Get Mystery Box with random crypto!

ሕያው ቃል

የቴሌግራም ቻናል አርማ hiyaw_qal — ሕያው ቃል
የቴሌግራም ቻናል አርማ hiyaw_qal — ሕያው ቃል
የሰርጥ አድራሻ: @hiyaw_qal
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 7.89K
የሰርጥ መግለጫ

''ነዋ ወንጌል መንግሠተ ሰማያት "፦ ወደ መንግሥተ ሰማያት የምታገባ ወንጌል እንሆ። "

Ratings & Reviews

4.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-08-20 21:06:44 ቀኑ ያንተ ነውና እንደሰትበት ዘንድ፣ ሌሊቱም ያንተ ነውና እናርፍበት ዘንድ፣ ክረምቱም ያንተ ነውና እናቅድበት ዘንድ፣ በጋውም ያንተ ነውና እናጭድበት ዘንድ እርዳን! በአማኑኤል ስምህ በፈሰሰው ደምህ። አሜን

ይቀላቀሉ ➙ @hiyaw_qal
ይቀላቀሉ ➙ @hiyaw_qal
2.7K viewsⒷaⒷa, 18:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-20 21:01:03
2.6K viewsⒷaⒷa, 18:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-19 20:33:32
ቡሄ ለምን እናከብራለን ?

በደብረ ታቦር ያበራው ኢየሱስ የሙሴም የኤልያስም ጌታ ነው። አብ ከሰማይ "እርሱን ስሙት" ያለው ኢየሱስ የአዲስ ኪዳን ቃል እና ሕይወት እርሱ ብቻ ስለሆነ ነው። ሰው ኢየሱስን ከሙሴ እና ከኤልያስ ጋር ቢያመሳስሉትም ኢየሱስ ግን እኩያ የሌለው የአብ አንድያ ልጅ እና አምላክ ነው። ሙሴም ኤልያስም ሕይወት አልሰጡም አላሰጡምም። ነገር ግን በሰዎች ልብ ውስጥ ከእግዚአብሔር ልጅ ከኢየሱስ እኩል ክብር ነበራቸው። እግዚአብሔር አብ ደግሞ ኢየሱስን አልቆ ማሳየት ፈለገ። በሰማይም ሆኖ ሙሴና ኤልያስ በተገኙበት ሊሰማ የሚገባው አሁን ተራው የኢየሱስ መሆኑን "እርሱን ስሙት" በሚል ግርማ ያለው ቃል ከሰማይ አሰማ። ሐዋርያትም ይሄን ከሰሙ በኋላ ትኩረታቸውን ሙሉ በሙሉ ኢየሱስ ላይ አደረጉ። ጌታም ሞቶ እስኪነሳ ድረስ ያዩትን ነገር ለማንም እንዳይናገሩ አስጠነቀቃቸው። ምክንያቱም ኢየሱስ ከኤልያስም ከሙሴም እንደሚበልጥ ከተሰማ ክርስቶስ አይሰቀልም ምክንያቱም ኢየሱስ አምላክ መሆኑን ካወቁ አይገድሉትምና። ጌታ ግን ሞቶ የማዳን ስራውን መፈጸም እንዳለወት ያውቃል። ሞቶ በደሙ መፍሰስ እኛ መዳን አለብን ምክንያቱም ደም ካልፈሰሰ የኃጢያት ስረየት የለምና "ዕብ 9፡22"።

ጌታ ሞቶ ከተነሳ በኋላ (ድነትን ከፈጸመ በኋላ) ግን ሐዋርያት ያዩትን እና ከአብ የሰሙትን ማሰማት ጀመሩ። ይህ የአብ አላማ አለምን በክርስቶስ ለመጠቅለል ከማሰቡ ጋር (ኤፌ 1፡10) አንድ ነው። ምክንያቱም ኢየሱስ ከዚህ በፊት እንደተላኩት ነብያቶች አይደለም። ያለማንም አጋዥነት ብቻውን ሊያድን እና ወደ አብ የሚያቀርብ ደግሞ የአብን ኃሳብ እንከን በሌለበት አሰራር ፈጽሞ አብን ያስደሰት እና ሊያስደስት የመጣ ብቸኛ አዳኝ ስለሆነ በእርሱ የሚያምኑትን ፈጽሞ ስለሚያድናቸው ይህን አደረገ።

https://t.me/Hiyaw_qal
3.9K viewsⒷaⒷa, edited  17:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-17 13:23:44 “ነገር ግን እርሱ በብርሃን እንዳለ በብርሃን ብንመላለስ ለእያንዳንዳችን ኅብረት አለን።” / 1ኛ ዮሐንስ 1፥7/

ከእግዚአብሔር ጋር ኅብረት ማድረግ ማለት እርሱ ማወቅ ፣ማፍቀርና ልጁ መሆን ማለት ነው ። ከእርሱ ጋር እውነተኛ ኅብረት ካለን በብርሃን እንኖራልን ። በጨለማና በኃጢአት የሚኖር ግን ከእግዚአብሔር ጋር ኅብረት የላቸውም ። ከእግዚአብሔር ኅብረት አለን ብለው ነገር ግን በኃጢአት ውስጥ ከተመላለሱ የሚኖሩትም በእውነት አይደለም ሐሰተኞች ናቸው ።እውነት የምንናገረው ብቻ ሳይሆን የምናደርገውና የምንኖረው ነው ። ሰለዚህም በእውነት መኖር አለብን ። በእውነትና በመንፈስ እግዚአብሔርን ማምለክ አለብን ። (የሐ 4:23) ። እውነት የሕይወት መንገድ ነው ። በእወነት ከኖርን ማለትም ከእግዚአብሔር ጋር ኅብረት ካለን ሁለት ነገሮች ይሆናሉ ። በመጀመሪያ እርሱ በእርሳችን አንድነት ይኖረናል በሁለተኛ ደረጃ የልጁ የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ከኃጢአት ሁሉ ያነጻናል ። “ነገር ግን እርሱ በብርሃን እንዳለ በብርሃን ብንመላለስ ለእያንዳንዳችን ኅብረት አለን፥ የልጁም የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ከኃጢአት ሁሉ ያነጻናል።” /1ኛ ዮሐንስ 1፥7/ ።

Facebook: https://www.facebook.com/103351765227313/posts/pfbid035mrCdvJhbekf2HguvxTX8L1MgXrHBPACkJVoxsc4wgayHqWiyjbz4ARLxjSnRfYjl/?app=fbl :Telgram: https://t.me/Hiyaw_qal
Telgram: https://t.me/ortohodox_new_mezmur
3.3K viewsⒷaⒷa, edited  10:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-16 18:33:10 “ፍቅራችሁ ያለ ግብዝነት ይሁን ።
— ሮሜ 12፥9

በክርስትና ሕይወት ውስጥ የመጀመሪያው ትልቁ መመርያ ፍቅር ነው ። “ፍቅር የሌለው እግዚአብሔርን አያውቅም፥ እግዚአብሔር ፍቅር ነውና ይላል ።ለለ መጸሐፍ ቅዱስ ፍቅራችሁ እውነተኛ ይሁን ይለናል ። ይህ እውነተኛ ፍቅር የሚመነጨው ከውስጣዊ ሰውነታችን ማለትም ከመንፈሳችን ነው ። ፍቅራችን ውጪዊ ከሆነ የሐሰት የግብዝነት ፍቅር ይሆናል ። ነገር ግን ይህ ፍቅር አይቆይም ። ፍቅሩ ሐሰተኛና ግብዝ የሆነ ሰው የራሱን ጥቅምና ምቾት ብቻ ነው የሚፈልገው ። ግን ፍቅሩ እውነተኛ የሆነ ሰው የእግዚአብሔር ጥቅምና የሌሎችን ምቾት ነው የሚፈልገው ። ፍቅር ይታገሣል፥ ፍቅር ቸርነትንም ያደርጋል፤ ፍቅር አይቀናም፤ ፍቅር በራሱ አይመካም፥ አይታበይም፤ የማይገባውን አያደርግም፥ የራሱንም አይፈልግም ለስው ነወ የሚኖረው ፥ አይበሳጭም፥ በደልን አይቆጥርም፤ ከእውነት ጋር ደስ ይለዋል እንጂ ስለ ዓመፃ ደስ አይለውም፤ ሁሉን ያምናል፥ ሁሉን ተስፋ ያደርጋል፥ በሁሉ ይጸናል። ይህ ነው እውነተኛ ፍቅር

Facebook: https://www.facebook.com/103351765227313/posts/pfbid035mrCdvJhbekf2HguvxTX8L1MgXrHBPACkJVoxsc4wgayHqWiyjbz4ARLxjSnRfYjl/?app=fbl :Telgram: https://t.me/Hiyaw_qal
Telgram: https://t.me/ortohodox_new_mezmur
3.2K viewsⒷaⒷa, edited  15:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ