድ ሰከንድ የብዙ አመታት ስቃይ ለቅሶን ወደ ደስታ መቀየር አይሳነዉም ..ታዳ በጊዜ ብዛት ሚፍታህ የሚያወራዉ ወሬ የማይሆን ለጆሮ የሚቀፍ ሆነብኝ ..ይህን አዲስ ባህሪ ከየት አመጣዉ እስከምል ድረስ ፀባዩ ተቀያየረብኝ ..... ስልክ ስንደዋወል እንዲህ ማለት ጀመረ>>>>>>

#ነዋል_ሚስቴ_ድንግል_ካልሆነች_መቼም_አፍርባታለሁ፡፡ የእኔ ሚስት ሁሌም ምኞቴ ድልግል እንድትሆን ነዉ..ባለፈዉ  ጓደኛየ አግብቶ  ሚስቱ ቢክራ ባለመሆና በጣም ተናዷል....እኔ ሚስቴ ቢክራ ባትሆን ሳልዉል ሳላድር ቀጥታ ለቤተሰቦቿ ነዉ የምመልሳት....
.....ጓደኛዉን ስሙን እየጠቀሰ እንትና ጓደኛየ ሚስት ቨርጅን ናት .. እንዴት ደስ እንዳለዉ ልነግርሽ አልችልም ጓደኛየ አሁን ድረስ ወሬዉ ሚስቴ እኮ ቢክራ አገኘሁባት እናንተ የምታገቡትን ሚስት አይቼ እያለን ነዉ ይለኛል.... በስልክ በተከታታይ ቀናት በደወለ ቁጥር የጓደኞቹን የትዳር ገጠመኝ ይነግረኝ ይዟል...

ስለጓደኞቹ ታሪክ ይተርክልኝ ይዟል .. ሚስቶቻቸዉ ጋር የተጣሉበት ምክንያት ምን እንደሆነ ...ከጓደኞቹ ሚስቶክ ቢክራ የሆኑት ማን እንደሆኑ እና ቢክራ ያልሆኑት ማን እንደሆኑ ታሪካቸዉን ይተርክልኛል ፡፡
....እኔም ሁሌም ታወራላችሁ ማለት ነዉ ስለዚህ ጉዳይ ??ብየ ጠየኩት
....እሱም አዎ ግድ ነዉ ጓደኞቼ ሚስጥር አይደብቁኝም እኔም አልደብቃቸዉም አለኝ

ሚፍታህ እንደዚህ ሲለኝ የኔ እጣ ፈንታ ምንድን ነዉ ???ነገ እኔም ስንጋባ ቨርጅን አይደለሁም አይቤን ለጓደኞቹ ሊያወጣብኝ ነዉ ማለት ነዉ፡፡ ሚፍታህ እኔን እስከማንነቴ አይቀበለኝም ብየ እራሴን አሳመንኩት፡፡ እየወደድኩት እያፈቀርኩት በልጅነቴ ስለተደፈርኩ ድንግል አይደለሁም ብየ ራሴን አሳምኜ ሚፍታህን ልለየዉ ወሰንኩኝ...



በልጅነቴ የደፈረኝን ቶፊቅን በመጥፎ ጎኑ እያሰብኩ ስሙን በመጥፎ እያነሳሁ ብቻየን መኝታ ክፍሌ ቁጭ ብየ አይኔ ቀይ ሸክላ አፈር እስኪመስል ድረስ አለቅስ ይዣለሁ .....ምን ይደረጋል ማንነት በእምባ አይመለስም...ፈሶ አያልቅ ወይ ከዚህ ጭንቀት አይገላግለኝ ..ይሄን ሁሉ የዘረገፍኩት እምባ አላህን ፈርቼ አንድ ቀን ባለቅስበት ስንት ሀጃየን ያሳካልኝ ነበር??ብየ አስባለሁ
ከአሁን ቡሀላ በአላህ ተወኩል ማድረግ አለብኝ አላህ ያለዉ ይሆናል ካልሆነ ይቀራል ብየ እራሴን አሳመንኩ...አላህ ያለዉ ሚፍታህ ለኔ ካለዉ ከነማንነቴ ከተቀበለኝ በሩ ክፍት ነዉ ካልሆነም አላህ የተሻለ ይሰጠኛል ብየ ሙሉ በሙሉ ሁሉ ነገሬን ለአሏህ ሰጠሁኝ...ይሄ የድንግልና ጉዳይ ሲነሳ ጉልበቴ የሚፍረከረከዉ እምባየ የሚፈሰዉ ለምንድን ነዉ?? ሰነፍ ደካማ መሆን የለብኝም እምነቴን ሙሉ በሙሉ ለአላህ መስጠት እንዳለብኝ እራሴን አሳመንኩኝ

    ሁሉን ነገር አየሁት ደስተኛ የምወደዉን አግብቼ ደስተኛ  ለመሆን ሞከርኩ አልተሳካም የብስ ስቃይ ይዞብኝ መጣ... ለሊት ቀን በቀን በመነሳት አልቅሼ ዱአየን አድርጌ ሁሉንም ሀጃየን ለአላህ ሰጠሁኝ

.....የእኔም የሚፍታህም ቤተሰቦች ሁለታችን እንድንጋባ ተጠይቆ እሺ ስለተባለ ..እኔ ደግሞ ሚፍታህ ከትዳር በፊት
እኔ በልጅነቴ ስለተደፈርኩ የዛ ጠባሳ ሳያንሰኝ በሚናገራቸዉ ቃላቶች  ልቤን እያደማዉ እያቆሰለዉ  ስለሆነ ...የጓደኞቼ ሚስቶች ቢክራ ናቸዉ ሚስቴ ቢክራ ካልሆነች በምላሹ እናቷ ቤት ነዉ የምልካት እያለ በተደጋጋሚ ስለነገረኝ ...ሚስት ብሎ እኔን ምርጫዉ አርጎኛል የእሱን መስፈርት ስለማላሟላ
ሚፍታህን አሳማኝም ሆነ የማያሳምን የተለያዩ ለፀብ ለቁርሾ የሚሆን ስበብ ፈልጌ አንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ልርቀዉ ወሰንኩኝ .........


#ክፍል
ይ.............ቀ............
.........ጥ............ላ..............ል


JOIN
´´´´´´´t.me/Islam_and_Science
t.me/Islam_and_Science
•════••• •••════•
1.4K viewsedited  06:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-22 09:14:31 አሳዛኝ እዉነተኛ ታሪክ
 
የታሪኩ ርዕስ
#የሆድ_ዉስጥ_ፉም_እሳት
      #ክፍል ☞ አስራ ሰባት

ፀሀፊ ☞ #አሚር_ሰይድ





ነዋል ከምሬ ነዉ አንቺን ማዉራት ከጀምርኩ ቡሀላ ወላሂ በልቤ ገብተሻል እወድሻለሁ አለኝ.....

 
እኔም የሰማሁትን ማመን አቃተኝ ... ተክዞ የተኛዉ ጆሮየ ቀጥ አለ....በጣም ደስ አለኝ የምሆነዉን አሳጣኝ...አቁነጠነጠኝ...መቼም በስልኩ ድምፅ ነዉ እንጂ የዛን ጊዜ ሚፍታህ ቢያየኝ ተገርሞም ስቆም አያበቃም ነበር ...ይሄን ደስታየን በግድ መዋጥ አለብኝ ሴት ነኝ እና ደስታየን መቆጣጠር አለብኝ
.....አረ ሚፍታህ አቀልድ አልኩት
...........ወላሂ ከምሬ ነዉ ነዋል ደግሞ ጊዜ መስጠት አልፈልግም ቶሎ ሀላሌ እንድትሆኝ ነዉ የምፈልገዉ፡፡ Coc ከተፈተንሽ ቡሀላ ቤተሰቦቼን ነግሬ ሽማግሌ እልካለሁ አለኝ፡፡
...........እኔም እሺ ልሰብበት ጊዜ ስጠኝ አልኩት..ብዙ ሴቶች እየወደድን ቶሎ እሺ ማለት ሴትን ልጅ ያስንቃል ብለን እናስባለን እየወደድኩም ቢሆን መግደርደር የሴትነት ወጉ ስለሆነ እኔም ልቤ እየፈለገ አፌ ልሰብበት የሚለዉን አስቀደምኩኝ ፡፡

ከ ከ3ቀን ቡሀላ ሚፍታህ ደዉሎልኝ የጠየኩሽን ጥያቄ ምን ወሰንሽ ??? ብሎ ጠየቀኝ
......እኔም እሺ ተስማማቻለሁ አልኩት
ሚፍታህ በጣምምም ተደሰተ በስልክ ደስታዉን ሊቆጣጠረዉ አልቻለም....የእኔም ደስታ ከሱ ቢበልጥ እንጂ አያንስም ...ይገርመኛል የኔዉ ሞኙ ልቤ ከካሊድና ከየሱፍ አስበልጦ ለሚፍታህ ትኩረት ሰጥቷል፡፡

ሚፍታህ ረመዷን ሲያበቃ ኢንሻ አላህ ለኢድ ጅማ መጥቼ በአካል እንገናኛለን አለኝ፡፡
.....እኔም ለሚፍታህ ለጠየቀኝ ጥያቄ መልሴ እሺ ብቻ ሁናል፡፡ ረመዷን ደረሰ ሚፍታህ ጋር ሁሌ ማታ ማታ እናወራለን ፡፡ ከማዉራታችን ብዛት አንዳንዴ ተራዊህ የማልሄድባቸዉ ቀናቶች ነበሩ...

ረመዷን አልቆ ኢድ ላይ ደርሰናል....ሚፍታህም ኢድን ቤተሰብ ጋር ለማክበር ከአዲስ አበባ ጅማ ተከስቷል.... ጅማ የኢድ ሶላት የምንሰግደዉ ጅማ ስታዲየም ነዉ.... ሰግደን ስንወጣ በስልክ ተደዋዉለን ለመጀመሪያ ጊዜ ሚፍታህ ጋር ተገናኘን . . እኔ እና ሚፍታህ ስንገናኝ ሁለት እህቶቹ ጋር አብሮ ነበር....አንዷ እህቱ የወንድሜ ሚስት ነዋል እንዴት ነሽ ብላ ሳመችኝ
.....እኔም ሚፍታህን እያየሁ በእህቱ ሁኔታ ተግባብተን ሳቅን
....ከመስገጃ ቦታዉ እየተመለስን ስለ አንዳንድ ነገሮች እያወራን ነዉ....ሚፍታህም እንዲህ አለኝ ፡- ነዋል ሁሉንም ቤተሰቦቼን እናቴም አባቴም እህቶቼም አንቺን እንደማገባ እቤት አሳዉቂያለሁ አለኝ ...
....ግን እናቴ አንቺን እንዳገባ አልተስማማችም አለኝ
.......እንዴት ላትስማማ ቻለች ??አልኩት
...........ነዋል እኮ ከ10ኛ ክፍል ቡሀላ አድጋ ነዉ እንጂ ገና ልጅ ናት ...አለችኝ አለኝ
...... እና ምን አልካት ??? አልኩት
............ነዋል ነዉ ማግባት የምፈልገዉ አሁን ትልቅ ሰዉ ሁናለች ቁመት ብጨምርም አብራ አስተሳሰብ ጨምራለች የትናንቷ ልጅ አይደለችም ብየ አሳኳት አለኝ
.......እናቴም፡- እሺ አንተ የወደድከዉን እኔም እወዳለሁ ብላ በኔ ሀሳብ ተስማማች አለኝ
እንደዚህ እየተጨዋወትን በደስታ ሁለታችንም በወሬ ፍንክንክ ብለን እኔን እቤቴ ሸኝቶኝ እሱም ወደ ቤቱ ተመለሰ፡፡
 
በዚሁ በኢድ ቀን የሚፍታህ እናት እና አባት የኔን ቤተሰቦች ሊዘይሩ እኛ ቤት መጡ፡፡
ከበፊትም ጀምሮ የእኔ ቤተሰቦች እና የሚፍታህ ቤተሰቦች በጣም ይግባባሉ፡፡ በተለይ ደግሞ የኔ አባት እና ኡስታዝ(የሚፍታህ አባት)በጣም ይቀራረቡ  ይዋደዳሉ፡፡ አባቴ የሆነ ሀሳብ ሲይዘዉ..ግራ የሚያጋባ ጉዳዮች ሲገጥሙት የሚፍታህን አባት ብዙ ጊዜ ሲያማክር አስታዉሳለሁ፡፡

ሚፍታህ ቀን በቀን በደወለ ቁጥር ይቼ ቃላት ምላሱ ላይ አብራ የተሰፋች ነዉ የሚመስለዉ ... #እወድሻለሁ_አፈቅርሻለሁ ሳይለኝ ዉሎ አድሮ አያቅም ...እኔም ይሄን ቃል ስሰማ ደስታኛ እንደሆንኩ ይሰማኛል... አሁን ዘመን ላይ ፍቅርን በአፋችን ስንገለፀዉ ለምላስ የብናኝ ያህል ክብደት አይኖረዉም ..እዉነተኛ ፍቅር ግን ማን ነዉ መግለፅ የሚችለዉ?? ስለፍቅር ምን በአንተ አስተሳሰብ ግለፅ ብላችሁ መቶ ሰዉ ብትጠይቅ የመቶዉም ሰዉ ስለፍቅር ያለዉ አመለካከት የተለያየ ነዉ ...ግን ለምን ይሆን በብዙ ሰዉ ልብ ያለን ፍቅር ቃላት ለመግለፅ የማይችለዉና ..ቃላቱ ሶስት ቃላት ናቸዉ #ፍቅር ግን ስለፍቅር ምን ትላለህ ሲባል ፍቅርን በቃላት መግለፅ አልችልም ሲሉ ይደመጣሉ..አንዳንድ ሙሁር ተብየዎች..ገጣሚዎች..ዘፋኞች ..ፍቅርን በማይታይ ህልም ሲስሉት እናስተዉላለን..ግማሹ የሰዉነቷን ክፍል ቆራርጠዉ አይኗ ከዋክብት..ጥርሷ ነጭ በረዶ ..ሷቋ የፀሀይ ጮራ ቁመቷን ተራራ..አፍንጫዋን ጥሩ መአዛ ብቻ የሚቀበል መጥፎ ሽታን የሚያስወግድ ..ችቧ አይሞላም ወገቧ ማር እሸት ነዉ ቀለቧ እየተባለ ..ወዘተ ብለዉ ሲጠቆሱት እያየን ነዉ...ግን ይሄ አገላለፅ ፍቅርን ይገልፀዋል ወይ??

★★★አንዳንድ ሠዉ ስለ ሌላ ሰዉ በዚህ ፍቅር ተብየዉ እየተጨነቀ ያስብና እየተቆጨ ይኖራል..በእርግጥም ሌላ ሠዉ መልካምን ለማድርግና ችግሩን ለማቅለል መጨነቅ ማሰብና መቆጨት መልካም ነዉ.
.
.
ማፍቅር መልካም ነገር ነዉ* አላህ በሰዎች መካከል የሚስቀምጠዉ ደስታን፣እርካታን የሚያጣጥሙት የሂወት ቅመም ነዉ ይህ ፍቅር ግን ያለቦታዉ ገብቶ የማይዋልበት ቦታ ሲገባ ስቃይና መከራ ይሆናል.
..
ከመፍትሄ ይልቅ ችግር ከእረፍት፣ ይልቅ ስቃይ ፣ከደስታ ይልቅ ሀዘንን ያበዛል .በተለይ በልጅነት ሂወት ላይ ሲከሰት መካራዉ ይደራረባል ሂወት አጭር ናት ከትደሰትክባት በሚል የተሳሳተ ተስፋ አጭሯን ሂወት ለስቃይና ለመከራ የሚያደርግ ስስት ዉስጥ ይገባል .
"
"
በጓደኛም ይሁን በአይን ስህተት* በጅንጀናም ይሁን በዉሸት ፍቅር የያዛቸዉ ይህንን ፍቅር የሚሉትን ስሜት ለማስታገስና ለማከም የማይገባዉ ጉድጓድ ዉስጥ ይገባሉ .ለመዉጣት ደግሞ መዉጫ ቀዳዳ ይጠፋል ..

:
ለማናዉቃቸዉና ለማንተማመንባቸዉ ጊዜ አዊይ ስሜቶች የማናዉቀዉን የማንተማመንበት ጣፋጭ ሂወት እናበላሻለን ከሸይጧን ግፊት ለሚደረግበት ስህተት ፍቅር በሚል ሽንገላ ከአላህ ሽልማት የሚጠበቀዉን እድል እናፈርሳለን...ግን ለዚህ ሁሉ መፍትሄዉ ፍቅርን በሰዎች ሁሉ ለሰጠዉ ፈጣሪ አመስግኖ መጀመሪያ ፍቅርን ለሰጠን ፈጣሪ ፍቅሩን ለፈጣሪ ከሰጠነዉ ሁላችንም አሸናፊዎች ነን፡፡ ፍቅርን ሳናባክን መጀመሪያ የሰጠንን ፈጣሪ አንርሳ ለምን የሰጠንን ነገር ሁሉም የሚቀመጠዉ በሂደት ነዉ...
መጀመሪያ ማስቀመጥ ያለብን ለፈጣሪ መሆን ሲገባዉ ነገር ግን ይሄን የመጀመሪያ እድል ለፍጡር ከተደረገ የፈጠረህን ፈጣሪ ሀቅ አጉድልሀል ..ባለቤቱ አምጥቶ አደራ ብሎ አስቀምጦ የሄደዉን ለሌላ ለማያገባዉ ከሰጠን ጥፋቱ አደራዉን የካደዉ ነዉ ...አደራችንን የሰጠንን ፈጣሪ እያስታወስን እናስቀምጥ፡፡ የዛን ጊዜ እኛ በፈጣሪ እገዛ አሸናፊዎች ነን፡፡

      ከኢድ ቀን ቢያነስ ከ15 ቀናት ቡሀላ የሚፍታህ አባት እንደ ሽምግልና ባይሆንም የአባቴን ሀሳቡን መረዳት ያክል እሳቸዉ እና የሚፍታህ አጎት ሁነዉ አባቴ እቤት ባለበት ሰአት መጡ....

ለአባቴ -------እኔና ሚፍታህ በአንድ ጎጆ ለመኖር መጨረሳችንን ሁሉንም ነግረዉት ግን የአንተ ፍቃደኝነት ያስፈልጋል .... ሚፍታህ ልጅህን ነዋልን ማግባት ይፈልጋል ፍቃደኛ ነህ ወይ ??? ብለዉ ጠየቁት
1.4K viewsedited  06:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-21 09:05:58 ሚፍታህ አላማዉ እኔን ማዉራት የጀመረዉ ለየሱፍ እኔን ድሮኝ ...እኔ ደግሞ ብዙ ጓደኞች ስላሉኝ ከእነሱ መካከል አንዷን እኔዉ መርጬ እንድድረዉ ይመስለኛል ......ወይም አይታወቅም የሰዉ አስተሳሰቡ በየሱፍ አሳቦ እኔን የሱ ማረግ ፈልጎም ሊሆን ይችላል.....
  በመነገታዉ ሚፍታህ ደዉሎልኝ ለየሱፍ ነዋል አልተስማማችም ከአቅሜ በላይ ነዉ ብየ በስልክ ነግሬዋለሁ አለኝ.... ነገር ግን እኔና ሚፍታህ አሁንም ማዉራት አላቆምንም...እንደዉም ከበፊቱ በባሰ መልኩ እያወራን ነዉ፡፡

   ደግሞ በተዘዋዋሪ ካሊድ  ከኔ ተስፋ አልቆረጠም ሁሌም ጅንጀና አይሆንለትም....ካሊድ ግልፁን እንደሚወደኝ እና ለወደፊት እኔን ማግባት እንደሚፈልግ ይነግረኛል....ሁሌም ጁምአ እየደወለ ነዋል ተረጂኝ እኔ ጅንጀና አይሆንልኝም  .... ነዋል አንድ ጥያቄ መልሽልኝ ምን አይነት ባል ነዉ የምፈልገዉ ??? አለኝ

.......እኔም ብዙ ሴቶች ሲጠየቁ የሚመልሱትን መልስ መለስኩለት_እኔ የምፈልገዉማ የተማረ ዲን ያለዉ ኪታብ የቀራ ከምንም በላይ  የሚወደኝ የምወደዉ የሚሳሳልኝ ልጅ ወልደን በፍቅር አብረን መኖር የምንችል እና ""እስከ ማንነቴ የሚቀበለኝ"" አልኩት....
.....ካሊድም:- ነዋል አንድ ነገር ልታዉቂ እፈልጋለሁ >>>>>አንቺ የሆንሽዉን ብትሆኝ ሁለት ጊዜ ባል አግብተሽ ብፈቺ አምስት ልጅ ቢኖርሽ ለኔ ምንም አይደል...እኔ የምፈልገዉ አንቺ የኔ እንድትሆኝ ብቻ ነዉ የምፈልገዉ<<<<<< አለኝ
....ካሊድ እኔን ከማንነቴ የሚቀበለኝ ይመስለኛል...ነገር ግን በጭራሽ ዉስጤ ሊቀበለዉ አልቻለም .....ከካሊድ ጋር ከብዙ ንትርክ ቡሀላ  ከእኔ ተስፋ አልቆርጥ ሲል በዉሸት እኔ የዉጭ ሀገር ፕሮሰስ ጀምሪያለሁ አሁን ማግባት አልችልም ብየ በዉሸት ተስፋ አስቆረጥኩት....
....ካሊድም ሳይወድ በግዱ እሺ አለኝ ግን ያዉ ስለትዳር ባናወራም ጁምአ ጁምአ ይደዉልልኛል

በተዘዋዋሪ ደግሞ ሚፍታህ ጋር ሳወራ ደስታየ ነዉ ምነዉ እወድሻለሁ ላግባሽ ባለኝ እያልኩ እነዚህን ቃላቶች ቢነግረኝ ምኞቴ ነዉ
እንደዚህ እያለ የኮሌጅ አንደኛ አመት እና ክረምቱም በዚሁ  አለፈ ....ሁለተኛ አመት የኮሌጅ ትምህርት ጀመርን አሁንም ከአህመድ ጋር እያወራን ነዉ፡፡

አንድ ቀን እንዲህ አለኝ...>>>>ነዋል ማግባት እፈልጋለሁ የአሁኑ አመት ላይ የመጀመሪያ እቅዴ ማግባት ነዉ ለኔ የምትሆነዉን ምረጭልኝ<<<<አለኝ
......እኔም ምን አይነት ሴት ነዉ የምፈልገዉ ?? ከጓደኞቼ በመስፈርትህ መሰረት መርጬ ፎቶ እና ስልኳን ልኬልህ ከተግባባችሁ ትጋባላችሁ ግን መስፈርትህ ምንድን ነዉ?? አልኩት

.....እሱም እሺ መስፈርቴ ቁመቷ ልክ እንደ አንቺ.. መልኳ ልክ እንደ አንቺ.. የትምህርት ደረጃዋ. ዲኗ እድሜዋ..ልክ እንደ አንቺ ሁሉ ነገሯ ልክ እንደ አንቺ አለኝ፡፡
ግን ልክ እንደ አንቺ ማለቱ ምን ማለቱ ነዉ .......,,እኔም ሚፍታህን እየወደድኩት እሱን ማጣት ሳልፈልግ ሂጄ መፍቱሀን ለሚፍታህ ልዳርሽ አልኳት
......መፍቱሀም እኔ አልፈልግም አለችኝ...እሷም እኔ እንደምወደዉ ከአነጋገሬ ከሁኔታየ ተረድታኛለች ግን ነዋል ለምን ሚስት ፈልጊልኝ ከሚልሽ ለምን አንቺን አያገባሽም ??? እንዲህ የሚልሽ አንቺ አግባኝ እንድትይዉ...የአንቺን  ቃልሽን እየጠበቀ ይሆናል አለችኝ....
ወደዳችሁም ጠላችሁም ሚፍታህ በስልክ በተደጋጋሚም ስለምናወራ ልቤ ተሰርቋል አጉል መቀራረብ ፍቅር የሚባል ጦስ ይዞ ይመጣል..

የበፊት ያለፉት ምርጥ ትዉልዶች ፍቅርን እንዴት ነበር የገለፁት እስኪ ከዚህ የንጉስ የፍቅር አገላለፅ እንመልከት
★★★ ሕንድን የከፈተዉ ሱልጣን ጋዛሊን ማህሙድ በጣም ተወዳጅ የሆነ አገልጋይ ነበረዉ...ስሙ ሙሀሙድ ይባላል ሱልጣን ማህሙድ አገልጋዩን የሚጠራዉ ሙሀመድ በሚለዉ መጠሪያዉ ሲሆን አንድ ቀን ግን በአባቱ ስም ጠራዉ
..በዚህ የሱልጣኑ ድርጊት ልቡ የተሰበረዉ አገልጋዩ ሱልጣኑ ለምን በአባቱ ስም እንደጠራዉ ሲጠይቀዉ
>>>>>>>>የምወድህ ልጄ!! ሁልጊዜም በስምህ ስጠራህ ነዉ የኖርኩት .. #በእነዚህ_ጊዚያት_ሁሉ_ዉዱዕ_እያለኝ_ነበር የጠራሁህ...ሆኖም ግን አሁን በአባትህ ስም በጠራሁህ ቅፅበት ዉዱዕ አልነበረኝም..ዉዱዕ ሳላደርግ ይሄን የተባረከ ስም ሙሀመድን መጥራት ስላሳፈረኝ ነዉ በአባትህ ስም የጠራሁህ በማለት ይቅርታ ጠየቀዉ፡፡


ይሄን ያህል ለተወዳጁ ነብዩ ሙሀመድ ሰ.ዐ.ወ ፍቅር ነበራቸዉ ዉዱእ ሳይኖራቸዉ የተከበረ ስማቸዉን ለመጥራት ለራሱ ይሄን ያህል ፍቅራቸዉ በልባቸዉ ገብቶ ያከብራቸዉ ይወዳቸዉ ነበር...ዛሬ ግን ስማቸዉን በቀላሉ አንስተን ከልብ ባልመነጨ ፍቅር በነሽዳ በተራ ሙነሺዶች ...በተራ የሰርግ ነሽዳ አድማቂ ተብየ ወጣቶች በዱአዉ በነሽዳዉ ሙሀመድ ነብየ ስንል እንዉላለን ሁሉም ከአንገት በላይ ነዉ..እስኪ እራሳችንን እንፈትሽ የነብዩን ልጆች ሁሉንም በቃላችን ሸምድደናል??ነብዩ በስንት አመታቸዉ ነዉ ነብይ የሆኑት??የነብዩ ሚስቶች ጥቀሱ ብትባሉ ስንቱን መጥቀስ እንችላለን?? ከነብዩ ምርጥ ሱሀቦች ስንት እናዉቃለን?? በስንት አመተ ሂጅራ ተወለዱ ?? ወዘተ የተለያዩ ጥያቄዎችን እራሳችንን እንፈትሽ፡፡ አሁን ላይ ገና እንቦቅላ ወጣት ተነስቶ ነሽዳ አወጣሁ ብሎ ሙሀመድ ነብየ ሲል ይስታወላል..ሰዉ በተዉሂድ መተናፅ ሲገበረዉ ሙነሺድ ተብየዎች ሰዉን ለማዘናጋት በቃል ብቻ የቀረ ከሆድ ያልገባ ዉዴታ ነቢይ ነቢይ እወድወታለሁ እያሉ ነሽዳ ሲያወጡ አብረዉ ሽርካ ሽርኩን ጨምረዉ ህዝቡን በጭፍን ሲመሩት እያየን ነዉ ...ግን የነብዩ ዉዴታ ይሄ ነዉ?? በፊት የነበሩ ምርጥ ትዉልዶች ግን ሙሀመድ የሚለዉን ስም ዉዱዕ ሳይኖራቸዉ ለመጥራት ይከብዳቸዉ ነበር እኛ ግን አብሮ ቂጣ እንደበላ ጓደኛ ስማቸዉን ስናነሳ እንደ ጩጫን እንኳ ክብደት አልቆጠርንም ...??እኛ ዉዴታን የምንገልፀዉ የማይጠቅም ግን ብዙ የሚጎዳ ነሽዳ እያዳመጡ አብሮ ሙሀመድ ነብየ ማለት ነዉ ?? ዉዴታ በነሽዳ ነዉ የሚገለፀዉ ??
ነብዩ ሙሀመድ ሰዐወ እኔን የሚወደኝ የሰራሁትን ስራ ይከተል ብለዋል...ዉዴታ የሚገለፀዉ እሳቸዉ የሰሩትን ስራ በመስራት ነዉ... መቼ ነዉ ሁላችንም ከኔ ጀምሮ ተዉሂድ ለመማር ፍቃደኛ የምንሆነዉ??ተዉሂድን ተምረን ትክክለኛ የእሳቸዉን መንገድ ተከትለን የእሳቸዉን መዉደዳችን የምናረጋግጠዉ?? ሁሉም መልሱን በልቡ ይመልስ....
   

ሚፍታህ ጋር  ማዉራቱን ተያይዘንዋል.... ረመዷን ደርሷል ፡፡ በዛዉም coc ፈተና ስለነበረኝ እየተዘጋጀሁ ነዉ፡፡

በጊዜ ሒደት አንድ ቀን እንዲህ አለኝ ነዋል ለየሱፍ ቢያወራሽ በጭራሽ እንዳነግሪዉ አደራ :-እኔ ለየሱፍ ልድርሽ ነበር ያሰብኩት .... ምርጫሽ እሱ ካልሆነ ካልፈለግሽዉ እኔ ላገባሽ እፈልጋለሁ ነዋል ወላሂ ከምሬ ነዉ አንቺን ማዉራት ከጀምርኩ ቡሀላ ወላሂ በልቤ ገብተሻል እወድሻለሁ አለኝ.....

 
#ክፍል
ይ...........ቀ............
.......ጥ...........ላ..........ል

Join
t.me/IslamisUniverstiy_public_group
  t.me/IslamisUniverstiy_public_group
1.8K views06:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-21 09:05:58 አሳዛኝ እዉነተኛ ታሪክ
 
የታሪኩ ርዕስ
#የሆድ_ዉስጥ_ፉም_እሳት
      #ክፍል ☞ አስራ ስድስት

ፀሀፊ ☞ #አሚር_ሰይድ




ገና በመጀመሪያ በደወለልኝ ቀን የሆነ መግለፅ የማልችለዉ ብዥታ አእምሮየን አናወዘዉ...ይገርማል


ማታም ልተኛ ስል ደወለልኝ እያወራን ነዉ........ቀን በቀን ቀን ማታም መደዋወሉን ከሚፍታህ ጋር ተያይዘንዋል ለምን በፊት ስለምንግባባ ለማዉራት እሱም እኔም አንፈራራም ፡፡ በቀላሉ እንደ ሴት ጓደኛ እንደምናወራዉ ያህል የእኔ እና የሚፍታህ ቅርርብ ወሬ እንደዛ ሆነ.........

አንዴ በስልክ እያወራን ነዋል ትልቅ ሰዉ ሁነሻል አሉ ፎቶሽን አሳይተዉኝ እኔ የማቅሽ ልጅ እንደነበርሽ ስለሆነ ነዋል አይደለችም እስከማለት ደርሼ ነበር በግድ አመንኩኝ... የሇላዉ መጣ እና የፊቱን ቀደመዉ እኛ እናሳድጋለን በቃ እናንተ ግን ያሳደጋችሁን ትረሳላችሁ ብሎ አሳቀኝ
...,ኪታብ ምን እንደምቀራ ጠየቀኝ ነገርኩት
....,እሱን ስጠይቀዉ አዲስ አበባ ነዉ የምኖረዉ ፡፡
ትምህርትም የተማርኩት አዲስ አበባ አዉልያ ኢስላማዊ ትምህርት ቤት እና ቁርአን የሀፈዝኩትም አዲስ አበባ ነዉ፡፡ አሁን የምሰራዉ ከቻይና ከዱባይ እቃ እያመጣሁ አዲስ አበባ ማከፋፈል ነዉ አስመጭ እና ላኪ ሁኜልሻለሁ አለኝ፡፡ ...አልሀምዱሊላህ ሒወት መስመር ይዛልኛለች ግን አንድ ነገር ብቻ ጎዶሎ ሁኖብኝ ያለኝ ብር ንብረት ደስታ አልሰጠኝም ጎዶሎ እንደሆንኩ ይሰማኛል አለኝ
.......እኔም ምንድን ነዉ የጎደለህ?? አልኩት
.........,እሱም ትዳር የለኝም ማግባት እፈልጋለሁ ...ደግሞ የማገባዉ.አንቺ የመረጥሽልኝ ከጀመአ ልጆች  ነዉ የምፈልገዉ ፈልጊልኝ  አለኝ
.....እኔም አብሽር ጣጣ የለም አንድ ላይ ሁነን እንፈልጋለን አልኩት፡፡
ግን ትዳር በፍለጋ ይገኝ ሁን ?ትዳር ቀልድ ነዉን?በኔ ፍለጋና በሚፍታህ ሀሳብ ይሳካ ይሆን?ለምን ትዳር በባህሪዉ መረጋጋት ትዕግስት ቆም ብሎ ማሰብ ያስፈልጋል፡፡
★★★ትዳር በባህሪው ትግዕስትን ይፈልጋል ኢማንና ፍቅርን አላማቸው አድርገው ባንድላይ ለመሆን የወሰኑ ሰዎች መደማመጥን ሀሳብን መቀባበል ካልቻሉ በዘመናችን ከእሾህ እንደተጠጋ ቁልቋል ሲያለቅሱና ሲያማርሩ እንዲሁም ደስታና ሰላም የሸሸው ህይወትን ሲገፉ ይኖራሉ።

   ዛሬ ዛሬ አያሌ የዘመኑ ወጣቶች ትዳርን አስበውበትና ወስነው ሳይሆን በዘፈቀደ ለጊዜያዊ ስሜት ብለው የሚገቡበት መሆኑ በጉልህ የሚታይ ነው ጋብቻ እርቆ ማሰብና ማሰላሰልን ብሎም መወሰንን ይጠይቃል።

ይሁንና ጋብቻ ሲጀመር ብዙ ውጣ ውረድ እንዳለው የሚዘነጉ ቀደም ብሎው ያላሰቡበት አንዳንዶች ገና ከጅምሩ በጋብቻቸው የተደላደለ ኑሮን ለመኖር ይፈልጋሉ፡፡ የትዳርን ትክክለኛ ገፅታ ማየት ተስኗቸው ትዳርን በየዋህነት የሚጀምሩ ሰዎች ትዳር እንዳሰቡት ሳይሆን ሲቀር ያለው አማራጭ የያዘውን ትቶ ሌላ ለመሞከር እንድ ሁለት ማለት ይሆናል ፡፡በመሆኑም ፍቅርንና ኢማንን አላማቸው አድርገው በትዳር ተሳስረው ለመኖር የወሰኑ ሰዎች በሰርጋቸው ማግስት ወይም በቀጣዩ የትዳር ህይወታቸው ውስጥ ግራ የሚያጋቡና ተስፋ የሚያስቆርጡ የስሜት አለመጣጣም የፋላጉት አለመርካት የአመለካከትና የልምድ ማነስ ልዩነቶች የሚታይበት ሊሆን ይችላል።

#ይሁን_እንጂ ትዳራቸውን እንደ አላህ ፍላጎትና ትዕዛዝ የጀመሩ ከመሆናቸው የተነሳ ለጊዜያዊ ችግር ብለው ወደ ፍቺ (ትዳርማፍረስ) አይሮጡም፡፡ ከዚህ ይልቅ ለገጠማቸው ችግር አላህ ሱበሀን ወተአላ ከልብ እየተማፀኑና የተፈጠረውን ችግር ለመቅረፍ አብረው ይሞክራሉ .... አንዱ የሌላውን ሃሳብ ለመቀበልና የታየውን ድክመት በይቅርታ ለማለፍ ፍቃደኞች ይሆናሉ። ይህም ትዳራቸው አስደሳች ህይወትና ረጅም ዕድሜ እንዲኖረው ለማድረግ ከማንም የተሻለ ዕድል ይሰጣቸዋል። ጋብቻ የተከበረ የህብረተሰብ የመጀመሪያ ተቋም እንደመሆኑ መጠን

ይህ ተቋም ያማረና የተስተካከለ እንዲሆን የአላህ
እዳርታ የግድ ስለሚሆን አላህ ሱበሀን ወተዓላ መለመንና መማፀን ያፈልጋል።አላህም በቁርአኑ ይህን አስመልክቶ እንዲህ ይላል

«ጌታችን ሆይ! ከሚስቶቻችንና ከዘሮቻችን ለዓይኖች መርጊያን ለእኛ ስጠን፡፡ አላህን ለሚፈሩትም መሪ አድርገን» የሚሉት ናቸው፡፡

በዚህ መልኩ የትዳር ህይወትን ከጀመሩ በኋላ ስለአንድነታቸውና ፍቅራቸው በጋራ ዱዓ በማድረግ መትጋት ይኖርባቸዋል ስለትዳራቸው በግልፅና በታማኝነት አብሮ መወያየትና መነጋገር ከቻሉ ዓላማቸው የሚሰምር መሆኑን ተስፋ እናደርጋለን የሚያጋጥሟቸው ችግሮችም በአላህ ሱበሀን ወተዓላ ፊቃድ ይወገዳሉ። ፈጣሪ ሚፍታህ ያሰበዉን አይነት ትዳር ለኔም የተፃፈልኝን አሳካልን ብየ በዱአ ተያይዣለሁ ፈጣሪ ይገዝሽ በሉኝ


      ሚፍታህ ከበፊቱ በበለጠ እያወራን ነዉ ማርሽ መጨመር እንጂ መቀነስ አይታሰብም ፡፡
ሚፍታህን ዲነኛ አዋቂ አድርጌ ነዉ የማስበዉ..ለምን ቁርአን ሀፊዝ ነዉ በተጨማሪም አዉልያ ኢስላማዊ ትምህርት ቤት ነዉ የተማረዉ በቂርአቱም በዲኑም በትምህርቱም ጎበዝ ስለሆነ ምነዉ ለኔ በሆነ ብየ ተመኘሁ፡፡፡

አንድ ቀን ሚፍታህ እንደዚህ አለኝ የአንቺን ስልክ ቁጥር የሰጠኝ የሱፍ ነዉ ነዋልን አዉራልኝ ብሎኝ ነዉ አለኝ...
.....እንዴ የሱፍ ጋር ትግባባላችሁ እንዴ ??? አልኩት
......,እሱም አዎ አንድ ነገር ልንገርሽ እኔ አንቺን የማወራሽ የሱፍን በfb አላወራዉ ስላልሽዉ ነዉ በጣም ነዉ የሚወድሽ ሁሌም ስንደዋወል ነዋል እወዳታለሁ እባክህ አንተ የኡስታዝ ልጅ ስለሆንክ፡በፊት ትግባባላችሁ ....አሁንም አንተ የምትላትን ስለምትሰማ በዛ በዚህ ብለህ አሳምንልኝ ብሎ ስልክሽን ሰጥቶኝ ነዉ አለኝ......
.......ጉድ ነዉ በጣም አጀበኝ ...የሱፍ ማለት እዚሁ ጂማ የሚኖር ጎረቤታችን ነዉ፡፡ የሱፍ ብዙ ጊዜ Facebook ላይ ያወራኛል እኔ ግን ከ10ክፍል ቡሀላ fb ላይ ማዉራት አይመቸኝም.... እሱ ቢያወራኝም ለማዉራት ቢፈልግም እኔ ግን አላወራዉም ፡፡

የሱፍ የሰራዉ ስራ በጣም አናደደደኝ እኔን ከፈለገኝ እኔን ከወደደኝ እኔን ማግባት ከፈለገ ፍቅር እና ትዳር ሰዉ የሚገባበት ወይ እኔ እምቢ ስል ነዉ እንጂ የሱፍ እኔን ማግባት እየፈለገ እንዴት ለሚፍታህ ነዋልን የወደፊት ሚስቴ እንድትሆን አመቻችልኝ ይላል ???? በጭራሽ የማይደረግ ነዉ የሰዉ ልጅ መጀመሪያ ግልፁን መናገር ነዉ እንጂ በታዋቂ ሰዉ ወይም በታዋቂ ሰዉ ልጅ እንደዚህ አይነት ስራ መስራቱ በእኔ አስተሳሰብ የወረደ እና በጣም የሚያሳፍር አስተሳሰብ ነዉ፡፡
እኔም ያወራኝ ለራሱ አለመሆኑን ሳዉቅ ከሚፍታህ ተስፋ ቆረኩ ....እኔም አሁን ላይ አላገባም መማር ነዉ የምፈልገዉ....  እናም አደራ የሱፍን እንደማልፈልገዉ መቼም እንደማላገባዉ ከኔ ተስፋ እንዲቆርጥ ንገረዉ አልኩት፡፡
....ሚፍታህም እሺ ካልፈለግሽ እምቢ ብላለች አልተሳካም ብየ እነግረዋለሁ አለኝ፡፡

ሚፍታህ ለሌላ ልዳርሽ ከሚለኝ እኔ ላግባሽ ቢለኝ በጣም ደስ ይለኝ ነበር....ምን ይደረጋል ነበር ሁኖ ቀረ፡፡ አንድ ነገር ይገርመኛል ሴት ልጅ የምትወደዉን ስትከተል የሚወዳትን ታጣለች ይባላል ካሊድ ላግባሽ ብሎ ስንት እንዳለመነኝ እኔም እምቢ እንዳላልኩኝ ..ግን ሚፍታህ ገና ለወደፊቱ ላግባሽ ቢለኝ ደስታየ ነዉ ምንም ሳላቅማማ ለመቀበል ዝግጁ ነኝ
1.4K viewsedited  06:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-20 08:22:14 ካሊድ ለሰልዋ እኔን እንደሚወደኝ ለወሬ ለጅንጀና ሳይሆን ቀጥታ ሽማግሌ ልኬ ማግባት ነዉ የምፈልገዉ ብሎ ነግሯታል
....ሰልዋ እኔን ስጠይቀኝ እኔ አሁን ማግባት አልፈልግም ቤተሰብም እንድማር ነዉ የሚፈልጉት አልኳት
........ከአሁን በፊት ካሊድ ብዙ ቀን ለሰልዋ እና ለመፍቱሀ እኔን እንደሚወደኝ ነግሯቸዋል፡፡ ካሊድ እኔን ለማዉራት በጣም ይፈራኛል ..ስለእኔ ጉዳይ የሚጠይቃቸዉ ሰልዋን እና መፍቱሀን ነዉ፡፡ለትዳር ዝግጁ ከሆነች እኔን ማግባት ምርጫዋ ከሆነ ዛሬ ነገ ሳልል ሽማግሌ ልኬ ለማግባት ነዉ አላማየ እያለ ሁሌ ይነግራቸዋል፡፡

ካሊድን ባንግባባም አቀዋለሁ ባጃጅ አለዉ በኛ አካባቢ መስመር ነዉ የሚሰራዉ ፡፡ ግን በእሱ ባጃጅ ስሄድ ትኩር ብሎ ያየኛል
......ሰልዋ ቀን በቀን ካሊድን ምን አሰብሽ?? አግቢዉ እያለች ስትጠይቀኝ ካሊድ ከኔ ተስፋ እንዲቆርጥ ብየ.....ማግባት አልፈልግም ስለዚህ ጉዳይ ሁለተኛ እንዳታነሺ አልኳት

እሺ ነዋል ግን ስልክ ቁጥሯን ስጭኝ ብሎኛል እሰጠዋለሁኝ አለችኝ
....እኔም እሺ ስጭዉ የተለየ ነገር ግን አይፈጠርም አልኳት

ካሊድ ጋር የምናወራዉ በTelegram ነዉ በስልክ እኔን ለማዉራት ድምፄን ለመስማት ይፈራል
በTelegram እያወራን እኔን ማግባት እንደሚፈልግ በግልፅ ነገረኝ
........እኔም ካሊድ ተረዳኝ አሁን ማግባት አልፈልግም ትምህርቴን መማር ነዉ የምፈልገዉ ከአሁን ቡሀላ ስለትዳር እንዳታነሳብኝ ብየ ተቆጣሁት
.....ነዋል ትምህርት እኮ ከትዳር አይከለክልም አለኝ
....,ከዛ በቃ አልፈልግም ተወኝ ብየ ከtelegram ወጣሁኝ፡፡ ተነስቼ ዉዱእ አድርጌ ሶላተል ኢስቲሀራ ሰገድኩኝ ..ልክ እንደሰገድኩኝ ልቤን እፍን አደረገኝ መረጋጋት አልቻልኩም...,ወዳዉ ለካሊድ በmessage መልዕክት ላኩለት

መልዕክቱም እንዲህ ብየ ነበር የላኩለት
"""""ካሊድ ሶላተል ኢስቲሀራ ስሰግድ ልቤን አፈነኝ የሰላም ስሜት አልተሰማኝም  ስለዚህ ተረዳኝ እኔ በጭሬሽ አንተን ላገባህ አልቾልም የትዳር ምርጫየም አይደለህም አልፈልግህም""""" አልኩት
......ካሊድም የላኩለትን message አይቶት---- መልሶ እንደዚህ ብሎ ላከልኝ-------ነዋል አብሽሪ አንቺን እየጀነጀንኩሽ አይደለም ደግሞም በኔ የተነሳ እንድትጨናነቂ እንድታስቢ አልፈልግም  ፡፡ ባይሆን አንድ ነገር ብቻ ፍቀጅልኝ በሳምንት አንድ ቀን ለሰላምታ ስደዉልልሽ አንስተሽ ፈታ ብለሽ አዉሪኝ መንገድም ላይ ስንገናኝ ሰላምታ ሳቀርብልሽ ፊት እንዳነሽኝ አናግሪኝ አለኝ
....,,እኔም እሺ በዚህ እስማማለሁ አልኩት

ከካሊድ ጋር በTelegram ማዉራት ቀነስን ሁሌ በሳምንት ጁምአ ጁምአ 8:00 ሰአት ሲል ሁሌ ይደዉልልኛል ፡...ከዛም እንዴት ነሽ ቤተሰብ ሰላምናቸዉ ??ጁምአ እንዴት ነበር ?? ትምህርት እንዴት ነዉ ?? ሳምንቱ እንዴት አለፈ ብሎ ይጠይቀኛል...
....,አጠር አጠር አድርጌ እመልስለታለሁ ከ10ደቂቃ የበለጠ ሳናወራ በአጭሩ ቶሎ ወሬያችንን እንጨርሳለን ፡፡ ሁሌ ጁምአ Alarm የቀጠረ ይመስለኛል 8:00 ሲል ይደዉልልኛል ከዚህ ዉጭ ከካሊድ ጋር ሌላ በስልክ ቅርርብ የለንም

  አንድ ቀን ክላስ በነበርኩበት  ቲወሪ የተማርነዉን ፕራክቲክ የምንሰራበት የምናይበት ክፍል(Dimonstration class) ሁኜ በፕራክቲክ እየተማርን .....የማለቀዉ ስልክ ቁጥር ተደወለ
.....,እኔም ማንሳት ስላልተመቸኝ ማንሳቱን ተዉኩት
..........አሁንም በድጋሜ ተደወለልኝ ፡፡ አሁን ድረስ የሚገርመኝ ስልኩ ሲደወል ጭንቅ ጥብብ አለኝ ሳየዉ ስልኩ አስፈራኝ....ይሄ የማላቀዉ ቁጥር ማን ይሆን ????
.... እየተደወለ ሲደጋገም መምህሬን አስፈቅጄ ወደ ዉጭ ወጥቼ ስልኩን አነሳሁት........



ነዋል አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱሏሂ ወበረካትሁ አለኝ
...እኔም ወአለይኩም ሰላም ወራህመቷሏሂ ወበረካትሁ አልኩት
....ሰላም ነሽ እንዴት ነሽ ነዋል?? አለኝ
........አልሀምዱሊላህ
......አወቅሽኝ ??? አለኝ
....እኔም አረ አላወኩህም ማን ልበል ??
......እሱም እርግጠኛ ነሽ አላወቅሽኝም ??ይሄን ድምፄን አስታዉሺ አለኝ
......እኔም በጭራሽ ይሄን ድምፅ ላስታዉሰዉ አልቻልኩም
.....እሱም እርግጠኛ ነሽ ??
..........እኔም አዎ እርግጠኛ ነኝ
.....ማስታወስ ባለመቻልሽ ገርመሽኛል ለማንኛዉም ሚፍታህ እባላለሁ አለኝ
..... አሁንም ላስታዉስህ አልቻልኩም አልኩት
....እሱም እንዴት ???
........ብዙ ሚፍታህ የሚባሉ ሰዎችን ስለማወቅ ልለይህ አልቻልኩም
............እሺ ከእነዚህ ብዙ ሚፍታህ ስሞች ዉስጥ የማትረሺዉ የትኛዉን ነዉ ???
.....በጣም አናደደኝ ሰማሀኝ ወንድም ለጅንጀና ጊዜም ሰአትም የለኝም ተወት አድርገኝ ብየ ተቆጣሁት
.....,አትቆጪ ሲርየስ አትሁኝ ሲርየስ መሆን ለወታደር ነዉ ለዛዉም ግድ ሁኖበት ነዉ...ለማንኛዉም አሁን ክላስ ነሽ መሰለኝ ቡሀላ ደዉየ ማንነቴን በደንብ እነግርሻለሁ አለኝ
...... እሺ ብየ ስልኩን ዘጋሁት
     
ስልኩን አዉርቼ እንደጨረስኩ የሆነ ደስ የሚል ስሜት ከየት እንደመጣ የማላቀዉ ተሰማኝ ..ገና ማንነቱን ሳላዉቀዉ ደዉሎ ለስለስ ባሉ በሚያምር ድምፆቹ ስላወራኝ ብቻ ደስተኛ ሁኛለሁ ...አላህ ለኸይር ያርግልኝ ....ከዛም ወደ ፕራክቲክ ክላስ ገባሁኝ፡፡

    ከትምህርት ቤት እንደወጣሁ አሁንም ቅድም በተደወለበት ስልክ ቁጥር ተደወለልኝ ....እኔም አነሳሁት ፡፡ እንደቅድሙ ሰላምታ ከተለዋወጥን ቡሀላ
.....,አሁንስ አስታወሽኝ ??? አለኝ
......... አላስታወስኩህም አልኩት
......እሺ ካላስታወሽኝ አላህ ቀልቡን እስኪ ሰጥሽ ማንነቴን ልንገርሽ ... አንቺን ኪታብ የሚያቀሩሽ የኡስታዝ ልጅ ነኝ አሁንስ አወቅሽኝ ???አለኝ
ሚፍታህን አሁን አወኩት የተለያየ ኪታብ ያቀሩን የኡስታዛችን ልጅ ነዉ
......... አዎ አዉቄሀለሁ አልኩት
......የተለያየ ወሬ ካወራን ቡሀላ ነዋል ከአሁን ቡሀላ እደዉልልሻለሁ ከአንቺ ትልቅ ሀጃ አለኝ ...ብሎ በአፉ ተነፈሰ
......እኔም እሺ ብየ ቻዉ ተባብለን የስልክ ወሬያችንን ጨረስን
.......ሚፍታህ የኡስታዛችን ልጅ ነዉ፡፡ በፊት ኪታብ ስቀራ ይቆጣጠረኛል፡፡ .... ወንድ ጋር ካወራሁ ይመክረኛል ...የሴት መጥፎ ጓደኞች ስይዝ ተይ እነዚህ ዱርየ ናቸዉ አይጠቅሙሽም ይለኛል፡፡ ኪታብ እየሰጠኝ ቅሪ እያለ ያበረታታኝ ነበር፡፡
ከዛ ወደ ዉጭ ሀገር ለስራ እንደሄደ ሰምቻለሁ ከአየሁት ብዙ አመታት አልፈዋል ....ዛሬ መደወሉ ገርሞኛል ደግም ከአንቺ ትልቅ ሀጃ አለኝ ብሎኛል እያልኩ ብቻየን እንደ እብድ አወራ ይዣለሁ፡፡ ገና በመጀመሪያ በደወለልኝ ቀን የሆነ መግለፅ የማልችለዉ ብዥታ አእምሮየን አናወዘዉ...ይገርማል


#ክፍል
ይ........ቀ.............
......ጥ........ላ................ል


JOIN
´´´´´´´ :¨·.·¨: ❀ share
           `·. t.me/Islam_and_Science
t.me/Islam_and_Science
•════••• •••════•
1.8K views05:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-20 08:22:02 አሳዛኝ እዉነተኛ ታሪክ
 
የታሪኩ ርዕስ
#የሆድ_ዉስጥ_ፉም_እሳት
      #ክፍል ☞ አስራ አምስት

ፀሀፊ ☞ #አሚር_ሰይድ





አብራኝ መድረክ የምትመራ ሰልዋ የምትባል ጓደኛ ነበረችኝ ...እሷም ብዙ ሰዉ አንቺ እንድመሪ ይፈልጋሉ ..አንቺ አቅርቢ አስተያየት ላይ ነዋል መድረክ ትምራ እየተባለ ስለሆነ አንቺ ነሽ መምራት ያለብሽ ትለኛለች፡፡ ሰልዋ አግብታለች ሁሌ አብረን ስንሆን ትዳር እንዳገባ ትመክረኛለች ..ነዋል አንቺን ብዙ ሰዉ ዳሪኝ አስተዋዉቂኝ እያሉኝ ነዉ፡፡ ትዳር ምን ያህል ደስታ እንዳለዉ ትነግረኛለች፡፡ እኔ ያገባሁት ቤተሰብ ያመጡልኝን ነዉ እንጂ ከትዳር በፊት Boy frind ብየ የያዝኩት ማንም ወንድ የለም ..ቤተሰብ ለኔ ይሆናል ብለዉ መርጠዉ ያመጡልኝ ጋር ተጋብተን በጣም ተዋደን ተፋቅረን ልጅም ወልደን እየኖርን ነዉ፡፡ ለምን ብትይ ከትዳር በፊት እንጠናና እየተባባልን ስላልተሰላቸን ይሄዉ ፍቅር ሰጥቶኝ እኔም ሰጥቸዉ እየኖርን ነዉ ትለኛለች ሰልዋ የዘወትር ምክሯ ነዉ፡፡
ሰልዋ በምትመክረኝ ምክር ምነዉ በአገባሁ እያልኩ ጥሩ ትዳር መመኘት ጀመርኩኝ...

★★★★ ከኒካህ በፊት ስለማንነታችን በደንብ እንተዋወቅ። ለትዳር ሂወታችን ጠቃሚ ስለሆነ እየተጠናና እንቆይ የሚባለው አባባል ከሸሪአ አንፃር እንዴት ይታያል?
የሴት ልጅ ክብሯ እና ውበቷ እራሷን የህዝብ ሃብት ከማድረግ መቆጠብ መቻሏ ነው፡፡ ይህን ደግሞ ሂጃብ ከማደረግ እራሷን ከመሸፈን አንስቶ ከማንኛውም አይነት አጂ ነብይ ወንድ ጋር ከኒካህ በፊት ግንኙነት ሳታደርግ መቆየት መቻሏ ነው፡፡

ወጣቱም፣አዋቂውም፣ጃሂሉም ባጠቃላይ ማገናዘብ የጀመረ ሙስሊም በሙሉ ከኒካህ በፊት ምንም አይነት ግንኙነት ማድረግ በኢስላም ክልክል መሆኑን ጠንቅቆ ያውቃል፡፡ ይህን የአላህን ክልከላ አውቆ የሚርቀው ግን በጣም ጥቂቱ ነው፡፡

በኢስላም ጋብቻ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ሲሆን መልካም የሆኑ ባል እና ሚስቶችን የሚጣመሩበት ይሆን ዘንድ ያዛል፡፡ ባለጌ ባለጌን እንጂ ጨዋን እንድታገባ በኢስላም አይፈቀደም፡፡ በዝሙት የተጨማለቀ ወንድም የሱ ቢጤውን እንጂ ጥብቅ የሆነችን ሴት እንዲያገባ አይፈቀደም፡፡ ታዲያ ከጋብቻ በፊት ዝሙት እስካልፈፀምን ድረስ ይህ ክልከላ አይመለከተንም ይባል ይሆናል፡፡

መረጃውም አላህ በተከበረ ቅዱስ ቁርአኑ እንዲህ ይለናል፡-
ጥብቆች ኾነው ዝሙተኞች ያልኾኑ የስርቆሽ ወዳጆችንም ያልያዙ ሲኾኑ አግቧቸው፡(ሱራ አል ኒሳዕ፡25) ብሎ አስቀምጦልናል፡፡

ኢብኑ ከሲር በተፍሲራቸው ይህን አንቀፅ  ሲፈስሩት ጥብቆች የሆኑ ማለቱ ምንም አይነት ዚና ያልፈፀሙ እና የብልግና ተግባር ከማንም ጋር ለመፈፀም እሺ የማይሉ እና ፍቅረኛ ያልያዙትን ማለት እንደሆነ አስቀምጠዋል፡፡

ተመሳሳይ መልዕክትም በሱረቱል ማዒዳ ላይ የሚከተለውን እናገኛለን

ከምእመናት ጥብቆቹም ከእነዚያ ከእናንተ በፊት መጽሐፍን ከተሰጡት ሴቶች ጥብቆቹም፤ ዘማዊዎችና (ዝሙተኞች) የምስጢር ወዳጅ ያዢዎች ሳትኾኑ ጥብቆች ኾናችሁ መህሮቻቸውን በሰጣችኋቸው ጊዜ ልታገቡዋቸው የተፈቀዱ ናቸው፡፡(አል ማዒዳ፡5)

ይህንንም አንቀፅ አስመልክቶ ኢብኑ ከሲር(አላህ ይዘንላቸው) ሲያብራሩ ጥብቅ የሆነችን ሴት የሚለውን ከዝሙት የራቀች ፣የወንድ እጮኛ ያልየዘች መሆኑን በመግለፅ ይህ ድንጋጌ ወንዱም ጥብቅ፣ዝሙተኛ ያልሆነ፣የሴት እጮኛ ያልያዘ መሆን እንዳለበት ገልፀዋል፡፡ በዚሁ ማብራሪያቸው ላይ ብዙ እጮኛ ያለውም ሆነ አንዲት እጮኛ ተመሳሳይ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

በዚህ ማብራሪያ ላይ ኢማሙ አህመድ(አላህ ይዘንላቸው) ከላይ በተገለፀው አንቀፅ መሰረት ጥብቅ ያልሆነ ወንድ ወይም እጮኛ የያዘ እንደሆነ ጥብቅ የሆነችን ሴት ተውበት አድርጎ ከድርጊቱ ሳይመለስ ማግባት ለሱ የተከለከለ መሆኑን ፡፡ እንዲሁም ጥብቅ ያልሆነች ሴት፣ ወይም ወንድ እጮኛ ይዛ የነበረች ሴት ከድርጊቷ ተውበት አድርጋ እስካልተመለሰች ድረስ ጥብቅ ወይም ጨዋ ወንድን ማግባት ክልክል ነው ማለታቸውን ኢብኑ ከሲር በተፍሲራቸው ላይ ገልፀዋል፡፡

እንግዲህ ከላይ እንደተመለከትነው ሴት እጮኛም ሆነ የወንድ እጮኛ መያዝ ምን ያህል የተከለከለ መሆኑን በግልፅ ተቀምጦልናል፡፡

አብዛኞቻችን በዚህ ጉዳይ ላይ እራሳችንን የምንሸውድባቸው መገለጫዎች አሉ፡፡ ከነዚህም መካከል ይህን ሃራም የሆነ ፆታዊ ግንኙነት ሃላል ለማስመለስ ከምንጠቀማቸው ምክንያቶች መካከል. ፡- እኛ አላህ ለሚወደው የትዳር ሂወት ተሳሰብን እንጂ ለሀራም አልተፈላለግንም፣ በቅርቡ ኒካህ ለማሰር አስበናል፣ ትምህርቴን እስክጨርስ እንጂ ኒካህ ቶሎ እናስራለን፣ አንዳንድ ነገሮችን እስካስተካክል ድረስ እንጂ ሽማግሌ እልካለው፣ ቤተሰቦቼ ልጅ ነሽ ስለሚሉኝ ላይፈቅዱ ስለሚችሉ እነሱን እስካሳምናቸው ትንሽ ታገሰኝ፣ ለትዳራችን የሚሆን መኖሪያ ቤት እና ቁሳቁስ እስካሟላ ጠብቂኝ፣ በአካል እስካልተገናኘን እኮ ሀራም ላይ አንወድቅም፣ ሰው ባለበት አካባቢ ብቻ አብረን ስለምንሆን ችግር የለውም፣ ከኒካህ በፊት ስለማንነታችን በደንብ ማወቅ ለትዳር ሂወታችን ጠቃሚ በመሆኑ እየተጠናናን ነው፣ ወዘተ..የሚሉ እራስን መሸወጃ ምክንያቶችን በመስጠት በሀራም ግንኙነት ውስጥ መዘፈቁን ይቀጥላሉ..ስለሆነም በሀራም የተጀመረ ነገር በረካ ስለሌለዉ .ሁሉም ለአቅማ አዳም የደረሰ ሰዉ ትዳርና እንቅልፍ በራሱ ጊዜ ይመጣል ብሎ መሶበር ከሀራም መራቅ እና ለሌት እየተነሱ ቁርአን እየቀሩ ከሶላትም በፊትም ቡሀላም በዱአ መበረታታት አለበት፡፡ ትዳር ከፈጣሪ የሚሰጥ ፀጋ ነዉ እንጂ ከፈጣሪ ባይሆንማ በየመንገዱ ያላገባ ወንድም ሴትም መንገዱን ይመላለስበታል..ስንቱን ለትዳር እንመኛለን??ግን ብዙ ተመኘን የምናገባዉ ግን ፈጣሪ የመረጠልንን አንዱን(አንዷን) መሆኑን የማይካድ ሀቅ ነዉ፡፡


ወንድ ለብቻ ሴት ለብቻ በመጋረጃ ተጋርዶ ስንሆን እኛ ሴቶቹ ዝግጅት ስናዘጋጅ ዳቦ ተቆርሶ ወይም ዉሀ ለመስጠት ወደ ወንዶቹ ወደሚቀመጡበት ከመጋረጃ ጀርባ ላላዉ ስጪ ሒጂ አድርሺ ትለኛለች
.....እኔም አልወስድም ሌላ ሰዉ ላኪ እላታለሁ
.....ከዛም እንደዚህ ትለኛለች ነብዩ ሙሀመድ ሰ.ዐ.ወ አሚሩን የተኻለፈ የረሱልን ትእዛዝ ኺላፍ ያደረገ ነዉ ደግሞ የረሱልን ኺላፍ ያደረገ ደግሞ አላህን ኺላፍ ያደረገ ነዉ ትለኛለች፡፡ እኔም ሳልወድ በግዴ ወደ ወንዶቹ መቀመጫ ሂጄ የላከችኝን የሚበላ የሚጠጣ ነገር ሰጥቼ ወዳዉ እወጣለሁ
ሰልዋ ማታ ትደዉልልኝ እና ስትገቢ እንደዚህ የለበሰዉ አንደዚህ ያለሽ ልጅ ብዙ ምልክት ትነግረኝ እና ልጁን ሳወቀዉ እሱ ልጅ ዳሪኝ እያለ ጠይቆኛል ትለኛለች...

ሰልዋም ምን ይሻለኛል?? ለየትኛዉ እንደምድርሽ የትኛዉን እንደምመርጥልሽ ግራ ገባኝ ዳሪኝ እያሉ ብዙ ሰዉ ጠየቀኝ ተቸገርኩኝ......ትለኛለች፡፡
..እኔም ቆይ እስኪ ልሰብበት ሰልዋ እላታለሁ

  .....እኔ የምፈልገዉ ከነማንነቴ የሚቀበለኝ ..በልጅነት መደፈሬን አዉቆ ሞራሌን የሚጠብቅልኝ ነዉ .... ደግሞ እሺ ተቀራረብኩኝ የኔን ማንነት እንዴት አድርጌ ነዉ የምነግረዉ ??? እንዴት ብየ ወንዶችን እቀርባለሁ??? እያልኩ ብቻየን በሀሳብ ጭልጥ ብየ ሀሳብ ወስዶ ይመልሰኛል

አንድ ቀን ሴት ተማሪዎች ቁርአን ሀፍዘዉ ስለጨረሱ ትልቅ ዝግጅት ተዘጋጅቷል ፡፡ አንድ ወጣት ጋር ስለዝግጅቱ ሰልዋ ጋር ያወራል... እኔ ስመጣ እንተዋወቅ አለኝ
.....እኔም እሺ አልኩት
.... ካሊድ እባላለሁ አለኝ
...እኔም ነዋል እባላለሁ አልኩት
በዛዉ ተዋዉቀን እናም አብረን እሷ ጋር ሄድን
1.5K views05:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ