Get Mystery Box with random crypto!

ሕያው ቃል

የቴሌግራም ቻናል አርማ hiyaw_qal — ሕያው ቃል
የቴሌግራም ቻናል አርማ hiyaw_qal — ሕያው ቃል
የሰርጥ አድራሻ: @hiyaw_qal
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 7.89K
የሰርጥ መግለጫ

''ነዋ ወንጌል መንግሠተ ሰማያት "፦ ወደ መንግሥተ ሰማያት የምታገባ ወንጌል እንሆ። "

Ratings & Reviews

4.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-31 16:06:32 ምዕራፍ ሁለት አለቀ
ይቀጥላል
249 viewsⒷaⒷa, 13:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 16:06:32 የገላትያ መልዕክት ማብራሪያ/ ክፍል 6/

የአይሁድ ሕግ ብቁ አለመሆኑ/ ገላ 2:15-21/

15-16 ጳውሎስ ንግግሩን በመቀጠል ለጴጥሮስና በገላቲያ ለነበሩ አይሁድ ክርስቲያኖች «እኛ አይሁዳዊ ነን ኃጢአተኞች የሆኑ አረማውያን አይደለንም »ይላል በአይሁድ አመለካከት ከሕዛብ ሁሉ የአይሁድን ሕግ ሰለማይከተሉ ኃጢአተኞች እንደሆኑ ይቆጠራል ። ጳውሎስ የሚናገረው በአይሁድ አመለካከት ነው ። ነገር ግን እኛ ክርስቲያኖች የሆንን አይሁድ እንኳ ሰው ሕግን በመጠበቅ እንደማይጸድቅ እናውቃለን ይላል። አይሁድ እና አሕዛብ ጻድቅ ተብለው ሊጠሩ የሚችሉት በኢየሱስ ክርስቶስ ካመኑ ብቻ ነው ። /ሐዋ 15:11/ ።ጳውሎስ ከመጀመሪውኑ ለገላቲያ ሰዎች ያስተማረው እውነተኛ ወንጌል ይህ ነው ። ካዲያ የገላትያ ክርስቲያኖች በኢየሱስ በማመን ከጸደቁ በኃላ አሁንም ለመጽደቅ የአይሁድን ሕግ መፈጸም ያስፈልጋል ወደሚለው እንዴት ዞር አሉ ? ይህ ሊሆን ይገባል ።

አንድ ሰው ለድህነት የሚያስፈልገው ምን እንደሆነ ሁላችንም ጠንቅቀን ልናውቅ ይገባል ። በመጀመሪያ መልካም የሆኑ ነገረ ሁሉ ከእግዚአብሔር ጸጋ የሚመጣ እንደሆነ ማወቅ ። ከእግዚአብሔር ጸጋ ማለትም ከፍቅሩ የተነሳ ክርስቶስ ሰዎችን ለማዳን ወደ ምድር እንደመጣ ። አይሁድ ይሁን አረማዊ ሰው ሁሉ ኃጢአተኛ ነው ። /ሮሜ 3:23-23/ ። ስለዚህ ሁሉም ሰው የኃጢአት ቅጣት ከሆነው ከዘላለም ሞት የሚያድነው አዳኝ ያስፈልገዋል ።/ ሮሜ 6:23/ ። ምህረት የማይገባን ኃጢአተኞች ሳለን ክርስቶስ ስለኛ ሞተ ። ክርስቶስ የእኛን ቅጣት ስለ ተቀበለልን በእርሱ ያመንን እኛ በእግዚአብሔር ዓይን ጻድቅ ሆነን እንጂ እንደ ተፈረደብን ሰው አንቆምም ። ይህም ሁሉ የእግዚአብሔር ጸጋ ውጢት ነው ።

ታዲያ ሰው ለመዳን ምን ማድረግ አለበት ? በክርስቶስ ማመን አለበት ። የእግዚአብሔር ጸጋ ጸጋ መቀበል ይኖርበታል ። እግዚአብሔር ይህንን ስጦታ ለምስጠት እጁን ዘርግቷል እኛ ስጦታውን መቀበል ይኖርብናል ። እምነት እጅን ዘርግቶ የእግዚአብሔርን ስጦታ የመቀበል ሁኔታ ነው ። ለዚህም ነው ጳውሎስ ለኤፌሶን ሰዎች ሲጽፍ «ጸጋ በእምነት አድኖአችኋል ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ እንጂ ከእናተ አይደለም ያለው ። የእኛ እምነት የእግዚአብሔር ጸጋ ለድህነታችን አስፈላጊ ነው ። በክርስቶስ ስናምን የእግዚአብሔር ጽድቅ እንቀበላለን ። ምንም ጥፋት እንደሌለበት ጻድቅ ተብለነሰ እንጠራለን ። /ሮሜ 5:1-2/ ። ስለዚ እግዚአብሔር ባለፈው ኃጢአታችን አይቆጣም ። ይልቁኑ ይቅርታውን ሰጥቶን ልጆቹ ያደርገናል ። በክርስቶስ ባመንን ቅጽበት ጻድቅ ሁነን ድኅነታችንን እናገኛልን ። ድህነትን በማግኘታችን የዘላለም ሕይወት እናገኛልን

ስለዚህ ለመዳን በመጀመሪ ጻድቃን መባል አለብን ። ለመጽደቅ በክርስቶስ ማመንን ይኖርብናል ። በክርስቶስ ለማመን ደግሞ በመጀመሪያ የእግዚአብሔር ስጦታ መቀበል አለብን ። እግዚአብሔር ዓለምን ከመፍጠሩ አስቀድሞ ጠርቶናል ።/ኤፌ 1:4/ ።ድህነታችን ፣ ጽድቃችን ፣ እምነታችንና መጠራታችን ሁሉ እጅግ ጥልቅ ከሆነ ከእግዚአብሔር ጸጋ የሚመነጩ ናቸው ። ሕግጋቶች ወይም ሰው ሰራሽ ወጎች በመፈጸም ድህነታችንን ለማግኘት አንሞክር ። በሰራነው ስራ ጻድቅ መባል አንችልም እንዲውም በስራችን ጽድቅን ለማግኘት መጣር የክርስቶስ ጸጋን መቃወም ነው ።

በቁ.ር.16 መጨረሻ ላይ ሕግን በመጠበቅ ማንም አይጸድቅም ሲል ተናግሯል ። ይህ ለምን ሆነ ? ምክንያቱም ማንም ሕግን እፈጽማለው የሚል አንዲቷን ግን ባይጠብቅ ሁሉን እንደተላለፈ ይቆጠራል ። /ያዕ 2:10/ ። ከትዕዛዛት ሁሉ ልንጠብቀው የማንችለው አትመኝ የሚለውን ነው ።/ዘጸ 20:17/ ። ከአስርቱ ትዕዛዛት ምናልባት ዘጠኙን እንጠብቅ ይሆነል ። አስረኛውን ግን ሁል ጊዜ መጠበቅ አንችልም ። አትመኝ ማለት ክፉ ምኞት አይኑርህ ማለት ነው ።

ቁ .ር 17. በዚህ ስፍራ ጳውሎስ ለአይሁድ አማኞች ይናገራል ። የአይሁድ ክርስቲያኖች ስጋት ውስጥ የከተታቸው የአይሁድ ሃይማኖትን ወግ ባይከተሉ ኃጢአታቸው የከፋ እንደሆነ በማሰባቸው ነው ። ይህ እውነት ከሆነ በክርስቶስ ማመን ወደ ባሰ ኃጢተኝነት ይመራል ማለት ነው ። በሌላ አነጋገር ክርስቶስ ኃጢአትን ይጨምራል ማለት ነው ። በጳውሎስ አባባል ግን ተቃራኒ እውነት ነው ። በክርስቶስ በማመን ብቻ አለመፈለጋቸው በእግዚአብሔር ፊት ይልቁን ኃጢአተኞች ያደርጋችኋል ቅዱስና ንጹሕ የመሆናቸው ብቸኛ መንገድ እምነትን በክርስቶስ ማድረግ የእርሱን ጽድቅ መቀበል ነወ ።

18. በሕግ መመካት እጅግ ኃጢአተኛ ያደርጋል ። ጳውሎስ የፈረሰውን መልሶ የመገንባት ሐሳብ የለውም ። አያስፈልግም ብሎ የተወዉን ሕግና ወግ እንድ ገና አያነሳም ። እንዲ ካደረገ ግን «የጸጋ ሕግን »ዋጋ ማሳጣቱ ነወ ። ይህም ሰዎች ሁሉ የሚጸድቁበትን የክርስቶስ ስራና መስዕዋት መቃወም ነው ። የክርስቶስን ጽድቅ ትቶ በቃት በሌለው ሕግ ለመጽደቅ መጣር በእግዚአብሔር ፊት እንድ ሕግ ተላላፊ ያስቆጥራል ። ምክንያቱም ሕግን በመጠበቅ ማንም ሊጸድቅ አይችልም ።

19.ሕግ በሰው ላይ ከመፍረድ በቀር ለኃጢአተኛ አዱስ ሕይወትን መስጠት አይችልም ። ሕጉ በጳውሎስ ላይ የሞት ፍርድ ፈርዶበት ነበር ። ጳውሎስ በሕጉ በኩል ለሕግ ሙቼ ነበር ይላል ። ነገር ግን ሲሞት ነጻ ይወጣል ። ዳኛ ፍርድ ከሰጠ በኋላ በጉዳዩ ላይ ስራ አይኖረውም ።በወንጀለኛው ላይ ያለው ስልጣን ያከትማል ። ወንጀለኛው ቅጣቱን በመፈጸም ከዳኛ ነጻ ይሆናል በተመሳሳይ መንገድ ጳውሎስ ለሕግ ስለ ሞተ ከሕግ ነጻ ሆኗል ። ሕግ ጳውሎስ ላይ የሞት ፍርድ ከፈረደበት በኋላ ምንም ሊያደርገው አይችልም ። ጳውሎስ በሞቱ ከጌታው ነጻ እንደወጣ አንደ ባሪያ ነው ።ስለዚህ አሁን ከቀድሞ ጌታው ከሕግ ነጻ በመሆኑ ክርስቶስን ለማገልገል ለእግዚአብሔር ለመኖር ነጻነት አለው ። /ሮሜ 6:7 , 7:4/ ። ክርስቶስ በውስጡ ስለሚኖር ጳውሎስ ለእግዚአብሔር ኃይል አለው ።

(ቁ.ር 20) ከክርስቶስ ጋር ተሰቅያለው እዚህ ስፍራ ጳውሎስ የሚሰጠው መስክርነት ምንኛ ጥልቅና አስደናቂ ነው። አንድ ሰው አዲስ መንፈሳዊ ሕይወት ከመቀበሉ በፊት መሞት አለበት (ሮሜ 6:6) ከክርስቶስ ጋር መሰቀል የኃጢአተኛው ማንነታችን መሞት ማለት ነው ። የዚህ ጊዜ የክርስቶስ ሕይወትና ባሕርይ በውስጣችን ይሞላል የእርሱ መንፈስ የሆነው መንፈስ ቅዱስ ውስጣችን ይገባል ። በመንፈስ ቅዱስም ቅድስናና የጽድቅ ሕይወት ለመኖር ኃይልን እናገኛለን በሕይወት የሚኖረው የቀድሞው ኦእኛነታችን ሳይሆን ክርስቶስ ነው ። የቀድሞው ኃጢአተኛ ማንነታችን ሞቷል ።

እስኪ ራሳችንን ይህን ጥያቄ እንጠይቅ ። በእኔ ውስጥ የሚኖረው ማነው ? የድሮ ማንነቴ ውይስ ክርስቶስ ?

የክርስትና ሕይወት እውነተኛው ትርጉም ክርስቶስ በአማኙ ሕይወት ውስጥ መኖሩ ነው ። በገዛ ፍቃዳችን ሕይወታችንን መኖር የለብንም ። በእምነት ክርስቶስ በውስጣችን እንዲኖር እንፈቅዳለን "ኢየሱስ በኔ ኑሩ እኔም በእናተ እኖራለውና ብሏል " ።/ዮሐንስ 15:4/ ሰለዚህ ኢየሱስ በእኛ ውስጥ ስለሚኖር እንደ ኢየሱስ መኖር እንጀምራለን ። የዚያን ጊዜ ሌሎች ሰዎች ክርስቶስን በእኛ ውስጥ አይተው እነርሱም ክርስቲያኖች ለመሆን ይፈልጋሉ ።

(21) ጳውሎስ " የእግዚአብሔር ጸጋ አልጥልም " ይላል ። ይህም ማለት እንደ ገና ድኅነትን ሕግ በመፈጸም ለማግኘት አልሞክርም ማለት ነው ። ሰው በክርስቶስ በማመን ሳይሆን ሕግን በመፈጸም የሚያድን ከሆነ በእርግጥ ክርስቶስ የሞተው በከንቱ ነው ።
255 viewsⒷaⒷa, edited  13:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 14:11:32 የወንጌል ቀዳሚ መልእክቱ፣ "ሥራ " የሚል አይደለም፤ "በክርስቶስ ተሠርቶልሃልና፣ በተሠራልህ እመን" የሚል ነው። ይህን ያመነ ይሠራ ዘንድ የሚገባ የፍቅር ምላሽ አለው።
882 viewsⒷaⒷa, 11:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 08:26:20
1.1K viewsⒷaⒷa, 05:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 08:54:32 የገላትያ መልእክት ማብራሪያ ክፍል /5/

▹ ጳውሎስ ጴጥሮስን ተቃወመው (2÷11-14)

▹ ጴጥሮስ ወደ አንጾኪያ በመጣ ጊዜ ፊት ለፊት ተቃወሙት ። በዚህ ክፍል በጳውሎስና በጴጥሮስ መካከል ሰለተነሣው ከፍተኛ አለመግባባት እናነባለን ። ጳውሎስ ፊት ለፊት መናገሩን እንጂ አለማማቱን እናስተውላለን ። እኛም እንዲህ ከወንድሞቻችንና እህቶች በሚፈጠረው አለመስምማት ፊት ለፊት እንወቃቀስ ። ወንድማችንንና እህታችንን በማማት ኃጢያት ውስጥ አንግባ ።
ጴጥሮስ ተሳስቶ ነበር ። ስህተት እንዳደረገ ራሱ እንኳን ተቀብሎአል ። ስህተቱም ለራሱም ለሌሎችም የተገለጠ ነው ።

(12) በጳውሎስና በጴጥሮስ መካከል የነበረው አለመግባባት በመሠረታዊ የክርስትና ትምህርት ላይ ሳይሆን ከባሕርይ የተነሳ ነበር ። ከአሕዛብ ወገን የመጡ ክርስቲያኖች የአይሁድ ወግና ሥርዓት የግድ መፈጸም የለባቸውም በሚል ሐሳብ ጴጥሮስ ተስማምቷል ። ከአይሁድ ወገን የሆኑ ጴጥሮስ እንኳን የአይሁድ ወግ አይጠብቅም ። በእርግጥ ኑሮ እንደ አሕዛብ ነበር (በቁ 14) ። የጴጥሮስ ስህተት ምን ነበር ? በቀላሉ በአንጾኪያ ካሉ አሕዛብ ክርስቲያኖች ጋር መብላትን ሰለተወ ነበር ። ይህን ለምን አደረገ ? ከኢየሩሳሌም ወደ አንጾኪያ የመጡ ከንዳንድ አይሁዳውያን «ወንድሞች» አይሁዳውያን ከአሕዛብ (ከአረማዊ) ለምግብ በአንድነት መቀመጥ የለበትም ስላሉ ነው ። እነዚህም ሰዎች ከተገረዙት ወገን የሆኑ አይሁዳውያን ነበሩ ። እነርሱም ለመዳን መገረዝ አስፈላጊ ነው ብለው ያስተምራሉ ። ስለዚህ ጴጥሮስ እነዚህን ሰዎች በመፍራት ልክ ከአሕዛብ ክርስቲያኖች ጋር በማዕድ ኅብረት እንደማያደርግ ሰው ራቀ ። በአይሁድ አመለካከት አረማውያን «የረከሱ» እንደሆኑ ይቆጥራሉ ። ሰለዚህ አይሁዶች ከአረማዊ ጋር መመገብ እንደ እነርሱ የረከሰ ያደርጋል ብለው ያምናሉ ። አይሁዶች ወደ ክርስትና ከመጡ ብኋላ እንኳን እንዲህ ያለ የተሳሳተ አመለካከት ከአእምሮአችን ቶሎ አይወገድም ። ጴጥሮስ እራሱ ከአረማውያን ክርስቲያኖች ማግለሉ ትክክል እንዳልሆነ ያውቃል ። ወደ ክርስትና የገቡ አይሁዶችና አረማውያን በእግዚአብሔር ፊት እኩል እንደሆኑ ያውቃል (የሐዋ 10÷27-28 ፣ 15÷7-9 ፣ገላ 3÷28) ። ነገር ግን ጴጥሮስ የጥንቱ ፍርሃትና ወግ አሸንፎት ስህተት ላይ ጣለው ። እኛም ከሌላው ክርስቲያን ጋር በብሔር ወይም በቆዳ ቀለም ምክንያት ኅብረት ላለመፍጠር ወይም ላለመመገብ ባንፈልግ በክርስቶስ ላይ ኃጢአት እንደሰራን እንወቅ ።

(13) በአንጾኪያ የነበሩ ክርስቲያን አይሁዶች ከጴጥሮስ ግብዝነት ጋር ተባበሩ ። ይህም ግብዝነት የተባለበት ምክንያት እነዚህ ሰዎች በአንደበታችው አይሁድና አረማዊ በክርስቶስ አንድ ናቸው እያሉ በተግባር ግን ክርስቲያን የሆኑትን አረማውያን የበታችና ርኩስ አድርገው ይቆጥሩፈሯቸው ነበር ። ከዚህም ሁኔታ በተለያዩ መንገዶች ወደተሳሳተ ነገር በቀላሉ እንዴት እንደምንነዳ እናስተውል ። ታላላቅ መሪዎች የሚባሉት ጴጥሮስና በርናባስ እንኳን ስህተት ውስጥ ወድቋል ። መሪዎች ሲሳሳቱ ሌሎችን ወደ ስህተት ይዘው ይገባሉ ። መሪዎች በተለየም ለአዳዲስ ክርስቲያኖች መልካም ምሳሌች ሊሆኑ ይገባቸዋል ። (ማር 9÷24)

(14) በሐዋርያት ሥራ 15÷13-19 እንደ ተገለፀው በኢየሩሳሌም የነበሩት መሪዎች ወደ ክርስትና የገቡት አረማውያን የአይሁድ ሕግ የግድ መከተል እንደሌለባቸው ተስማምተዋል ። አይሁድና አሕዛብ በክርስቶስ በማመን በጸጋ እንደሚድኑ ይህ የወንጌል እውነት ነው ። ጴጥሮስ ከእውነት ጋር ተስማምቷል (የሐዋ 15÷7-11) ። በተጨማሪም እንደ አረማዊ ኑሯል ። አሁን ግን ከአረማዊ ወገን ከመጡ ክርስቲያኖች ጋር ለመብላት አለፈቀደም ። ምክንያቱም አረማውያን «ያልነጹ/ርኩስ» ሰለሚባሉ ነው ። ከጴጥሮስ ባሕርይ እንደሚታየው « የአይሁድ ሕግ ካልተከተላችሁ ከእናንተ ጋር አልበላም » ለአረማውያን በድርጊቱ መናገሩ ነው ። በዚህም መንገድ ወደ ክርስትና የገቡ አረማውያን የአይሁድ ወግ ፣ ሕግ እንዲከተሉ ማስገደዱ ነበር ።

▹ አንዳንድ ገለጻዎች

▹(በቁ.ር 11) አይሁድ በሚለው ቃል ፋንታ አንዳንድ ትርጉሞች «የተገረዘ» ይላሉ ።ይህም በመጀመሪያ በግሪክ መጸሐፍ እንደተጻፈው ሲሆን በትርጉም አንድ ናቸው ።
▹(12) አሕዛብ የሚለው ቃል በመጀመሪያ የግሪክ መጸሐፍ «ያልተገረዙ» የሚል ሲሆን በትርጉም አንድ ናቸው ።
▹(13) ቀኝ እጅን መስጠት (መጨበጥ ) በአብዛኛውን ሕዝብ ዘንድ ኅብረት ምልክት ነው ። በጳውሎስ ዘመንም እንዲሁ ነበር ።
▹(14) አንጾኪያ በሰሜን ሶርያ ዋንኛ ከተማ ነች ። በአንጾኪያ የቤተክርስቲያን መመስረት በሐዋርያት ሥራ 11÷19-25 ላይ ተዘግቦ ይገኛል

ይቀጥላል
ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like, Subscribe , Follow እና Share ያድርጉ :-

Facebook: https://www.facebook.com/103351765227313/posts/pfbid036avLND9y5yFnfpbMcmXf42UYCh1RHeynqpCAAEg58GtPff2PBEMtmdDXWT6beqZFl/?app=fbl Telgram: https://t.me/Hiyaw_qal
Telgram: https://t.me/ortohodox_new_mezmur
1.6K viewsⒷaⒷa, edited  05:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 21:48:29 መዝሙር ልጋብዛችሁ ። እናተም ከወደዳችሁት ሌሎችን ጋብዙ ።
400 viewsⒷaⒷa, edited  18:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 08:59:21 ክርስቲያኖች በቤተክርስቲያን ያሉንን ልንታዘዝ ይገባናል ።

(7-8) ጴጥሮስና ሌሎቹ የእየሩሳሌም ቤተክርስቲያን መሪዎች ለወንጌል ሥራ አደራ እንደተሰጣቸው ጳውሎስም እንዲሁ ተሰጥቶታል ። በኢየሩሳሌም የነበሩት ሐዋርያት ለአይሁድ ወንጌልን እንደሰበኩ ጳውሎስ ለአሕዛብ ወንጌልን እንዲሰብከ ተሹሟል ። ሰለዚህ እግዚአብሔር በሌሎቹ ሐዋርያት እንደሰራ በጳውሎስም ይሰራ ነበር ። ጳውሎስና ሌሎች ሐዋርያት የሰበኩት አንድ ወንጌል ነው ።

(9) የኢየሩሳሌም ቤተክርስቲያን መሪውች በደስታ የጳውሎስና የበርናባስን ሐዋርያነት ተቀብለው ለመስማማታቸው ቀኝ እጃቸውን ሰጧቸው ። ጳውሎስ የተሰጠኝን ጸጋ አውቀው ይላል ። ይህም የሐዋርያነት ጸጋ ነበር (ኤፌ 3÷7-8)። የኢየሩሳሌም ቤተክርስቲያን ዋና መሪዎች ያዕቆብ ፣ ጴጥሮስ (ኬፋ ) እና ዮሐንስ ነበሩ ። እነዚህ ሰዎች ጳውሎስ የቤተክርስቲያን አዕማድ ይላቸዋል ። ዮሐንስ የኢየሱስ ተወዳጅ ደቀመዝሙር በመባይ የሚታወቅ ሲሆን የዮሐንስ ወንጌልና በስሙ የተጻፉትን ሦስት የአዲስ ኪዳን መልእክቶች ጽፎአል ። እነዚህ የኢየሩሳሌም ቤተክርስቲያን መሪዎች ጳውሎስና በርናባስ ለአሕዛብ እነርሱ ደግሞ ለአይሁድ ወንጌልን ሲሰብኩ ተስማምተዋል ። ይህም ጥሩ ቅንጅት ነበር ። አንዳንድ ክርስቲያኖች ለአንድ ሥራ ይጠራሉ ። ልሎች ደግሞ ለሌላ ስራ በእግዚአብሔር ይጠራሉ ። እግዚአብሔር ወደሚልከን ቦታ ለመሄድ ዝግጁ መሆን ይገባናል ።

(10) የእየሩሳሌም ቤተክርስቲያን መሪዎች ጳውሎስን አንድ ነገር እንዲያደርጉ ለመኑት ይህም ድሆችን እንዲያስብ ። መሪዎች ይህን ሲሉ በኢየሩሳሌም ያሉ ችግረኞች ክርስቲያኖች ማለታቸው ነበር ። በአዲስ ኪዳን መጸሐፍት በአንዳንድ ስፍራ ጳውሎስ በአሕዛብ ክርስቲያኖች ዘንድ እየዞረ በኢየሩሳሌም ለነበሩ ችግረኞች ክርስቲያኖች ገንዘብ እንዳሰባሰበ ተጠቅሷል ። (የሐዋ 11÷29-30 ፣ ሮሜ 15÷25-26 )

አንዳንድ ገለጻዎች

ቁጥር (6 ) ላይ ጴጥሮስ በሚለው ስም ፋንታ አንዳንድ ትርጉሞች «ኬፋ » ይላሉ ። ኬፋ በግሪክ ቋንቋ ጴጥሮስ ማለት ነው ።
(7) ኪልቅያ የአሁኗ ደቡብ ቱርክ ስትሆን ፥ በደቡብ ሶሪያ የምትገኝ የሮም ግዛት ነበረች ።

(9) አንዳንድ የአይሁድ ወንዶች በስምንተኛው ቀን መገረዝ ይጠበቅባቸዋል ።( ዘፍ 19÷9-14) ። ጳውሎስ በነበረበት ዘመን መገረዝ አይሁድ መሆንን የሚያረጋግጥ ወጫዊ ማስረጃ ነበር ።

(10) የግሪክ ሰዎች በደቡባዊ አውሮፓ በምትገኝ አገር የሚኖሩ ናቸው ። በአዲስ ኪዳን ዘመን ግሪክ የሮም ግዛት እንዷ ክፍል ነበረች ። የግሪክ ሰዎች አይሁዳውያን አልነበሩም ። የዳበረ ባሕልም አልነበራቸውም ። በዚህም ዘመን በመካከለኛው ምሥራቅ የነበሩ አብዛኞዎቹ ሙሁራን የግሪክ ቋንቋ ይናገሩ ነበር ። አዲሰ ኪዳን በመጀመሪያ የተጻፈ በግሪክ ቋንቋ ነው ።

ይቀጥላል ...........
ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like, Subscribe , Follow እና Share ያድርጉ :-

Facebook: https://www.facebook.com/103351765227313/posts/pfbid036avLND9y5yFnfpbMcmXf42UYCh1RHeynqpCAAEg58GtPff2PBEMtmdDXWT6beqZFl/?app=fbl
Telgram: https://t.me/Hiyaw_qal
Telgram: https://t.me/ortohodox_new_mezmur
838 viewsⒷaⒷa, edited  05:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 08:59:21 የገላትያ መልእክት ማብራሪያ ክፍል /4/

ምዕራፍ 2
የጳውሎስ በሐዋርያት ተቀባይነት ማግኘት (2÷10)

(1) አብዛኛውን የመጽሐፍ ቅዱስ ሊቃውንት በዚህ ቁጥር የተጠቀሰው ወደ ኢየሩሳሌም የተደረገው ጉዞ በሐዋርያት ሥራ 15÷1-29 ከተጠቀሰው ጉዞ ጋር አንድ ነው ይላሉ ። በዚህም ጉዞ ከጳውሎስ ጋር ከተጓዙት አንዱ በርናባስ ነበር ። ይህም ሰው በጳውሎስ የመጀመሪያ ተልዕኮ ጎዞ ላይ የቅርብ አጋሩ ነበር (የሐዋ 9÷27 ፣ 11÷22-26) ። ሌለኛ አጋር ደግሞ በ2ቆሮ 7÷6-7 እና 8÷16-17 ላይ የተጠቀሰውን ወጣቱ ቲቶ ነበር ። በኋላ በአዲስ ኪዳን ውስጥ የተጠቀሰውን « የሐዋርያው መልዕክት «ለቱቶ» ጻፈለት ። ወደ ኢየሩሳሌም የተደረገው ጉዞ ዓላማ በግልጽ ሁኔታ በሐዋርያት ሥራ 15÷1-2 ላይ ተገልጿል ። ጳውሎስ በነበረበት ዘመን ቀድሞ የአይሁድ እምነት ተከታዮች በነበሩት ክርስቲያኖች ወደ ክርስትና በመጡት አሕዛብ መካከል ከፍተኛ የሆነ አለመግባባት የሆነ ተነስቶ ነበር ። የአይሁድ ክርስቲያኖች ወደ ክርስትና የመጡት አሕዛብ የአይሁድን ሕግ መፈጸም አለባቸው የሚል ክርክር ነበራቸው ። (የሐዋ 15÷1-) ጳውሎስ ግን ከአሕዛብ ለሆኑት አማኞች በመወገን የአይሁድ ክርስቲያኖን ትምህርት በብርቱ ተቃውሟል ። የእርሱ ክርክር ከአሕዛብ ወገን ወደ ክርስትና የመጡት ሰዎች የአይሁድ ሕግ የመፈጸም ግዴታ የለባቸውም የሚል ነበር ። ስለዚህም ከኢየሩሳሌም ከአካባቢው ወደ ገላትያ የሄዱት የአይሁድ ክርስቲያኖች የገላትያ ክርስቲያኖች የሙሴን ሕግ መፈጸም እንዳለባቸው ማስተማር ሰለ ጀመሩ ይህን የተሳሳተ ትምህርታቸውን ለመቃወም በኢየሩሳሌም ወደምትገኘው ቤተክርስቲያን መሪዎች ለመሄድ ወሰነ ። ጳውሎስ ወደ ኢየሩሳሌም የሄደው ከተገለጠለት ራእይ የተነሳ ነበር ። ይህም ራእይ ወደ ኢየሩሳሌም መሄዴ እንዳለበት መንፈስ ቅዱስ የገለጠለት ነው ። ጳውሎስ በሕይወት ዘመን ሁሉ ዋና ዋና በሆኑት ጉዳዮች ላይ መንፈስ ቅዱስ በሚገለጥለት ልዩ ራእይ እየተመራ ይሄድ ነበር ። (የሐዋ 16÷6-10፣ 22÷17-18 ፣ 27÷23-26) ። በኢየሩሳሌም መሪዎች ፊትም በአሕዛብ መካከል ሰለሚሰበከው አስታወቀ ። ይህም ወንጌል ምን ነበር ? አንድ ሰው የሚደነው የአይሁድን ሕግ በመጠበቅ ሳይሆን በጸጋ እንደ ሆነ የሚናገሩ በእምነት የሚገኝ የክርስትና የጸጋ ወንጌል ነው ። በኢየሩሳሌም የሚገኙ የአይሁድ ክርስቲያኖች መሪዎች የጳውሎስን ትምህርት ባይቀበሉ የዚያን ጊዜ በእርግጥ የጳውሎስ ስበከት ከንቱ ይሆን ነበር ። እስካሁን ሩጫውን በከንቱ የሚሮጥ ሰው ይሆን ነበር ። ጳውሎስ ለኢየሩሳሌም ቤተክርስቲያን መሪዎች ይህን የተናገረው ለበቻቸው ነበር ። በከተማው ካሉት ከአይሁድ ክርስቲያኖች መካከል አለመግባባትና ብጥብጥ እንዲነሣ ጳውሎስ አልፈለገም ።

(3) ጳውሎስ ከቤተክርስቲያን መሪዎች ጋር ያደረገው ስብሰባ የተሳካ ነበር ። ከነበሩት ዋና ጉዳዮች አንዱ አሕዛብ ክርስቲያኖች እንደ አይሁድ ሕግ መገረዝ አለባቸውው ወይም የለባቸውም የሚል ሐሳብ ነበር ። የአይሁድ ክርስቲያኖች የግድ አስፈላጊ ነው ሲሉ ፥ ጳውሎስ ደግሞ አሰፈላጊ አይደለም ይል ነበር ። በመጨረሻም የኢየሩሳሌም ቤተክርስቲያን መሪዎች በጳውሎስ ትምህርት ተስማሙ ። ይሄንንም ማስረጃ በማድረግ ቲቶን የገረዝ ዘንድ ግድ አላሉትም (ቲቶ የግሪክ ሰው እንጂ አይሁድ አልነበረም ) ቲቶ ባይገረዝም እንደ ክርስቲያን ወንድም ተቀብለውታል ። ዛሬ ለእኛ ይህ ትንሽ ነገር መስሎን ሊታየን ይችላል ነገር ግን በክርስትና ሃይማኖት ታሪክ በኢየሩሳሌም የተደረገው ይህ ስብሰባ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ስብሰባ ነው ። ምክንያቱም ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ሰው የሚድነው የትኛውም ሕግ በመጠበቅ ሳይሆን በጸጋና በእምነት አማካኝነት ብቻ እንደሆነ ያስረዳናል ። ይህ የክርስቲያኖች ወንጌል ነው ። የክርስትና እምነት በዓለም ላይ ካሉ ሃይማኖቶች ለየት የሚያደርገውም ለዚህ ነው ። በሌሎች ሐይማኖት ትምህርት ሰው ለመዳን አንዳንድ ግዴታዎችን ፣ ወጎችን ፣ ሥርዓቶችን መፈጸም ይገባዋል ። እነዚህ ሃይማኖቶች የተመሰረቱት አንደ ሰው በሚያደርገው ጥረት በሚገኘው ዋጋ ላይ ነው ። የክርስትና እምነት ግን ከዚህ ሙሉ በሙሉ የተለየ ነው ። እንደ ክርስቶስ ወንጌል ከሆነ ማንም በስራ ድህነትን ማግኘት አይችልም ። ድህነት በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በማመን የሚገኝ የእግዚአብሔር ጸጋ ነጻ ስጦታ ነው ።

(4) ድህነት ለማግኘት የአይሁድን ሕግ መፈጸም ግድ ነው ብለው የሚያስተምሩትን ጳውሎስ ሐሰተኛ ወንድሞች በማለት ይጠራቸዋል ። እነርሱ እወነተኛ ክርስቲያኖች አልነበሩም ። ጳውሎ ሰለ እነርሱ እንደ ሰላዮች ወደ ቤተ ክርስቲያን ሾልከው ገብተዋአለ ሲል ጽፎአል ። የበግ ለምድ እንደ ለበሱ ተኩላዎች (ማቴ 7÷15) የሴጣን አገልጋዮች ነበሩ ። አዲስ ክርስቲያኖች ነፃነት በመግፈፍ እንደ ገና የሕግ እስረኞች ሊያደርጓቸው ይሞክራሉ ። ሴይጣን ድህነታችንን ሊወስድብን እንደማይችል ያውቃል ። (የሐዋ 10÷7-29) ። ሰለዚህ ይህን ነፃነታችንና ደስታችንን ሊወስድብን ይጥራል ። ሐሰተኛ ወንድሞችን ወይም ሐሰተኛ ነብያትና አስተማሪዎችን እንዴት ልናውቅ እንችላለን ? ሁለት የማወቂያ መንገዶች አሉ ። የመጀመሪያው በሚናገሩት ቃል ማወቅ እንችላለን ። (1ዮሐ 4÷1-2) ። ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነና በሥጋ ወደ ምድር እንደ መጣ የሚያምን ማንኛውም ሰው እውነተኛ ነብይ ነው ። (ሮሜ 10÷9) ሁለተኛው መንገድ በሚሰሩት ሥራ በፍሬአቸው ሐሰተኛ ነብያት እናውቃቸዋለን ። (ማቴ 7÷16-18) ። እወነተኛ ነብያት በተሳሳተ ትምህርት ውስጥ ሊወድቁ ይችላሉ ። አዎ የኢየሱስ ዋንኛ ደቀመዝሙር የነበረው ጴጥሮስ እንዲሁም በርናባስ በዚሁ የአይሁድ መምህራን ትምህርት ስህተት ውስጥ ገብተዋል ። ቢሆንም በእንድ ወቅት ጴጥሮስና በርናባስ ተሳስተው የነበሩ ቢሆንም ሐሰተኛ ወንድሞች አልሆኑም ። በቤተክርስቲያን ውስጥ በመካከላቸው አለመግባባት ሲፈጠር ሌላውን ወገን ሐሰተኛ ወንድሞች ብለን ለመጥራት የሚቸኩሉና የተዘጋጁ አንዳንድ ሰዎች አሉ ። በዚህም መንገድ በወንድሞቻችን ላይ ልንፈርድ አይገባም (ማቴ 7÷1) የሰውን ልብ የሚያው እግዚአብሔር ብቻ ነውና (ማቴ 13÷24-30)

(5) ከአይሁድ ወገን የነበሩት ወንድሞችን የስህተት ትምህርት በመቃወም ጳውሎስ ጸንቶ ቁሟል ። በገላትያ ክርስቲያኖች ብቻ ሳይሆን በክርስቲያኖች ዘመን ሁሉ እወነቱ ተጠብቆ እንዲቆይ ጳውሎስ ለወንጌል እውነት ተሟግቷል ።

(6) ጳውሎስ ወደ ኢየሩሳሌም በሄደ ጊዜ ዋንኞች የሆኑት የቤተክርስቲያን መሪዎች በእርሱ መልእክት ላይ አንዳችም ነገር አልጨመሩም ነበር ። ጳውሎስ የተሰጠውን ስልጣን ተቀብለዋል ። ከአሕዛብ ወገን የመጡ ክርስቲያኖች የአይሁድን ሕግ የግድ መጠበቅ አለባቸው አላሉም ። በኢየሩሳሌም የነበሩት የቤተክርስቲያን መሪዎችና ሐዋርያትን ጳውሎስ ከእርሱ በላይ አድርጎ አልቆጠራቸውም ። ጳውሎስ የሐዋርያነቱን ስልጣን የተቀበለው ከእነዚህ ሰዎች ሳይሆን በቀጥታ ከእግዚአብሔር እንደሆነ እናውቃለን ። እግዚአብሔር ሰዎችን የሚያየው በዓለም ውስጥ ያላቸውን ስፍራ ሳይሆን በውስጣቸው ያለውን መንፈሳዊ ሁኔታ ነው ። ጳውሎስ በዚህ ቦታ የጸፈው ለመሪዎቻችን እንዳንታዘዝ ወይም እንዳናከብራቸው ሳንሆን እንደ ሌሎቹ ሐዋርያት እነርሱ መሪና ሐዋርያ እንደሆነ ማሳየቱ ነበር ። ስለዚህም የእነርሱ ወሳኔ ለመከተል ግዴታ አልነበረበትም ። ይሁን እንጂ ዋንኞች ያልሆንን
719 viewsⒷaⒷa, 05:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 23:26:59
እኛ ስንጸልይ እግዚአብሔር ይሰማል
እኛ ስንሰማ እግዚአብሔር ይናገራል
እኛ ስናምን እግዚአብሔር ይሰራል

ጸልዩ!!
897 viewsⒷaⒷa, 20:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 17:21:30 ኢየሱስ ናዝራዊ

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአብሮ አደጎቹና ዘመዶቹ ተራ ሕልም ያለው ተደርጎ ይታያል ። ፖለቲከኞች ለወንበራቸው የሚያሰጋ የዙፋን አደጋ አድርገው ቆጥረውታል ። የሃይማኖት አባቶችም በትክክል አገልግለው የሚያገኙትን እንጀራ በግብዝነት ተውኔት ከሕዝቡ ለማግኘት ፈልገዋል ፣ በዚህም ኢየሱስን የጥቅማቸው ተጋፊ ብለው በመፈረጅ ከቅናታቸው ጥልቀት የተነሣ ለሞት ከጅለውታል ። ደቀ መዛሙርቱም የተጨቆነ ኑሮ መኖር ሰልችቷቸው ነበርና የዳዊትን መንግሥት አስመላሽ አድርገው ገምተውታል ። ባለጠጎችም የሀብት ተቀናቃኝና የምቾት እንቅፋት ብለው ሰይመውታል ። ማኅበረሰቡም ሰው የማይመርጥ ዘማዊና ቀራጭ ወዳድ አድርጎ ሥሎታል ። ኢየሱስ ጌታችን ለብዙዎች ጥያቄ ላመኑበት ግን መልስ ነው ።

ዲያቆን አሸናፊ መኮንን
Facebook: https://www.facebook.com/103351765227313/posts/pfbid035mrCdvJhbekf2HguvxTX8L1MgXrHBPACkJVoxsc4wgayHqWiyjbz4ARLxjSnRfYjl/?app=fbl :Telgram: https://t.me/Hiyaw_qal
Telgram: https://t.me/ortohodox_new_mezmur
1.1K viewsⒷaⒷa, 14:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ