Get Mystery Box with random crypto!

ISLAM IS UNIVERSITY

የቴሌግራም ቻናል አርማ islamisuniverstiy_public_group — ISLAM IS UNIVERSITY I
የቴሌግራም ቻናል አርማ islamisuniverstiy_public_group — ISLAM IS UNIVERSITY
የሰርጥ አድራሻ: @islamisuniverstiy_public_group
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.00K
የሰርጥ መግለጫ

⭐️ሰው የሚገነዘብ አእምሮና የሚያፈቅር ልቦና ባለቤት ነው።እነዚህ ሁለቱ ካልተመጣጠኑ ስብእናው አደጋ ውስጥ ነው።የሚያገናዝበው አዕምሮው፣የሚያፈቅረው ልቡ፣የሚንቀሳቀሰው አካሉናወደ ሰማይ የሚወነጨፈው መንፈሱ በውህደት ካልተንቀሳቀሱ ሰውየው ላይ ችግር አለ ማለት ነው
📨የፍቅር እና የጥላቻ ስሜቱ፣የፍላጎት እናየፍርሃት መንፈሱ በአዕምሮ ብስለት ካልተገራ አስቸጋሪ ነው
አስተያየት👇
T.me/Aisuu_bot

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 28

2022-09-10 20:44:00 የዑመር ኢብኑልኸጣብ (ረዐ) 20ምርጥ ምክሮች፤
.
1. ‹የምትጠላውን ሰው ተጠንቀቅ፤›

2. ‹ብልጥ ሰው የእለት ስራዎቹን ከራሱ ጋር ይተሳሰባል፡፡

3. ‹የዛሬን ስራ ለነገ አታሳድር፡፡›

4. ‹ከሰዎች ጥያቄ ተነስተህ አስተሳሰባቸውን መለካት ይቻላል፡፡›

5. ‹ለሌሎች ዳዕዋ በምታደርግበት ወቅት እራስህን አትርሳ፡፡›
.
6. ‹ከዱንያ ትንሽን ብቻ ስትፈልግ ይበልጥ ነፃነትን እያገኘህ ትሄዳለህ፡፡›

7. ‹ወንጀል አለመስራት ከፀፀት ይሻላል፡፡›

8. ‹ታጋሽ ሁን፤ ትዕግስት የእምነት ምሶሶ ነችና፡፡›

9. ‹አሏህን ፈሪ መሆን እድለኛነት ነው፤ ከዚህ ውጭ ያለው እድለቢስ መሆን ነው፤›

10. ‹ወደ አኺራ የሄዱ ሰዎችን ንግግር ጠብቁ፤ እነርሱ የተናገሩት አሏህ እንዲናገሩ ያገራላቸውን ብቻ ነውና፡፡
.
11. ‹አሏህን ፍራ፤ እርሱ ሁሌም ህያው፤ ከርሱ ውጭ ያሉ ሁሉ ጠፊ እና አላቂ ናቸውና፡፡

12. ‹ጥፋቴን በነገረኝ ሰው ላይ የአሏህ እዝነት ይውረድ፡፡

13. ‹እውቀትን ገብያት፤ ከዚያም ለሰዎች አስተምር፡፡›

14. ‹የተከበርክ፣ ታማኝ እና እውነተኛ ሁን፡፡›

15. ‹ትምክህተኛ ምሁር አትሁን፤ ትምክህተኛነት እና እውቀት አንድ ላይ አይሄዱምና፡፡
.

16. ‹ለዚህች አለም ፍቅር ያለው አዋቂ ባየህ ግዜ እውቀቱ አጠራጣሪ መሆኑን ተረዳ፡፡›

17. ‹ትንሽ አውርቶ ብዙ በሚሰራ ሰው ላይ የአሏህ እዝነት ይውረድ፡፡›

18. ‹ታማኝነት ማለት በምትሰራው፣ በተናገርከው እና በምታስበው ነገሮች ልዩነት አለመኖር ማለት ነው፡፡

19. ‹የሰው ልጅ ምንም እንኳ እንደ ቀስት ቀጥ ያለ ስራ ቢሰራ ተቃውሞ አያጣውም፡፡›

20. ‹አዕምሮህ እንዲሰፋ ከፈለግክ፤ ከፈሪሀ አሏሆች ጋር ተቀመጥ፤›

ለወዳጆችዎ ሼር በማድረግ ያካፍሉ

SHARE SHARE
http://t.me//@arebgendamesjid
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ
1.2K views17:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-10 10:39:21    ከልጅነት ጀምሬ የምቀራረበዉ ኡስማን  ትምህርት ቤት አንድ ስለሆነ ቁርአን ቤትም እንገናኛለን እሱም ቁርአን ላይ ጠንክሯል፡፡ ቁርአናችንን እየተዉን እቤታቸዉ እየሄድን ባንጫወትም ግን እኔ እና እሱ የልጅነት ፍቅር ተብየ በሁለታችን ልብ ዉስጥ አለ
   ኡስማን ጋር ከአንደኛ ክፍል እስከ ሰባተኛ ክፍል ድረስ ስንማር አንድ ትምህርት ቤት ስለነበርን የፍቅር ይሁን የልጅነት ነገር ይሁን አላቅም ኡስማንን ሳየዉ ፍዝዝ የማለት ልቤ እንደመደንገጥ ሰዉነቴ አልታዘዝ አልታዘዝ እንደማለት ይሆናል ፡፡ ግን ፍቅር ማለት ምን ማለት ነዉ??
በነብዩ ጊዜ የነበሩ ሱሀቦች ፍቅርን እንዲህ ነበር የተረጎሙት

★★★በአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ጊዜ በኡሁድ ዉጊያ ነብዩ ሰ.ዐ.ወ ተገድለዋል የሚል ዜና መዲናን እየናጣት ነበር ..የመዲና ሰማይ በዚህ አሳዛኝ ወሬ በሀዘን አጥልሏል..መረጃዎችን ለማግኘት ወደ ኡሁድ አቅጣጫ እየተመመ ነዉ
ከአንሶሮች መካከል የሆነችዉ ሱመይራ(ረ.ዐ) ሁለት ልጆቿ አባቷ ባለቤቷና ወንድሟ ሰማዕት መሆናቸዉን ተረዳች ..ሱመይራ እነዚህ ሁሉ ወገኖቿ ቢሞቱባትም በዚህ ሁሉ የሀዘን ዉርጅብኝ አልተናወፀችም ..እልቁንስ እሷን ያስጨነቃት በእዉነት የታወቀዉ የጓጓችለት አንድ ዜና አለ ይህም የነብዩ ሰ.ዐ.ወ በሒወት መኖር ነዉ
..በእርሳቸዉ ላይ የደረሰ አንዳች ክፉ ነገር አለ??በማለት ጠየቀች
...የነብዩ ባልደረባዎችም ለአላህ ምስጋና ይገባዉ እርሳቸዉ በሒወት ይገኛሉ በመልካም ሁኔታ ላይ ይገኛሉ አሏት
ሱመይራ እንዲህ አለች ፡-እሳቸዉን እስከማይ ድረስ እረፍት አላገኝም የአላህ መልዕክተኛን (ሰ.ዐ.ወ)አሳዩኝ አለች
እሳቸዉን እንዳሳዩዋትም በቀጥታ ወደ እርሳቸዉ በመሄድ የካባቸዉን ጫፍ ከያዘቼ ቡሀላ እንዲህ አለች
"""""እናቴና አባቴ መስዋት ይሁንለልዎ የአላህ መልዕክተኛ ሆይ!እርስዎ በሂወት እስካሉ ድረስ ሌላዉ ሁሉ ቀላል ነዉ ..ያ በነብዩ ዙሪያ የነበሩ የተባረከ ትዉልድ ለእርሳቸዉ ይህን የመሰለ ድካ የሌለዉ ፍቅር ይለግሳቸዉ ነበር ...እኛስ?? ፍቅርን በሰዉ አይደል የምናመሳስለዉ ???

  እኔ ስድስተኛ ክፍል በምማርበት ጊዜ ኡስማን ጋር ብዙ ጊዜ ቁርአን ቤት እና ትምህርት ቤት እንገናኛለን ቁርአን እቀራለሁ እንጂ ሶላት አልሰግድም ለዚህም ምክንያት ቤተሰቦቼ ስገጅ ብለዉ ስለማያበረታቱኝ ነዉ ...   ትምህርት ቤት ስሄድ ሱሪ እለብሳለሁ ..

ሱሪ በምለብስ ጊዜ ኡስማንም ቁርአን ቤት ስትመጪ ሒጃብ ትለብሻለሽ ትምህርት ቤት ደግሞ ሱሪ ትለብሻለሽ አንዴ ቃልቻ አንዴ ዱሪየ እስታይል አትከይ ከአሁን ቡሀላ ትምህርትም ስትመጪ ሱሪ ለብሰሽ እንዳትመጪ ብሎ ይቆጣኛል፡፡
....እኔም እሺ ከአሁን ቡሀላ አለብስም አልኩት

እኔ ከኡስማን ጋር ጊዜ ማሳለፍ እሱም እኔ ጋር ጊዜ ማሳለፍ ደስ ይለዋል፡፡ ኡስማን ጋር ከትምህርት ቤት ስንመለስም ስንሄድም ተቃቅፈን ነዉ....የክላስ ልጆች ነዋል እና ኡስማን እኮ ይዋደዳሉ ተቃቅፈዉ ነዉ የሚሄዱት እያሉ ሁሌ ያወራሉ ፡፡ አዎ እዉነታቸዉን ነዉ የኡስማን ሰፈር ቆሎ በር አካባቢ ነዉ፡፡ አንዳንዴ እኔን አጂፕ ድረስ ይሸኘኛል
 
አሁን ድረስ የሚገርመኝ ሁሌ እቤቴ ስሄድ ሶላት ባልስግድም __ግን በዱአ አላህን በመለመን አምን ነበር፡፡ መስገጃ ቦታ ላይ ሱጁድ ወርጄ  ስቅስቅ ብየ እያለቀስኩ ያረቢ  ኡስማንን የኔ አድርግልኝ ኡስማን የኔ የወደፊት ባሌ አድርግልኝ አንዴ የፍቅር ጥያቄ ይጠይቀኝ እምቢ አልልም እንዲጠይቀኝ አርግልኝ  እያልኩ አላህን እለምናለሁ ፡፡
   ግን ቢጠይቀኝ ገና ልጅ ነኝ ምን እለዋለሁ??? እንዴ ሁለታችንም ልጆች ነን ትዳር የማይታሰብ ነዉ እንዴት ይሄንን ሀሳብ ልመኝ ቻልኩኝ??? ደግሞ ለኡስማን የተለየ አመለካከት ቢኖረኝም ወንድ ልጅ እንደ ቶፊቅ ጨካኝ ቢሆንስ እያልኩ ብቻየን የሀሳብ ማዕበል ወስዶ ይመልሰኛል ..ነገር ግን ኡስማንን መራቅ የማልችልበትም ደረጃ ላይ ነኝ፡፡

ትምህርት ቤቶች ላይ ጥንቃቄ ግድ ነዉ ትዉልዱ ገና ከአራተኛ ክፍል ጀምሮ ሌላ መስመር ይጀምራል...ቤተሰብ ልጄ ገና ህፃናት የሚለዉን የድሮ ተረት ትተዉ  ልጅን እንደልጅ ሳይሆን እንደ እህትነት አርገዉ ቢቀርቡ የተሻለ ነዉ..አንድ ሰዉ ሁሌ የሚናገራት ንግግር ትዝ ይለኛል የሴት እና የአር ትንሽ የለዉም ይላል እዉነቱን ነዉ ሴት ልጅ ገና ልጅ ናት ቢባል በወንድ ልጅ አፍ መሸወዳ አይቀርም..አርም ትንሽ ብትሆን መሽተቱ አፍንጫ መረብሹ ስለማይቀር ወላጅ የትምህርት ቤት አዋዋልን ልብ ሊል ይገባል ባይ ነኝ፡፡
  
ኡስሚ አንዳንዴ እየቀለደ ነዋል አፈቅርሻለሁ እኮ ምናምን ሲለኝ እዉነት እየመሰለኝ ልቤ ድንግጥ ይላል ወይ የልጅነት ፍቅር ...








#ክፍል
ይ.......ቀ.......ጥ
......ላ........................ል


JOIN
´´´´´´´ :¨·.·¨: ❀ share
           `·. t.me/Islam_and_Science
t.me/Islam_and_Science
•════••• •••════•
   
1.6K views07:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-10 10:39:20 አሳዛኝ እዉነተኛ ታሪክ
 
የታሪኩ ርዕስ
#የሆድ_ዉስጥ_ፉም_እሳት
      #ክፍል ☞ አራት

ፀሀፊ ☞ #አሚር_ሰይድ




  ነዋል አንቺ ገና የልጅነት ሒወትሽን ሳታጣጥሚ ክፉ እና ደጉን በማትለይበት በለጋ እድሜሽ በአራት አመትሽ በጎረቤታችን ልጅ  አንቺም እኔም በምናቀዉ በቶፊቅ  ተደፍረሽ ነበር ..ለዛ ነዉ ልጅቱ ጋር ስትጣሉ #በቶፊቅ_የተደፈርሽዉ ያለችሽ ..መስጊድ ዉስጥ ያቺ ልጅ እናቷ ነግራት አንቺን የነገረችሽ የማይካድ ሀቅ ነዉ ነዋልየ  

አንቺ ልጅ ስለሆንሽ ስለማታስታዉሽ ነዉ  ብላኝ እንባዋን እየዘረገፈች  የቤት ሰራተኛችን ነገረችኝ፡፡

ሰራተኛችን ስነግረኝ ቁሜ ቀረሁ እንባየ በሁለት ጉንጮቼ ኩልል እያሉ ወረዱ ...እዉነት መሆኑን አረጋገጥኩ ... ወደድኩም ጠላሁም አምኖ መቀበል እንጂ መቀየር የማልችለዉ የተፈጠረ ሀቅ ነዉ፡፡
የኔ ሂወት ዉጣ ዉረድ ስቃይ ፈተና ከዚሁ ከአራት አመቴ ይጀምራል

       ሬቱን ከማር ለይቼ ሳላውቀው
       ሀራሙን ከሀላል ከቶ ሳለየው
       አፍረተ ገላዬን መሸፈን ሳለምድ
      ጣፍጭ የሚያታለኝ በግድም በውድ

     ብልጠት ያላበቀልኩ እንቡጥ ከረሜላ
     ገና ያልበሰልኩ ጥሬ እንቡቅላ
     እንኳንስ ቀበቶ ለኔ ሊፈቱ
     የስሜታቸውን ጥግ በኔ ላይ ሊያበርዱ

      ገና ሲያዩኝ ላይን የማሳሳ
     እንኳንስ ሊነኩኝ ሲያዩኝ የሚያሳሳ
    እንዴትስ ተችሎት ስቃይ አሸከመኝ??
     አካሌን ለአካሉ ለምኑ ተመኘኝ???
     

ሰራተኛችን ከነገረችኝ ቡሀላ ወደ ሆላ ማሰብ ጀመርኩ በዛ ጊዜ አባቴ ቶፊቅን በሽጉጥ እገላለሁ ሲል እና ገና በተደፈርኩኝ አካባቢ ሆስፒታል ስሄድ ፓሊስ ጣቢያ አባቴ ጋር ስሄድ ፍርድ ቤት አብረን እየሄድን አባቴ ሲከራከር ትንሽ ትዝታዎች ብልጭ ይልልኝ ጀመር ፡፡

ቶፊቅም እዛዉ ፍርድ ቤት ሲቀርብ ታወሰኝ ነገር ግን አልታሰረም በብር ቅጣት ተቀጥቶ ክሱ የተቋረጠ ይመስለኛል...ግን ለመን አልታሰረም ህይወቴን ልጅነቴን አይደል የወሰደዉ????በአራት አመቴ ህፃን ልጅ ነኝ መደፈር የሚባለዉን አላቅም..ቶፊቅ ግን ትልቅ ልጅ ነዉ ቢያንስ ሀያ አመት ይሆነዋል፡፡ ገና እኔ ሰዉነቴ ሳይጠነክር ሳያዝንልኝ እንደ ደፈረኝ አስተወስኩኝ ፡፡  ሰራተኛችኝም ብዙ ነገሮችን እያረጋጋች ነገረችኝ ...

ቶፊቅ ጅማ የሚኖረዉ ከአያቱ ጋር ነዉ ፡፡ ከእኛ ቤት ጎን ነዉ ቤታቸዉ ፡፡ ሁሌ መጫወት ስፈልግ የእኛ ግቢ በጣም ሰፊ ቢሆንም ቤታችን ሙሉወን G2 የተሰራ ሲሆን  መኪና ማቆሚያ ብቻ ነዉ ያለዉ ...ስለሆነም እነ ቶፊቅ ቤት መጨዋት ለኔ ይመቸኛል ...የቶፊቅ አያቶቹ ነጋዴዎች ስለሆኑ እሱ ነዉ ቤት ሲጠብቅ የሚዉለዉ.....
    እዛ ግቢ እቃቃ ስንጫወት እንትና የኔ ልጅ ትሁን እንትና እየተባለ ቶፊቅ እኔን የኔ ልጅ ናት ብሎ ሁሌ እቃቃ ስንጫወት የቶፊቅ ልጅ ነበር የምባለዉ ፡፡ ቶፊቅ ለቤተሰቦቼ ጥሩ መስሎ የሚታይ ሁሌ እቤቴ ሲወስደኝ አቅፎ ተንከባክቦ ስለሆነ እናቴም አባቴም አይጠረጥሩትም ....እንደዉም አባቴ ልጄን የወደደ እኔን ወደደ ይባል የለ ..ቶፊቅን በጣም ይወደዋል..,

  አንድ ቀን እናቴ ድስት ከእነቶፊቅ ቤት አምጪ ብላ ላከችኝ.... እሱ ቤት ስሄድ ቶፊቅ ማንጎ እየበላ ነበር....ማንጎ ስጠኝ ???ስለዉ
ድስቱን ለእናትሽ አድርሰሽ ነይ እና እሰጥሻለሁ አለኝ
....እኔም ለእናቴ ድስቱን ሰጥቼ ወደ ቶፊቅ ቤት ተመለስኩኝ ...ከዛም ማንጎ ሰጥቶኝ የፈለገዉን የልጅነት ገላየን ሲጫወትበት ...እናቴም ልጄ ምን ሁና ቀረች ??መጣሁ ማንጎ ተቀብየ  ብላኝ ?? ከነቶፊቅ ቤት ዉጭ ሂዳ ይሆን እንዴ ??ብላ ...እነ ቶፊቅ ቤት መኖሬን አልመኖሬን ለማረጋገጥ ስትገባ ቶፊቅ እኔን ልብሴን አስወልቆ እንዳሻዉ ሲያደርገኝ በአራት አመቴ መቀበል የማልችለዉ በደል ሲያደርስብኝ እናቴ በአይኗ ተመለከተች
......እናቴም ያየችዉን ማመን አቃታት. ባለችበት ድርቅ ብላ ቀረች..
....,የምታወራዉ የምትለዉ አጣች አፏ ተያያዘ ..ምን ይደረጋል ይሄ እንኳን የወለደችኝ እናቴ ለኔ የምትሳሳስልኝ አድጌ ብዙ ደረጃ እንድደርስ የምጠበቅ ልጅ ..በልጅነቴ ተደፈርኩ ...እናቴ የኔን ክብር ማጣት በአይኗ አየችዉ፡፡
የምትለዉ ስታጣ ጩኸቷን አቀለጠችዉ.
  የእኛ ሰፈር የሚኖሩ ሰዉ አንድም ሳይቀር ልጅ ትልቁ ወጣቱ ሽማግሌዉ የኔን መደፈር በአንዴ ታወቀ...ቶፊቅም አፍሮ ለጊዜዉ ከአካባቢዉ ተሰወረ፡፡ ሰራተኛችን በሂደት ሁሉንም ነገረችኝ፡፡

   ከሁሉም ሰዉ የቤት  ሰራተኛችን ትሻለኛለች እሷ ትረዳኛለች፡፡ ቤተሰቦቼ ጋር ብር እርዚቅ ቤታችን ላይ ይኑር እንጂ ምንም ስምምነት የለም... ሁሌ መጣላት ነዉ ስራቸዉ፡፡ የመጨረሻ ልጅ እህቴ ከተወለደች ቡሀላ እናት እና አባቴ አንድ ላይ  ሲተኙ እንኳ አይቻቸዉ አላቅም፡፡
     የኔ ስነ ልቦና ጫና እያለብኝ ግን ቤተሰብ ባለመስማማታቸዉ እኔን ከጎኔ ሁኖ አብሽሪ እያለ የሚያፅናናኝ ቤተሰብ ዘመድ ጎረቤት ጓደኛ የለኝም ፡፡

   ቶፊቅ በኔ ላይ የሰራዉ በደል ትዝ ሲለኝ ብቻየን አልቅሼ እምባየን የሚጠርግልኝ የለ እኔዉ እራሴ በአስሩም የእጅ ጣቶቼ እያቀያርኩ ከፊቴ አብሰዉ ይዣለሁ፡፡ ለማን አልቅሼ ነግሬ አብሽሪ ይበለኝ ??? ማን ነዉ ከጎንሽ ነን የሚለኝ ???

አንዳንዴ ይሄ መደፈሬ ትዝ ሲለኝ ብቻየን ሁኜ ድብር ብሎኝ ስቀመጥ....አባቴ በከፋኝ በደበረኝ ቁጥር ከጎኔ ሁኖ ነዋል ምን ሆንሽብኝ?ደብሮሻል ፊትሽ ተቀያይሯል እኮ እያለ  ያፅናናኝ ነበር ....
ግን ይሄንን ወሬ ሰራተኛችን ስለነገረችኝ ለአባቴ መናገር አልችልም፡፡ ያለኝ አማራጭ አባቴ ጋር ስሆን ደስተኛ ምንም ቅር ያላለኝ በሒወቴ የተደሰትኩ እመስላለሁኝ..ብቻየን ስሆን ደግሞ ባለቅሰዉ ባለቅሰዉ ደግሜ ባለቅሰዉ ምንም ሊወጣልኝ አልቻለም ፡፡እምባየ አለማለቁ ለራሴ ይገርመኛል
   ደግሜ ከእኔ ቁስል በላይ የሚያመኝ እናት እና አባቴ ማታ ማታ በተጣሉ ቁጥር እኔ ሌላ ሀዘን ለቅሶ ጭንቀት ነዉ ፡፡ ለማን አግዛለሁ ?? ማን ጥፋተኛ እንደሆነ አላቅም ግን ሲመስለኝ እኔ ጋር የተያያዘ እንደሆነ ይታወቀኛል

ግን ብዙዉን ጥፋቱ እናቴ ትመስለኛለች..ሁሌም ቢሆን ነገር አፈንፍና ነዉ የምትጣላዉ

   እናት እና አባቴ ትዳራቸዉን አይፋቱ እኛ ሶስት ልጆች ተፈጥረናል ፡፡ ተስማምተዉ አይኖሩ መስማማት አልቻሉም ፡፡ ብር ሀብት ሳያንስ ግን መስማማት ባለመቻላቸዉ አላህ የሰጠንን ሀብት ንብረት በደስታ መጠቀም አልቻልንም ፡፡

  ከእናቴ በላይ አባቴ በጣም ይቀርበኛል የቶፊቅን በደል አብሽሪ አይዞሽ አይለኝም..ለምን እኔ የማቅ አይመስለዉም ፡፡ ይሄን ሚስጥር ማወቄን ቢሰማ ቀጥታ ሰራተኛችን ጋር እንደሚጣላ እርግጠኛ ነኝ
 
አባቴ ግን ሁሌ ባገኘኝ ቁጥር በዙ ቀን እየደጋጋመ ፀጉሬን እያሻሸ አንቺ ባትፈጠሪ ኑሮ እናትሽ ጋር መለያየታችን አይቀርም ነበር ...እናትሽ ጋር ለመፋታት አስብ እና አንቺ ትዝ ስትይኝ እንደገና እተወዋለሁ ይለኛል፡፡
ሁሌም ቢሆን የአይኔ ማረፊያየ ነሽ..አላህ ይጠብቅልኝ ብሎ ግንባሬን ሳም አርጎኝ ስሄድ የሆነ ደስ የሚል ስሜት ይፈጥርልኛል..ልቤም እንደመረጋጋት ይላል
1.4K viewsedited  07:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-09 08:43:41 አሳዛኝ እዉነተኛ ታሪክ
 
የታሪኩ ርዕስ
#የሆድ_ዉስጥ_ፉም_እሳት
      #ክፍል ☞ ሶስት

ፀሀፊ ☞ #አሚር_ሰይድ


     ያቺ ልጅ በልጅነቴ የሰደበችኝ አባቴ በሽጉጥ እገላለሁ ያለዉ ሚስጥር ሙሉ በሙሉ እየተገለጠልኝ መጣ.....
.....ኢሻ ሶላት እስከሚደርስ ደአዋ እየተደረገ ሶላቱን እየተጠባበቅን በነበርንበት ሰአት እምባየ እንደ ወራጅ ወንዝ ይወርድ ጀመር.... በአንዴ የለበስኩትን ሒጃብ በእምባ አራስኩት ....ግን የነገረችኝ እዉነት ነዉ እንዴ?እያልኩ በእድሌ ማዘን ጀመርኩ....

ልጅቱንም ከአሁን ቡሀላ አንቺ ጋር ወደ መስጊድ መሄድም መምጣትም ጓደኛም መሆን አልፈልግም ብየ ከመስጊዱ ዉጭ በመዉጣት እምባየን ጠርጌ ፊቴን ታጥቤ መልሼ መስጊድ ገብቼ ኢሻንም ተራዊህን ሰግጄ እቤቴ ብቻየን ተመለስኩኝ...........
    
በመነገታዉ ወደ መስጊድ ብቻየን ስሄድ የእሷ ቅርብ ጓደኞች መስጊድ መግቢያ በር ላይ አገኘሆቸዉና ነዋል በምን ተጣልታችሁ ነዉ ?? አብራችሁ መስጊድ እየሄዳችሁ አልነበር እንዴ ?? አንቺም ብቻሽን እሷም ብቻዋን ነዉ የምትሄደዉ ምን ሁናችሁ ነዉ ??ብለዉ ሰብሰብ ብለዉ ጠየቁኝ
......እኔም አይ ለጊዜዉ ተጣልተን ነዉ ቀላል ፀብ ነዉ እንታረቃለን ብየ ማለፉን ፈለኩኝ ለምን የተጣላንበትን ምክንያት መንገር ለኔ በጣም የሚቀፍ እና አሳፋሪ ነዉ ............
   እነሱም ነዋል ለምን ትዋሺናለሽ ?? አንቺ ባነግሪንም እኛ የተጣላችሁበትን ምክንያት አዉቀንዋል ፡፡ የተጣላችሁበትን ምክንያት እሷ የአንቺን የምታቀዉ ሚስጥር እናቷ ስለነገረቻት ስለምታዉቀዉ ነዉ አይደል አንቺ "..................." ስለሆንሽ በዚህ እዉነተኛ ወሬ አፍረሽ አይደል የተጣላሽዉ አሉኝ፡፡
.....እኔም በልጅቱ ነገረኛነት ሚስጥር አለመጠበቅ በማዘን ጥሩ ጓደኛ አለመሆኗን ታዝቤ ልጆቹን ትቻቸዉ ጥሩም መጥፎም ሳልመልስ ሄድኩኝ....አንዷ እየሄድኩ ከሆላየ እየተከተለች መጥታ """"""ነዋል አንቺ"" ............. ""ስለሆንሽ አታናግሯት ብላኛለች ስለሆነም እኛም ከአሁን ቡሀላ አናወራሽም አሉኝ፡፡
  
የዚች ልጅ መጥፎ ጓደኝነት ከነከነኝ በሰራችዉ ስራ በጣጣም አዘንኩ ...ለነገሩ ሰዉ አመሉ መጥፎ ከሆነ ጥሩ ለመሆን እድል ይጠይቃል ፡፡መጥፎ ጓደኛ በህይወት ላይ የራሱ የሆነ መጥፎ ጫና አለዉ ...
  ነብዩ ሙሀመድ ሰ.ዐ.ወ በሀዲሳቸዉ ሙዕሚንን እንጂ አትጎዳኝ ...እንዲሁም አንድ ሰዉ በጓደኛዉ እምነት ላይ ነዉ ;ከእናንተ አንዳችሁ ከማን ጋር እንደሚወዳጅ ይመልከት ..እንጂ ዝም ብሎ ወዳጅነት አይመስርት ሲሉ ይመክራሉ

አብደላ ቢን ኡመር ደግሞ አስገራሚ ምክር ለግሰዉናል ፡- "ጠላትህን ራቀዉ፡ወዳጅህን ተጠንቀቀዉ ሙዕሚን ሲቀር፡አላህን ከሚፈራ በቀር ታማኝ የለምና፡ጠማማን አትጎዳኝ ከጥመቱ ያስተምርሀል፡ሚስጥርህን ለእሱ አትንገር ፡ማማከር ስትፈልግ አላህን የሚፈሩ ግለሰቦችን አማክር...ብለዋል

ጓደኝነት በኢስላም ልዩ ትኩረት ከተሰጣቸዉ ግንኙነቶች አንዱ ነዉ፡ሰዉ ዉሎዉን ይመስላል ይባላል ከመጥፎ ሰዎች የዋለ እንደዛዉ መጥፎ የመሆን እድል ይገጥመዋል ፡ ከጥሩ ሰዎች የዋለ እንደ እነሱ ጥሩ ሰዉ የመሆን እድሉ ሰፊ ነዉ፡፡

    በሰፈር ልጆች ወሬ ሒወት ገና በልጅነቴ አስጠላችኝ...ለወደፊት ለመኖር ተስፋ ቆረኩ በልጅነቴ ህይወት ጨለመችብኝ ..ኑሪ ኑሪ የሚል ተስፋ ከኔ ላይ ጥሎኝ ሲሄድ ታየኝ.... ብቻየን በየመንገዱ ማልቀስ ጀመርኩ ...ግን ፈጣሪ በልጅነቴ ጀምሮ ለምን ሊፈትነኝ ፈለገ እያልኩ ብቻየን አስባለሁ..... በኔ እኩያ ያሉ ልጆች ደስታ ጨዋታና ሳስታዉስ በተዘዋዋሪ ደግሞ እኔ በመደሰቻየ ስቄ ተጫዉቼ በማደጊያየ የሰቀቀን የለቅሶ ህይወት ለመኖር ተገደድኩ .....
ወሬዉ ትክክል መሆኑን ሲደጋገም አረጋገጥኩ......... ግን የበለጠ እርግጠኛ መሆን የፈለኩት ሰራተኛዋ ስነግረኝ መሆኑን እራሴን አሳመንኩኝ....

ረመዷን አልቆ ክረምቱም አልፎ ስደስተኛ ክፍል ገባሁ ....የቤት ሰራተኛችን የአላህ ነገር የአባቴ ጓደኛ እሷን አግብቶ ወደ ናዝሬት እንደሚወስዳት ከአባቴ ሰማሁኝ....

   ይህን ወሬ አባቴ እንደነገረኝ ማሻ አላህ አልኩ..ከዛም አባቴ ለስራ ከቤት ሲሄድ ...
የቤት ሰራተኛችንን ሚስጥሩን እንድነግረኝ ...እባክሽ ስሰቃይ አልኑር እዉነቱን ንገሪኝ እኔ የሰፈር ልጆች እየነገሩኝ ነዉ አንቺ እዉነት ነዉ በይኝ እና ቁርጤን ልወቀዉ ብየ እያለቀስኩ ለመንኳት
......እሷም እንባየን እያበሰች ነዋል እሺ እነግርሻለሁ እምባሽን ጥረጊ አለችኝ.....
...እኔም ሚስጥሩ እዉነት መሆኑን ለማረጋገጥ ወዳዉ እንባየን ጠረኩኝ
......, ሰራተኛችንም ለአባትሽ ላልናገር ብለሽ በአላህ ስም ማይልኝ አለችኝ
...........እኔም ወላሂ ለአባቴ በጭራሽ ላልናገር ብየ ማልኩኝ
....ሰራተኛችን ለስለስ ባለ ድምፅ ነዋል እኔ ባልወልድሽም የማይሽ እንደ ልጄ ነዉ እዚህ ቤት ሰራተኛ ሁኜ ማገልገል የጀመርኩት ገና አንቺ ሳትወለጅ እናት እና አባትሽ ከተጋቡበት ጊዜ ጀምሬ ነዉ.....በመንከባከብ ያሳደኩሽ እኔዉ ነኝ፡፡

ነዋል ግን በልጅነትሽ አንድ የተፈጠረ ነገር አለ.. ስነግርሽ መጨናነቅ አያስፈልግም ለወደፊት ጠንካራ እና ለሰዉ ወሬ የማትበገሪ መሆን አለብሽ ..ይሄ በአንቺ ቤተሰብ እና በኔ ቁጥጥር የሆነዉ ሚስጥር አገር ያወቀዉ ፀሀይ የሞቀዉ የአደባባይ ሀቅ ነዉ.... ከሰፈር ልጆች የምሰሚዉ ሚስጥሩ በሁሉም የሰፈር ሰዉ ትልቁም ትንሹም ያቀዋል .....

   ነዋል አንቺ ገና የልጅነት ሒወትሽን ሳታጣጥሚ ክፉ እና ደጉን በማትለይበት በለጋ እድሜሽ በአራት አመትሽ..........

#ክፍል
ይ.......ቀ........
......ጥ.......ላ...........ል



JOIN
´´´´´´´ :¨·.·¨: ❀ share
           `·. t.me/Islam_and_Science
t.me/Islam_and_Science
•════••• •••════•
2.0K views05:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-08 15:24:13 አቂደቱል ዋሲጥያ
ሸይህ ዑመር አሊ
  ክፍል- የመጨረሻ ክፍል-
http://t.me//@arebgendamesjid
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ
ዘርፍ
1.9K views12:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-08 10:25:45 አባቴም ነዋልየ አትከፊብኝ እኔ እኮ ተናድጄ ነዉ የገረፍኩሽ በቁርአንሽ ጎበዝ እንድትሆኝልኝ ነዉ ሁሌም ምኜቱ ፡ብዙ ጊዜ ነግሬሻለሁ ለአንቺ ብየ ነዉ ከእናትሽ ጋር የምኖረዉ ደልቶኝ ተመችቶኝ ሳይሆን አንቺን ብየ እንደሆነ ..ነዋል መቼም ቢሆን አንቺን አልጠላሽም.... ከገረፍኩሽ ቡሀላ የዛኑ ቀን ተፀፅቻለሁ ማታ ወደ ቤት ስገባ እኔን ፍርቻ ብቻሸን መኝታ ክፍልሽ ስትገቢ ምነዉ ባልገረፍኳት እያልኩ እየፀፀተኝ ነዉ አለኝ
.......እኔም አባቴ አንተ ልክ ነህ ጠፋቱ የኔ ነዉ ይቅርታ አድርግልኝ......ከአሁን ቡሀላ ጨዋታ አያታልለኝም መጥፎ ጓደኞችንም አልይዝም የዛሬን ይቅር በለኝ አልኩት አንገቴን አቀርቅሬ
....አባቴም አረ ዛሬ እዚህ ላዝናናሽ የመጣሁት አንቺ ተሸማቀሽ አንገትሽን እንድትደፊ ሳይሆን እኔ የገረፍኩሽን ይቅርታ ልልሽ ነዉ አለኝ፡፡ ከዛም ሁለታችንም ታረቅን አንዴ ሳቅ በሳቅ ደስታ ሆነ ..ከዛም ወደ ጅማ ጥሩ ጊዜ አሳልፈን ተመለስን

  አምስተኛ ክፍል ተምረን ጨረስን እኔ በምማርበት ጊዜ ክረምት ላይ የረመዷን ፆም ያዝን ....እኛ ሰፈር የሚገኘዉ ኑር(አጅፕ) መስጂድ ተራዊህን ለመስገድ አንዲት የሰፈራችን ልጅ ጋር ተራዊህ አብረን ሂደን አብረን ወደ ቤት እንመለሳለን ፡፡

ረመዷን አጋምሰናል ኑር(አጅፕ) መስጂድ ኢሻን ልንሰግድ ተቀምጠን .....ልጅቶ እንደዚህ አለችኝ
.......ነዋል የሆነ ነገር ልንገርሽ አዳምጪኝ ?? አለችኝ
....እኔም ..ምንድን ነዉ??ንገሪኝ አልኳት እናቴ እኮ """ #ነዋል " ..........."ብላኛለች.. አለችኝ ...

ይሄንን ስትነግረኝ ፍዝዝ ድንዝዝ ብየ ቀረሁ መሬት የዋጠኝ ነዉ የመሰለኝ ላቤ በግንባሬ ችፍ ችፍ ሲል ይታወቀኛል......እራሴን መቋቋም አቃተኝ ..ጭንቅላቴ ፍልፍል ቋጥኝ ዲንጋይ ይመስል በጣም ከበደኝ...
መስጊድ እስከ መሆኔ ዘንግቸዋለሁ...

   ያቺ ልጅ በልጅነቴ የሰደበችኝ አባቴ በሽጉጥ እገላለሁ ያለዉ ሚስጥር ሙሉ በሙሉ እየተገለጠልኝ መጣ.....


  የተደበቀዉ ሚስጠር ምን ይሆን???

#ክፍል
ይ......ቀ........
.....ጥ.......ላ..........ል



·¨: ❀ share
           `·.     t.me/Islam_and_Science
t.me/Islam_and_Science
  •════••• •••════•
  
1.9K viewsedited  07:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-08 10:25:45 አሳዛኝ እዉነተኛ ታሪክ
 
የታሪኩ ርዕስ
#የሆድ_ዉስጥ_ፉም_እሳት
      #ክፍል ☞ ሁለት

ፀሀፊ ☞ #አሚር_ሰይድ



 የቤት ሰራተኛችን እያለቀሰች እንዲህ አለችኝ፡- ነዋል አሁን ለአንቺ መንገር አልችልም ገና ልጅ ነሽ ....የወር አበባ ማየት ስጀምሪ  የዛን ጊዜ እነግርሻለሁ እንድነግሪሽ አታጨናንቂኝ አለችኝ እያለቀሰች ፡፡
...እኔም መንገር ካልፈለክሽ አላስገድድሽም አትጨናነቂ አልኳት ፡፡

እሷን ማጨናነቅ አልፈለኩም.. በቤት ሰራተኛችንም አልፈረድም ለምን እኔ እና አባቴ በጣም እንቀራረባለን ይሄ ሚስጥር እሷ እንደነገረችኝ ከአወቀ አባቴ ጋር እንደሚጣሉ አቃለሁ .......
  
የሚገርማችሁ እኔ ሳድግ እቤት ጥሩ ኑሮ ብንኖርም ብር ብቻ ለሰዉ ልጅ ደስታን አይፈጥርም እናት እና አባቴ ሁሌ እንደተጣሉ እንደተጨቃጨቁ ነበር... በሰላም ሳይጣሉ ያደሩበትን ቀን መቁጠር ይቀላል፡፡ እኔ ታዳ ማታ ማታ በተጣሉ ቁጥር እኔ መጨነቅ መጠበብ ነዉ ስራየ..

    ሁሌ ታዳ እናቴ አባቴን በነገር ስትወጋዉ ከሳሎን ተነስቶ ሌላ ክላስ ገብቶ ብቻዉን ቁጭ ይላል.....እኔም ለአባቴ እራቱን ይዤ ያለበት ክላስ እሄዳለሁ ... አባቴም ፀጉሬን እያሻሸ እንዲህ ይለኛል  .....ነዋልየ የአይኔ ማረፊያ እናትሽ ጋር ብዙ ቀን ለመፋታት አስባለሁ ግን አንቺ ትዝ ትይኛለሽ እኔና እሷ ተፋተን አንቺ ስትሰቃይ አባቴን ወይ እናቴ ናፈቁኝ እያልሽ ስትሰቃይ በአይኔ እየታየኝ እንደገና እተወዋለሁ....እኛ ስንጣላ አትጨናነቂ መኝታ ክላስ ግቢ ብዙ ነዉ ሚስጥሩ ነዋል ይለኛል፡፡

_እናቴ ደግሞ እንዲህ ትለኛለች.......በሂወቴ አንቺን ካረገዝኩ ጊዜ ጀምሮ አሁን ድረስ የተረገመ ሒወት ዉስጥ ነዉ የገባሁት ምነዉ ተወልደሽ ባልነበር ትለኛለች እየተናደደች ...
.......እናቴ ከምነግራችሁ በላይ በጣም ሀይለኛ ቁጡ ዉሀ ለምን ቀጠነ ብላ የምትጨቃጨቅ ...ለሰዉ በቀላሉ የማትመለስ ናት ፡፡ እኔን ለራሱ ስትናገረኝ ሁሌም ቢሆን ለኔ ክብር የላትም ቃላቶችን መጥና ከአፏ መወርወር አትችልም ... በተዘዋዋሪ ደግሞ አባቴ አስተዋይ እረጋ ያለ ነገሮችን በትግስት የሚያልፍ ለቤተሰቡ ክብር ያለዉ እና በተናደደ ሰአት ደግሞ ፊቱ ለመቅረብ የሚፈራ ቁጡ ሀይለኛ ነዉ ግን ለነገሮች ሁሉ አይቸኩልም ፡፡ አባቴ ትዳሩ እንዳይበተን ተረጋግቶ ይዞት ነዉ እንጂ እንደ እናቴ ሀይለኝነት ትዳሩ ፈራሽ ነዉ ፡፡

ትዳር ማለት የአንዱን ጎዶሎ አንዱ ይሞላል ማለት ይህ ነዉ፡፡ አባቴ የእናቴን ጎዶሎ እየሞላ ትዳራቸዉ እንዲቀጥል አስተዋፅኦ አድርጓል፡፡
እናቴ ይሄን የነብዩ ሀዲስ የረሳችዉ ይመስለኛል
★★★ተወዳጁ የአላህ መልዕክተኛ ነብዩ ሙሀመድ ሰ.ዐ.ወ እንዲህ ብለዋል ፡-በሚስት ላይ ያለባት ከባዱ ሀቅ የባሏ ሀቅ ነዉ..በወንድ ላይ ደግሞ ያለበት ከባዱ ሀቅ የእናትና አባቱ ሀቅ ነዉ..በማለት የባል ሀቅ ምን ያህል ከባድ እንደሆነ ለማሳየት ሞክረዋል..

ነብዩ ሰ.ዐ.ወ በሌላ ዘገባቸዉ ማንኛዉም ሴት ባሏ እርሷን እየወደዳት በርሷ ላይ ተደስቶ ከሞተች ጀነት ትገባለች...ብለዋል፡፡ እናትሽ ፀባዯን አላህ ያስተካክልልኝ ብላችሁ እስኪ ዱአ አድርጉልኝ

  
    በትርፍ ሰአቱ ቁርአን ቤት እየሄድኩ ስቀራ  ኡስማን ከሚባል ልጅ በፍቅር ወደኩኝ........በፍቅር ስል የሌላ እንዳታደርጉት በልጅነት ስናድግ በጣም የምንቀራረብ ልጆች ነን፡፡ አንድ ቁርአን ቤትና ትምህርት ቤት ነን
  የኡስማን አባት እና እናት የመንግስት ሰራተኛ ናቸዉ .......ኡስማን አንድ እህት አለችዉ ... ቁርአን የሚያቀራን ሸህ ስለሚገርፉን መድረሳ እንገናኝና የኡስማን ቤተሰቦች እቤት ካሉ ቁርአን እንቀራለን ግን እቤት ከሌሉ ዛሬ የሉም ስራ ናቸዉ ከተባለ ቁርአናችንን መቅራት ትተን አሱር አዛን እስከሚል ድረስ እነ ኡስማን ቤት ሂደን ስንጫወት ስንደባደብ እንዉላለን ....አሱር አዛን ሲል እኔ ወደ ቤቴ ተመልሼ ቁርአን የቀራሁ መስየ እሄዳለሁ፡፡

ኡስማን ጋር ያዉ የልጅነት ነገር መጫወት መደባደብ እንጂ ሌላ ነገር የለም ግን የእቃቃ ባል ይባል የለ ....ኡስማን ጋር በልጅነታችን በጣምምም እንዋደዳለን፡፡
  
አባቴ ከትምህርት መልስ ቁርአን ቤት እንድቀራ የፈለገዉ የሰፈር ልጆች ጋር እንድቀራረብ ስለማይፈልግ ነዉ....ከሰፈር ልጅ ጋር አብሬ አላደኩም የወንድም የሴትም የሰፈር ልጅ ጓደኛ የለኝም፡፡ ለምን ያቺ ልጅ ከሰደበችኝ ቡሀላ ከሰፈር ልጆች ጋር እኔም መጫወት እየከበደኝ መጣ .....

አንዳንዴ ብቸኝነት ሊዉጠኝ ሲደርስ ልጆቹ ጋር ልጫወት ስቀርባቸዉ የሚጫወቱትን ጨዋታ ትተዉ ይነሱና እኔን ብቻየን ጥለዉኝ ይሄዳሉ
.....እኔም ስማቸዉን እየጠራሁ ለምን ትሄዳላችሁ??አብረን እንጫወት እንጂ ??? ስላቸዉ
..........እነሱም ቤተሰቦቻችን አንቺ ጋር እንዳንጫወት ከልክለዉናል አንቺ ጋር አንጫወትም እያሉኝ ጥለዉኝ ይሄዳሉ..........እኔ ለመጫወት ወደ ልጆቹ ሲሄድ እነሱም ይሸሹኛል ወይ ክፉ እድል.......
 
   ከአሱር ቡሀላ ከቁርአን ቤት ስመለስ እቤት እየመጣ ትምህርት የሚያስጠናኝ አንድ ልጅ አለ........ከዛ ዉጭ ግቢ ዉስጥ ታናሽ ወንድሜ እና እህቴ ጋር እየተጫወኩ ነዉ ጊዜየን የማሳልፈዉ፡፡


ጊዜዉ በቀልዱም በምሩም ቁሞ አይጠብቅም   ቁርአን ቤት ሄድኩኝ እያልኩ ስጫወት መዋል ከጀመርኩ ሶስት አመት ሆነኝ ፡፡ ኡስማን እና እህቱ ጋር ከሁለተኛ ክፍል ጀምረን ነበር ቁርአን ቀራሁ እያልኩ መኖሪያ ቤታቸዉ እየሄድኩ የምጫወተዉ
 
ጉድ እና ጅራት ከስተቡሀላ ነዉ አይደል የሚባለዉ መቼም ይሄ ጉድ ተደብቆ አልቀረም....አንድ ቀን አባቴ ቁርአን ቤት መጥቶ ሸህየዉን ስለእኔ ሲጠይቃቸዉ ብዙ ቀን እንደማልመጣ እና እነ ኡስማን ቤት ስጫወት እንደምዉል መረጃዉ ደረሰዉ
  
እቤት ስገባ------- አባቴ ተቆጥቶ ፊቱ የእሳት ፉም መስሎ ጠበቀኝ.........
   
.... ነዋል ነይ ቁጭ በይ አለኝ በንዴት
......እኔም እሺ ብየ ቁጭ አልኩኝ.
...... ለስንት ደረጃ ትደርሻለሽ እያልኩ አንቺ ቁርአን ቤት ነኝ እያልሽ ሶስት አመት ስቀልጂ መቆየትሽን ዛሬ ቁርአን የሚያቀራሽ ኡስታዝ ነገረኝ....እንዴት እንደዚህ ትሰሪያለሽ ??? አለኝ
....እኔም ደንግጬ አፌ ተያያዘ የምመልሰዉ ጠፋኝ

አባቴም የመኖሪያ ቤታችንን በር ቆልፎ ለመጀመሪያ ጊዜ ገረፈኝ ....ከቀበቶ አልፎም እጄን አስሮ በርበሬ አጠነኝ

...አባቴ ከተናደደ ተናደደ ነዉ ብጮህ ብጮህ የሚገላግለሉኝ ሰዎች ወደ ቤት መግባት አልቻሉም.. አባቴ ገርፎ በርበሬ ከአጠነኝ ቡሀላ በሩን ከፈተዉ እና ጥሎኝ ሄደ
    
እናቴ ጎረቤት እና የቤት ሰራተኛችን ተሰብስበዉ ቢያባብሉኝ ቢያባብሉኝ እምባየ ሊቋረጥ አልቻለም

.........ከዚህ ቀን ቡሀላ አድቤ ቁርአን ቤት እየሄድኩ መቅራቴን ቀጠልኩ ... ከነኡስማን እና እህቱ ጋር ለጊዜዉም ቢሆን ጓደኝነታችንን ሰረዝን...


አባቴ እኔን ወደ ሶሰት ቀን የሚሆን አኮረፈኝ ...እኔም መልሼ አይኑን ማየት ፈራሁ ፡ አባቴ ሲመጣ ተጠምጥሜ እንደማልስመዉ ..አሁን ግን የእሱ መምጫ ሰአት ሲደርስ አይኑን ማየት እየፈራሁ መኝታ ክፍሌ እገባለሁ፡፡
  
ከሶሰት ቀን ቡሀላ አባቴ ነዋል ነይ ዛሬ ይዠሽ የምሄድበት ቦታ አለ አለኝ
...እኔም እሺ ብየ  አባቴ ጋር መኪናዉን እየነዳ ከጅማ በ45Km በቅርብ እርቀት የምትገኘዉ ወደ አጋሮ ከተማ አባቦቃ መናፈሻ ወስዶ ሲያዝናናኝ ሲያስደስተኝ ዋለ
1.8K viewsedited  07:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ