Get Mystery Box with random crypto!

Apostolic Church of Ethiopia (የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያን)

የቴሌግራም ቻናል አርማ onegodonlyjesus — Apostolic Church of Ethiopia (የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያን) A
የቴሌግራም ቻናል አርማ onegodonlyjesus — Apostolic Church of Ethiopia (የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያን)
የሰርጥ አድራሻ: @onegodonlyjesus
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.81K
የሰርጥ መግለጫ

Apostolic Church of Ethiopia believe in One God, Water Baptism
in the name of Jesus Christ
#እስራኤል_ሆይ_ስማ_አምላካችን_እግዚአብሔር_አንድ_እግዚአብሔር_ነው
#ዘዳ 6:4
☞ @onegodonlyjesus1
☞ @onegodonlyjesus
🗣ስብከቶች🗣
✍የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች✍
🎵 መዝሙሮች🎶
🗣መንፈሳዊ ትረካዎች🗣
📝 ሕይወት ለዋጭ.....

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-06-26 22:53:49
671 views19:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-26 22:53:41 “እነሆ፥ ፈጥኖ ቢነጥቅ የሚከለክለው ማን ነው? እርሱንስ፦ ምን ታደርጋለህ? የሚለው ማን ነው?” (ኢዮብ 9፥12)።
ቢሾፕ ተክለማሪያም ገዛኸኝ የተወለዱት በአድዋ አውራጃ በአምባይሰይነይቲ ወረዳ ልዩ ቦታ ጮማእምኒ በሚባል ስፍራ ሚያዝያ 11 በ1929 ዓ.ም ተወለዱ፡፡ በልጅነታቸው ብዙ የሕይወት ውጣውረድ ያጋጠማቸው ሲሆን በዘመድ ቤት ሆነው በአድዋ ከተማ የመጀመሪያና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በወር 15 ብር ከመንግሥት እየተከፈላቸው ተከታትለው በከፍተኛ ማዕረግ አጠናቅቀዋል።
ቀሪውን ሕይወታቸውን በሙሉ እግዚአብሔርን በመፈለግ የእግዚአብሔር ጥሪ ገና በ14 ዓመት ዕድሜአቸው የመጣላቸው በመሆኑ ምላሽ ለመስጠት አንገታቸውን ወደ መንፈሳዊ ነገር አዙረው አንድ ወጣት ጓደኛቸው እሳቸውንና መጽሐፍ ቅዱስን አስተዋወቃቸው። ስለ መንፈስ ቅዱስም ሙላት ከሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ 2 እየጠቀሰ ሲያስረዳቸው ወ/ም ተክሌም ጥማት አደረባቸው፤ ፍለጋውን ይቀጥሉና ከብዙ ምኞትና ፍለጋ በኋላ መንፈስ ቅዱስ ተሞሉ።
በመቀሌ፣ በወሎ፣ በወልዲያ እና በሰሜኑ ክፍል አንድ ብሎ የጀመሩት የወንጌል እንቅስቃሴ ወደ ኤርትራ ተሻግሮ የእስራት ገፈትም ገና ቅምሻ የጀመረባቸው ከመጀመሪዎች አከባቢዎች የሚጠቀሱ ናቸው።
ጥቅምት 5 ቀን በ1957 ዓ.ም በመንፈስ ቅዱስ ተሞሉ። በኅዳር 5 ቀን የመጀመሪያውን የኢየሱስን ድንቅ ተአምራት በሕይወታቸው አዩ።
በሉተራን መጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ቤት ለአራት ዓመታት ቲዮሎጂን ተከታትለዋል። ቀጥሎም በናዝሬት (አዳማ) በሚገኘው በሜኖናይት መጽሐፍ ቅዱስ አካዳሚ ተከታታይ ሁለት ዓመታት የክረምት ትምህርት ተምረዋል።
ግማሽ ምዕተ-ዓመት የሚጠጋ ዓመታትን ቤተክርስቲያንን ከኢየሱስ እጅ በታች የበላይ ጠባቂ በመሆን መርተዋል። ከደርዘን (ከ12) በላይ የስነመለኮት መጽሐፍትን ለትውልድና ለቤተክርስቲያን አበርክተዋል። በርካቶች በእንግሊዝኛ፣ በአማርኛ፣ በኦሮሚኛና በትግሪኛ ትርጉም የእሳቸው ሥራዎች ለአንባቢያን በቅተዋል።
ከእነዚህም፦
መለኮታዊ ኃይል በ1961
እድን ዘንድ ምን ማድረግ ይገባኛል?
ጥያቄዎቻችሁና መልሶቻቸው
ትምህርተ-መለኮት
አዲስ ልደት
መጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ለጀማሪዎች
መጽሐፍ ቅዱስ ጸሐፊያን
ስነመለኮት (Bible writers theology)
ኢየሱስን ማን ይሉታል?
ቃሉ ይናገር
የመልዕክቶች አጠቃላይ ትምህርት
በእግዚአብሔር መጽሐፍ ፈልጉ
አንድ መንጋ
በስርዓት ታነጹ...ይጠቀሳሉ።
የአንድ አምላክ ትምህርትና የስሙ ጥምቀት በአጥንታችን ሰርጎ እስኪገባ፣ በደማችን እስክዋሄድ ዕድሜ ልካችን ሲናገሩ ኖረዋል። የሙዚቃ መሳሪያ ተጫዋች ናቸው፣ ዘማሪ ናቸው፣ የስነመለኮት አስተማሪና ተመራማሪ ናቸው፣ የተዋጣላቸው ሰባኪ፣ ጸሐፊም ነበሩ።

ቤተክርስቲያንን በዓለም አቀፉ ይዘት የመሩ መሪም ነበሩ፡፡ የእኚህ ሰው ሁለገብ አገልግሎታቸው እንዲሁ በሰው ጥበብ የተገኘ ተስጥኦ ነው ለማለት እንቸገራለን፤ ከሰማይ አምላክ የተሰጠ ጸጋ ነው እንጂ።

የጥንቱ መሰረት ዳግም በአንድ ሰው ልብ ተጸንሶ በመንፈስ ቅዱስ ምሪት በግለሰብ ቤት የተጀመረውን የሐዋርያትን ትምህርት ሰንሰለት ከ82 በላይ በዓለም አገራት እንዲስፋፋ የራሳቸውን ጥረት አድርገው ለእግዚአብሔር ፍቃድ ተገዢ ሆነዋል።
እኚህ ታላቅ ሰው በአሜርካን ሀገር በሚገኘው Christian life college የክብር ዶክትሬት ማዕረግ ተሸልመዋል። በ1993 ዓ.ም በካናዳ ሀገር ከሚገኘው ከጄነስስ ኢንስቲትዩት የስነመለኮት ትምህርት ተከታትለው ሦስተኛ ድግሪያቸውን "The mystery of God revealed እና mentally arrested by the myth of psychotherapy" በተባሉ ርዕሶች የምርምር ጽሑፋቸውን በማቅረብ በኢንስቲትዩቱ ከፍተኛ አድናቆትን አግኝተዋል።
በኢትዮጵያ ምድር የሐዋርያት ወንጌል እንዲስፋፋ ያደረጉት ትግል እንዲህ በጥቂት ገጾች ተጽፎ የሚበቃ አይደለምና ክብር ይገባቸዋል። ታሪካቸው ከቤተክርስቲያን ታሪክ ጋር በእሳቸው የተሰራው የኢየሱስ ሥራ ሲወሳ ይኖራል።
የእግዚአብሔር ቃል “የጥቂቱን ነገር ቀን የናቀ ማን ነው? ” (ዘካ 4፥10) እንደሚል ከእሳቸው ጋር መንፈሳቸውን ደግፈው ከተነሱ በጣት በሚቆጠሩ አባቶች የተጀመረው ይሄው እንቅስቃሴ ዛሬ ከ7 ሚሊዮን በላይ የአንድ አምላክ ልጆችን ከአለም ዙሪያ አስተሳስሯል ዛሬም ተቀጣጥሎ ቀጥሏል፡፡
ዶክተር ቢሾፕ ተክለማሪያም አንድ ወቅት ጣሊያን አገር ለህክምና በሄዱበት ሀከሙ
696 views19:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2019-09-17 05:29:26 #ለምስጋና_ተመለሱ
“ኢየሱስም መልሶ፦ አሥሩ አልነጹምን ? ዘጠኙስ ወዴት አሉ ? ከዚህ ከልዩ ወገን በቀር እግዚአብሔርን ሊያከብሩ የተመለሱ አልተገኙም አለ ። ” ሉቃ. 17፡17-18 ።የለምጽ በሽታ እንደ ዛሬው ያለ የቆዳ በሽታ አልነበረም ። የመጀመሪያ ተላላፊበሽታ ነው ። ሁለተኛ ከርኩሰት ጋር የተያያዘ ነው። ለምጽ ያለበት ሰው በካህኑ አዋጅ ራሱን ከሕዝቡ ለይቶ በምድረ በዳ ይኖራል ። ከተፈወሰ ሲመለስ ፣ ካልተፈወሰ በዚያው ይሞታል። የሚወዳቸው ቤተሰቦቹም ቤዛ ሊሆኑለት አይችሉም ። “ርኩስ ነኝ” ብሎ በራሱ ላይ ያውጃል ፣ ሰው ከቀረበውም እየሮጠ ይሸሻል ። ከባድ ጭንቅ ነው ። ጌታችን በሰማርያ ሲያልፍ አሥር ለምጻሞችን በምድረ በዳ አገኘ ። እነዚህ ለምጻሞች
ያገናኛቸው ኑሮ ሳይሆን ችግር ፣ ከተማ ሳይሆን ምድረ በዳ ነው ። ሐኪም ቤትና ስደት ያፋቅራል ።ችግሩ ያ ሲያልፍ መረሳሳት ይመጣ ይሆናል ። የችግር ቦታዎች ጥላቻና ራስ ወዳድነት የሚገረዝባቸው የግርዛት ኮረብታዎች ናቸው።ጌታችንን ባገኙት ጊዜ አልሮጡም ፣ እንደውም እየጮኹ ቀረቡት ። እርሱ የሚያነጻ ነውና ርኩሶችን አይሸሽም ። የሰው ቅድስና ግን ከራሱ አልተርፍ ስትል መሸሽ ይጀምራል ። “ኢየሱስ ሆይ አቤቱ ማረን አሉት ። ማረን ቢበድሉም ባይበድሉም ትልቅና የመጨረሻ ጸሎት ነው ። ቢታመሙም ባይታመሙም ሐኪም ጋ መሄድ መልካም ነው ። ስለ መፈወስ ቢለምኑ አንድ ልመና ነው ። እርሱ ከማራቸው ግን ሁሉም ጸጋ የእነርሱ ነው ። ማረኝ የጸሎት አባ ጠቅል ነው ። ምሕረት ያለውን ጌታ ማረኝ አሉት ። ማረኝ የሚባልም እርሱ ብቻ ነው ። ሰው ይቅር ይላል ፣መማር ግን የአንድ አምላክ ግብር ነው። ሰው ይተዉልናል ፣ እግዚአብሔር ግን እንዳልበደለ አድርጎ ይቀበለናል ። ጌታችን “ራሳችሁን ለካህን አሳዩ” አላቸው ። ለምጻም ናችሁ ብሎ ያረጋገጠውና በአዋጅ የለያቸው ካህኑ ነውና የሚመልሳቸውም ካህኑ ነው። ፈውሱን ጌታ አደረገና አዋጁን ግን ለባለሥልጣኑ ካህን ተወለት ። እግዚአብሔር ራሱ የሠራውን ሥርዓት ራሱ አያፈርስም ። “እነሆም ሲሄዱ ነጹ” ይላል ። በጣም ድንቅ ነገር ነው ። ከእነርሱም አንዱ እንደ ተፈወሰ ባየ ጊዜ ጌታችንን ሊያመሰግን ወደ ኋላ ተመለሰ ። ሌሎቹ ግን ቤተሰቦቻቸውንና የተለዩትን መንደር ለማግኘት ገሰገሱ ። አንገታቸው ወደፊት እንጂ ወደኋላ ዞር ብሎ የሚያይ አልነበረም ። ይህ አንዱ ሰው በጌታ እግር ላይ ወድቆ ማመስገን ጀመረ።ያ ሰው ግን የተናቀ ሳምራዊ ነበረ ። ከተናቀው ሰው የከበረ ምስጋናና ውለታ አክባሪነት ወጣ ። በማይጠበቅ ቦታ የማይጠበቅ ግብር ይገኛል። ዝናብ የሌላቸው ደመናዎች ብዙ አሉ ፣ ይህ ሰው ግን በቀትር የዘነበ ምስጋና አለው ። ድብልቅ ከሚባል ሕዝብ የጠራ ምስጋና ወጣ። ወገኑ ሳምራዊ ሳለ እንዴት አብሯቸው ከረመ ብንል የከፋ ችግር የሚያንሰውን ዘረኝነት አስረስቷቸው ነው ። በዘረኝነት የሰከሩ የባሰ ችግር ሲመጣ ይረሱታል ። “እዬዬ ሲዳላ ነው” ይባላል ። ሰው በጦርነት መሐል ልቅሶ አይቀመጥም ። ተደላድሎ ሲቀመጥ ግን ስለሞተው ወንድሙ ማልቀስ ይጀምራል ። ካልበሉ እንባም አይመጣም ። “ኢየሱስም መልሶ፦ አሥሩ አልነጹምን ? ዘጠኙስ ወዴት አሉ ? ከዚህ ከልዩ ወገን በቀር እግዚአብሔርን ሊያከብሩ የተመለሱ አልተገኙም አለ ።” ለምስጋና የሚመለስ ከአሥር አንድ መሆኑ ይገርማል ። ዘጠኙ ተፈውሰዋል
ውለታው የነካው ግን አንዱ ነው ። ዛሬም ከአሥሩ አንዱ ብቻ ለምስጋና ይመለሳል ። እነዚያ ዘጠኙ የገሰገሱት ግን ወደ ሚያልፉት ወዳጆቻቸው ነው። ደግሞም ርኩስ ብላ ወደ ገፋቻቸው ዓለም ነው ። ዛሬም ሰዎች ሲፈወሱ ወዳወገዘቻቸው ዓለም ይመለሳሉ ። ለምስጋና የሚመለሱ ጥቂቶች ናቸው ።የሚበዛው የምስጋና ዕዳ ያለበት ነው ። ወዳጆቼ ትልቁ በደል የእግዚአብሔርን ውለታ መርሳት ነው ። መቃብራችሁ የተደፈነላችሁ ፣ ከጫካ ሕይወት ወጥታችሁ ከሰው ቊጥር የተደመራችሁ ፣ የክረምትን ያህል በእንባ የታጠባችሁ ፣ ከሩቅ አገር ወደ ክርስቶስ የመጣችሁ ፣ … ለምስጋና ተመለሱ። ፈውስም ማግኘትም ዘላለማዊ አይደሉም ። ዘላለማዊ እግዚአብሔር ብቻ ነው ።
@onegodonlyjesus
Join & Share
14.2K viewsedited  02:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2019-09-16 03:53:59 አንድ አምላክ ብቻ!!!
8.0K views00:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2019-09-16 03:51:07
7.2K views00:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ