2022-07-30 13:12:46
ባሪያ በባይብል
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
90፥13 እርሱም ባሪያን መልቀቅ ነው፡፡ فَكُّ رَقَبَةٍ
በባይብል ዕብራዊ ባሪያ በገንዘብ ከተገዛ ስድስት ዓመት አገልግሎ በሰባተኛው ዓመት ነጻ ይወጣል፥ ዕብራዊ ባሪያ ብቻውን በገንዘብ ተሽጦ ከሆነ ብቻውን ነጻ ይወጣል፥ ከእነ ሚስቱ ተሽጦ ከሆነ ሚስቱም በሰባተኛው ዓመት ከእርሱ ጋር ነጻ ትወጣለች፦
ዘጸአት 21፥2 ዕብራዊ ባሪያ የገዛህ እንደሆነ ስድስት ዓመት ያገልግልህ፥ በሰባተኛውም በከንቱ አርነት ይውጣ።
ዘጸአት 21፥3 ብቻውን መጥቶ እንደሆነ ብቻውን ይውጣ፤ ከሚስቱ ጋር መጥቶ እንደሆነ ሚስቱ ከእርሱ ጋር ትውጣ።
ቅሉ ግን ባሪያው ብቻውን ከተሸጠ በኃላ ገዢው ጌታ ሚስት ከዳረው እና ልጆች ከወለደ እርሱ በሰባተኛው ዓመት ነጻ ሲወጣ ሚስቱ እና ልጆቹ ግን ለገዛው ጌታ ባሪያ ይሆናሉ፥ በሰባተኛው ዓመት ይህ በገንዘብ የተገዛው ባሪያ ሚስቱ እና ልጆቹን ጥሎ ላለመሄድ ከፈለገ በገንዘቡ የገዛው ጌታ ወደ ፈራጆቹ ወስዶ ጆሮውን በወስፌ በስቶ ለዘላለም ባሪያ ያረገዋል፦
ዘጸአት 21፥4 ጌታው ሚስት አጋብቶት እንደ ሆነ ወንዶች ወይም ሴቶች ልጆች ብትወልድለት፥ ሚስቱና ልጆችዋ ለጌታው ይሁኑ፥ እርሱም ብቻውን ይውጣ።
ዘጸአት 21፥5 ባሪያውም፦ "ጌታዬን ሚስቴን ልጅቼንም እወድዳለሁ፥ አርነት አልወጣም" ብሎ ቢናገር፥ ጌታው ወደ "አማልክቱ" הָ֣אֱלֹהִ֔ים ይውሰደው፥ ወደ ደጁም ወደ መቃኑ አቅርቦ ጆሮውን በወስፌ ይብሳው፤ ለዘላለምም ባሪያው ይሁን።
እዚህ አንቀጽ ላይ "ሃ- ኤሎሂም" הָ֣אֱלֹהִ֔ים የተባሉት ፈራጆች ሲሆኑ ሰውን በዚህ ደረጃ ማሰቃየት ተገቢ ነውን? ከዕብራዊ ውጪ ያለ ባሪያ ደግሞ ባርነቱ የጊዜ ገደብ የለውም፥ ምክንያቱም እንደ ቦታ ርስት ናቸውና፦
ዘሌዋውያን 25፥44 ወንድ ባሪያና ሴት ባሪያ መግዛት ብትፈልግ ግን በዙሪያችሁ ካሉት ከእነርሱ ከአሕዛብ ወንድና ሴት ባሪያዎችን ግዙ።
ዘሌዋውያን 25፥45 ደግሞም በእናንተ መካከል ከሚቀመጡት መጻተኞች፥ በምድራችሁም ውስጥ ከወለዱአቸው በእናንተ መካከል ከሚቀመጡት ከዘራቸው ውስጥ ባሪያዎችን ግዙ፤ ርስትም ይሁኑላችሁ።
ሰውን ባሪያ አርጎ እንደ ሸቀጥ መግዛት እና መሸጥ በባይብል መደበኛ ሕግ ነው፥ እንግዲህ ከበርቴ መሸጥ የሚቻለው የሌላ ሰው ልጅ ብቻ ሳይሆን የገዛ ሴት ልጅን ጭምር ነው፦
ዘጸአት 21፥7 ሰውም ሴት ልጁን ለባርነት ቢሸጥ ባሪያዎች እንደሚወጡ እርስዋ አትውጣ።
በባይብል ባሪያ እንደ ሰው አይታይም፥ ሰው ሰውን ቢገድል ይገደላል፥ ነገር ግን ሰው ባሪያውን ቢገድል ይቀጣል እንጂ አይገደልም፦
ዘጸአት 21፥12 ሰው ሰውን ቢመታ ቢሞትም፥ እርሱ ፈጽሞ ይገደል።
ዘጸአት 21፥20 ሰውም ወንድ ባሪያውን ወይም ሴት ባሪያውን በበትር ቢመታ፥ ቢሞትበትም፥ ፈጽሞ ይቀጣ። የተመታው ግን አንድ ወይም ሁለት ቀን ቢቈይ ገንዘቡ ነውና አይቀጣ።
ሰው ባሪያውን ደብድቦት ባይሞት ምንም አይቀጣም። ባሪያ መግረፍ መደበኛ ሕግ መሆኑን የምናየው በኢየሱስ ትምህርት ውስጥ በተሰጠው ምሳሌ ነው፦
ሉቃስ 12፥47 የጌታውንም ፈቃድ አውቆ ያልተዘጋጀ እንደ ፈቃዱም ያላደረገ ያ ባሪያ እጅግ ይገረፋል።
"ሎሌ" ማለት "ወንድ ባሪያ" ማለት ሲሆን "ገረድ" ደግሞ "ሴት ባሪያ" ማለት ነው፥ በአዲስ ኪዳን እንኳን ባርነት ሊቀር ይቅርና ባሮች ለጠማማ ጌቶቻቸው በፍርሃት እንዲገዙ ወፍራም ትእዛዝ አለ፦
1 ጴጥሮስ 2፥18 ሎሌዎች ሆይ! ለበጎዎችና ለገሮች ጌቶቻችሁ ብቻ ሳይሆን ለጠማሞች ደግሞ በፍርሃት ሁሉ ተገዙ።
ኤፌሶን 6፥5 ባሪያዎች ሆይ! ለክርስቶስ እንደምትታዘዙ በፍርሃት እና በመንቀጥቀጥ በልባችሁ ቅንነት በሥጋ ጌቶቻችሁ ለሆኑ ታዘዙ።
ባሮች ለጌቶቻቸው መታዘዝ ያለባቸው ልክ ለክርስቶስ በፍርሃት እና በመንቀጥቀጥ እንደሚታዘዙት መሆን እንዳለበት ጳውሎስ አስረግጦና ረግጦ ይናገራል። መገዛት ያለባቸው ለታይታ ሳይሆን ከልባቸው መሆን አለበት፥ ከቀንበር በታች ያሉቱ ባሪያዎች ሁሉ ለገዙአቸው ጌቶች መገዛታቸው እና መታዘዛቸው እንደ ክብር መቁጠር አለባቸው፦
ቆላስይስ 3፥22 ባሪያዎች ሆይ፥ በቅን ልብ ጌታን እየፈራችሁ እንጂ፥ ለሰው ደስ እንደምታሰኙ ለታይታ የምትገዙ ሳትሆኑ በሥጋ ጌቶቻችሁ ለሆኑ በሁሉ ታዘዙ።
ቲቶ 2፥9-10 ባሪያዎች ስለ መድኃኒታችን ስለ እግዚአብሔር የሚሆነውን ትምህርት በሁሉ ነገር ያስመሰግኑ ዘንድ ለገዛ ጌቶቻቸው እንዲገዙ፣ በሁሉም ደስ እንዲያሰኙ፣ ሳይቃወሙና ሳይሰርቁም በጎ ታማኝነትን ሁሉ እንዲያሳዩ ምከራቸው።
1 ጢሞቴዎስ 6፥1 የእግዚአብሔር ስምና ትምህርቱ አንዳይሰደብ ከቀንበር በታች ያሉቱ ባሪያዎች ሁሉ ለገዙአቸው ጌቶች ክብር ሁሉ እንደ ተገባቸው ይቍጠሩአቸው።
ጥቁር ሰው በተለምዶ "ባሪያ" "ባሪዬ" "ባርች" የሚል ስያሜ የመጣው ምዕራባውያን አፍሪካውያንን በባርነት ከገዙበት ወዲህ ነው፥ ምዕራባውያ ክርስቲያኖች የባሪያ ንግድ ያጧጧፉት ብሉይ እና አዲስ ኪዳን ላይ ያሉትን አናቅጽ መሠረት አድርገው ነው። ስሌቭ"slave" የሚለው የእንግሊዙ ቃል እራሱ የመጣው ጀርመን ክርስቲያኖች ስላቭ"slavonic" ሕዝቦችን ወደ አሜሪካ አህጉር በባርነት መግዛት ከጀመሩበት ወዲህ ነው፥ ደቡብ አሜሪካን ያሉትን 642 ሚልዮን ሕዝቦች የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን በባርነት እና በጉልበት በመግዛት ላቲን አሜሪካ ያደረገችበት እና ዛሬ ከላቲን አሜሪካ ሕዝብ 69% ካቶሊክ የሆነው በባርነት ነው። በኢሥላም ባሪያን ከባርነት ማላቀቅ የከፍታ ማማ ነው፦
90፥11 ዓቀበቲቱንም አልወጣም። فَلَا اقْتَحَمَ الْعَقَبَةَ
90፥12 ዓቀበቲቱም መውጣቷ ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ? وَمَا أَدْرَاكَ مَا الْعَقَبَةُ
90፥13 እርሱም ባሪያን መልቀቅ ነው፡፡ فَكُّ رَقَبَةٍ
ክርስቲያኖች ሆይ! የቱን ትመርጣላችሁ? በሕጉ ውስጥ ባሪያን ነጻ ለማውጣት የሚያስተምረውን እሥልምናን ወይስ ባርነትን የሚያጠናክር እና የሚያበረታታ ክርስትና? አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።
ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
@islam_ustaz_abuhayder
ወሠላሙ ዐለይኩም
235 viewsedited 10:12