Get Mystery Box with random crypto!

የሀይማኖት ንፅፅር ☪️vs✝️

የቴሌግራም ቻናል አርማ islam_ustaz_abuhayder — የሀይማኖት ንፅፅር ☪️vs✝️
የቴሌግራም ቻናል አርማ islam_ustaz_abuhayder — የሀይማኖት ንፅፅር ☪️vs✝️
የሰርጥ አድራሻ: @islam_ustaz_abuhayder
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.34K
የሰርጥ መግለጫ

📖የሀይማኖት ንፅፅር☪️
ይህ ግሩፕ
👉 እዉነትን የምናቅበት ወደተፈጠርንበት እምነት የምንመለስበት በቂ እዉቀት የምናገኝበ ነዉ:: @islam_ustaz_abuhayder
🤥ሼር ያድርጉን::

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-07-30 13:12:47 የሣሚሪይ ጥጃ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

7፥148 የሙሣም ሕዝቦች ከእርሱ መኼድ በኋላ ከጌጦቻቸው ወይፈንን አካልን ለእርሱ "ማግሳት" ያለውን አምላክ አድርገው ያዙ፡፡ وَاتَّخَذَ قَوْمُ مُوسَىٰ مِن بَعْدِهِ مِنْ حُلِيِّهِمْ عِجْلًا جَسَدًا لَّهُ خُوَارٌ

ሙሣ ለአርባ ቀን ወደ ተራራ ከሄደ በኃላ የሙሣም ሕዝቦች ከጌጦቻቸው ወይፈንን አካልን ለእርሱ ማግሳት ያለውን አምላክ አድርገው ያዙ፦
7፥148 የሙሣም ሕዝቦች ከእርሱ መኼድ በኋላ ከጌጦቻቸው ወይፈንን አካልን ለእርሱ "ማግሳት" ያለውን አምላክ አድርገው ያዙ፡፡ وَاتَّخَذَ قَوْمُ مُوسَىٰ مِن بَعْدِهِ مِنْ حُلِيِّهِمْ عِجْلًا جَسَدًا لَّهُ خُوَارٌ

"ዒጅል" عِجْل ማለት "ጥጃ" ማለት ሲሆን ይህም ጥጃ "ወይፈን" ነው፥ "ወይፈን" ማለት "ወጣት ጥጃ" ማለት ነው፥ "ጀሠዳ" جَسَدًا ማለት "አካል" ማለት ሲሆን እዚህ ዐውድ ላይ "ምስል" ወይም "ቅርጽ" የሚል ፍቺን ለማመልከት የገባ ነው። የሙሣም ሕዝቦች በምድረበዳ አምላክ አርገው የያዙት ይህ የጥጃ ቅርጽ ማናገር እና መምራት የማይችል ጣዖት ነበረ፦
7፥148 እርሱ የማያናግራቸው እና መንገድንም የማይመራቸው መኾኑን አይመለከቱምን? አምላክ አድርገው ያዙት፡፡ በዳዮችም ኾኑ፡፡ أَلَمْ يَرَوْا أَنَّهُ لَا يُكَلِّمُهُمْ وَلَا يَهْدِيهِمْ سَبِيلًا ۘ اتَّخَذُوهُ وَكَانُوا ظَالِمِينَ

ሣሚሪይ የሙሣም ሕዝቦች ካመጡለት ጌጣጌጥ ቅርጽ በመቅረጽ እና የጂብሪል ፈረስ ከረገጠው ዱካ ማለትም ኮቴ ላይ አፈር ዘግኖ በቅርጹ ላይ በማድረግ ማግሳት ያለው ጣዖት ሠርቷል፦
20፥96 «ያላዩትን ነገር አየሁ፥ ከመልእክተኛው ዱካም ጭብጥ አፈርን ዘገንኩ፡፡ በቅርጹ ላይ ጣልኳትም፡፡ እንደዚሁም ነፍሴ ሸለመችልኝ» አለ፡፡ قَالَ بَصُرْتُ بِمَا لَمْ يَبْصُرُوا بِهِ فَقَبَضْتُ قَبْضَةً مِّنْ أَثَرِ الرَّسُولِ فَنَبَذْتُهَا وَكَذَٰلِكَ سَوَّلَتْ لِي نَفْسِي

እዚህ አንቀጽ ላይ "መልእክተኛ" የተባለው ጂብሪል ሲሆን ሣሚሪይ የጂብሪል ፈረስ ዱካ የረገጠበትን አፈር ጥጃው ውስጥ ሲበትነው ጥጃው መጓጎር ያለው ሆነ፥ የሙሣም ሕዝቦች፦ "ይህ አምላካችሁ የሙሣም አምላክ ነው ግን ረሳው" አሉ፦
20፥88 ለእነርሱም አካል የኾነ ጥጃን ለእርሱ መጓጎር ያለውን አወጣላቸው፡፡ ተከታዮቹ «ይህ አምላካችሁ የሙሣም አምላክ ነው ግን ረሳው» አሉም፡፡ فَأَخْرَجَ لَهُمْ عِجْلًا جَسَدًا لَّهُ خُوَارٌ فَقَالُوا هَـٰذَا إِلَـٰهُكُمْ وَإِلَـٰهُ مُوسَىٰ فَنَسِيَ

"ኹዋር" خُوَار የሚለው ቃል "ኻረ" خَارَ‎ ማለትም "አገሳ" "ጓገረ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ማግሳት" "መጓጎር" ማለት ነው፥ ያ የጥጃ ቅርጽ ልክ እንደ ጥጃ ድምፅ ነበረው። ሚሽነሪዎች፦ "ድምፅ ካለው ሕይወት አለው፥ ሕይወት ካለው ደግሞ ሣሚሪይ ለቅርጹ ሕይወት እንዴት ሰጠው? ሕይወት መስጠት የፈጣሪ ችሎት ብቻ ነው" ብለው ይጠይቃሉ።
፨ሲጀመር አንድ ግዑዝ ነገር ድምፅ ስላለው ሕይወት አለው ብሎ መደምደም ቂልነት ነው፥ ምክንያቱም ዕሩቅ ሳንሄድ ሠው ሠራሽ"artificial" የሆኑት ሮቦት ልክ እንደ ሰው ድምፅ ከማውጣት አልፈው የማሰብ ክህሎት"intelligence" ኖሯቸው ሒሣብ ያሥባሉ፣ ስም እና ቁጥር ይመዘግባሉ፣ መረጃ እና ማስረጃ ያቀብላሉ። ቅሉ ግን ሕይወት የላቸው፥ በተመሳሳይ የሳምራዊው ጥጃ ልክ እንደ ጥጃ ድምፅ ስለነበረው ሕይወት አለው ማለት አይደለም።

፨ሲቀጥል "ሕይወት የነበረው ጥጃ ነበረ" ቢባል እንኳን ፈጣሪ ሕይወት ከሚሰጥበት ችሎት ጋር የሚመዛዘን፣ የሚነጻር እና የሚለካ አይደለም፥ ምክንያቱም የሙሣ በትር እባብ ሲሆን በተመሳሳይ የፊርዐውን ደጋሚዎች ገመዶቻቸው እና ዘንጎቻቸው እባቦች አድርገዋል። የሙሣም እባብ የደጋሚዎችን እባቦች ውጣቸዋለች፦
20፥66 «አይደለም ጣሉ» አላቸው፡፡ ወዲያውም ገመዶቻቸው እና ዘንጎቻቸው ከድግምታቸው የተነሳ እነርሱ የሚሮጡ እባቦች ኾነው ወደ እርሱ ተመለሱ፡፡ قَالَ بَلْ أَلْقُوا ۖ فَإِذَا حِبَالُهُمْ وَعِصِيُّهُمْ يُخَيَّلُ إِلَيْهِ مِن سِحْرِهِمْ أَنَّهَا تَسْعَىٰ
20፥69 «በቀኝ እጅህ ያለቸውንም በትር ጣል! ያንን የሠሩትን ትውጣለችና፥ ያ የሠሩት ሁሉ የድግምተኛ ተንኮል ነውና፡፡ ድግምተኛም በመጣበት ስፍራ ሁሉ አይቀናውም» አልን፡፡ وَأَلْقِ مَا فِي يَمِينِكَ تَلْقَفْ مَا صَنَعُوا ۖ إِنَّمَا صَنَعُوا كَيْدُ سَاحِرٍ ۖ وَلَا يُفْلِحُ السَّاحِرُ حَيْثُ أَتَىٰ

እኛም በተራችን ጥያቄ እንጠይቃለን። ሕይወት መስጠት የፈጣሪ ብቻ ችሎት ከሆነ ደጋሚዎቹ እንዴት እባቦች ሠሩ? ይህ ጉዳይ እኮ በባብይልም አለ፦
ዘጸአት 7፥10-12 ሙሴ እና አሮንም ወደ ፈርዖን ገቡ፥ ያህዌህም እንዳዘዛቸው እንዲሁ አደረጉ፤ አሮንም በትሩን በፈርዖን እና በባሮቹ ፊት ጣለ፥ እባብም ሆነች። ፈርዖንም ጠቢባንንና መተተኞችን ጠራ፤ የግብፅም ጠንቋዮች በአስማታቸው እንዲሁ ደግሞ አደረጉ። እያንዳንዳቸውም በትራቸውን ጣሉ፥ እባቦችም ሆኑ፤ የአሮን በትር ግን በትራቸውን ዋጠች።

በሰፈሩት ቁና መሰፈር ይሉካል እንደዚህ ነው፥ ሕይወት መስጠት የፈጣሪ ብቻ ችሎት ከሆነ የግብፅም ጠንቋዮች እንዴት በትራቸውን እባቦች አደረጉ? በመተትስ ቢሆን ሕይወት ያለው እንስሳ ማድረግ ይቻላልን? ይህንን መልስ ስትሰጡ የሣሚሪይ ጥጃ ድምፅ ያለው ቅርጽ መሆኑ አይደንቃችሁም። አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
@islam_ustaz_abuhayder

ወሠላሙ ዐለይኩም
734 viewsedited  10:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-30 13:12:47 ነቢያችን”ﷺ” የነቢያት መደምደሚያ ናቸው፤ ወሕይ መውረድ እሳቸው ጋር ቆሟል፤ ከእርሳቸው በኃላ ሪሳላ መውረድ አሊያም ነበእ መውረድ ቆሟል፦
33፥40 ሙሐመድ ከወንዶቻችሁ የአንድንም ሰው አባት አይደለም፤ ነገር ግን የአላህ መልክተኛ እና *”የነቢያት መደምደሚያ”* ነው፤ አላህም በነገሩ ሁሉ ዐዋቂ ነው። مَا كَانَ مُحَمَّدٌ أَبَا أَحَدٍ مِنْ رِجَالِكُمْ وَلَٰكِنْ رَسُولَ اللَّهِ وَخَاتَمَ النَّبِيِّينَ وَكَانَ اللَّهُ بِكُلِّ شَيْءٍ عَلِيمًا
ጃምዒ አት-ተርሚዚ መጽሐፍ 8, ሐዲስ 2272
አነስ ኢብኑ ማሊክ እንደተረከው የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ *”በእርግጥም መልእክተኛነት እና ነብይነት ተዘግቷል። ከእኔ በኃላ መልእክተኛም ነብይም የለም*። حَدَّثَنَا أَنَسُ بْنُ مَالِكٍ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ” إِنَّ الرِّسَالَةَ وَالنُّبُوَّةَ قَدِ انْقَطَعَتْ فَلاَ رَسُولَ بَعْدِي وَلاَ نَبِيَّ

ምን ትፈልጋለህ? ነቢያችን"ﷺ" ከእርሳቸው በኃላ የፈጣሪ ነቢይ ፈጽሞና ጨልጦ እንደማይመጣ ፍርጥ አርገው እንቅጩን ነግረውናል። እዚሁ ሐዲስ ላይ "ነቢይነት"Prophethood" ተብሎ የተቀመጠው ቃል "ኑቡወት" نُّبُوَّة ሲሆን “ነበእ” نَبَإِ ለሚለው ቃል ተለዋዋጭ ቃል ነው፤ ነቢይነት ከተዘጋ ትንቢትም ተዘግቷል። ከእርሳቸው በኃላ የሚመጣ ነቢይ እና መልክተኛ ከሌለ ከቁርኣን በኃላ የምሰማው ከፈጣሪ የመጣ መልእክት እና ትንቢት የለም። አለ የተባለው ሁሉ የሐሳዌ መልእክት እና ትንቢት ነው። “አድ-ደጃል” الدجّال‌‎ የሚለው ቃል “ደጀለ” دَجَلَ ማለትም “ቀላቀለ” ከሚል ግስ የመጣ ሲሆን “ቀላቃይ” ማለት ነው፤ እውነትን ከሐሰት ጋር የሚቀላቅል ማለት ነው፤ ይህ ቋንቋዊ ፍቺው ሲሆን ሃይማኖታዊ ፍቺው ደግሞ “ኀሳዌ” ማለትም “አሳሳች” “ውሸተኛ” “ቀጣፊ” ማለት ነው። ዋናው ደጃል “መሢሑል ደጃል” ማለትም “ኀሳዌ መሢሕ” ሲሆን እርሱ ከመምጣቱ በፊት የሚመጡ ሠላሳ ደጃሎች አሉ፤ “ደጅጃሉን” دَجَّالُونَ የሚለው ቃል “ደጃል” دجّال‌‎ ለሚለው ነጠላ ቃል ብዜት ነው፤ እነዚህ ወደ ሠላሳ የሚቃረቡ ደጃሎች “እኔ የአላህ መልእክተኛ ነኝ” ወይም “እኔ የአላህ ነብይ ነኝ” ብለው ይነሳሉ፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 54, ሐዲስ 108
አቢ ሁረይራህ”ረ.ዐ.” እንደተረከው ነብዩም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ *“የመጨረሻይቱ ሰአት አትቆምም ሠላሳ የሚቃረቡ ደጃሎች ቀጣፊዎች ተነስተውስ፦ “እኔ የአላህ መልእክተኛ ነኝ” ብለው ቢናገሩ ቢሆን እንጂ”*። عَنْ أَبِي، هُرَيْرَةَ عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ” لاَ تَقُومُ السَّاعَةُ حَتَّى يُبْعَثَ دَجَّالُونَ كَذَّابُونَ قَرِيبٌ مِنْ ثَلاَثِينَ كُلُّهُمْ يَزْعُمُ أَنَّهُ رَسُولُ اللَّهِ
ሱነን አቢ ዳውድ :መጽሐፍ 37, ሐዲስ 13
የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ *ከእኔ ኡማህ ውስጥ ሠላሳ የሚያህሉ ቀጣፊዎች፦ “ነብይ ነኝ” ብለው ይነሳሉ፤ ነገር ግን እኔ የነብያት መደምደሚያ ነኝ፤ ከእኔ በኃላ ነብይ የለም”*። وَحَتَّى تَعْبُدَ قَبَائِلُ مِنْ أُمَّتِي الأَوْثَانَ وَإِنَّهُ سَيَكُونُ فِي أُمَّتِي كَذَّابُونَ ثَلاَثُونَ كُلُّهُمْ يَزْعُمُ أَنَّهُ نَبِيٌّ وَأَنَا خَاتَمُ النَّبِيِّينَ لاَ نَبِيَّ بَعْدِي

በነቢያችን"ﷺ" ኡማህ ውስጥ የሚነሱት እነዚህ ሐሰተኛ ነቢያት ሲሆኑ በክርስትናው ደግሞ የተነሱት እልፍ አእላፍ ናቸው። "ነቢይ ነኝ" ብለው የተነሱት ባሃኦላህ፣ ረሺድ ኸሊፋህ፣ ጉላም አሕመድ ወዘተ መነሻቸው "ለወልይ የሚሰጥ ከራመት አለኝ" በሚል ሽፋን ነው፤ "ዶሮን ሲያታልሏት፥ ሙቁ ውኃው ለገላሽ ነው አሏት" ይባል የለ? የወደፊቱን ክስተት፣ ክንውን፣ እና ድርጊት ዕናውቃለን የሚሉት ጋር ሄዶ ማመን ትልቁ ሺርክ ነው፥ ከኢሥላም አጥር ያስወጣል፤ ድርጊቱ ኩፍር ነው፦
ሱነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 1, ሐዲስ 682
አቢ ሁረይራህ”ረ.ዐ” እንዳለው፦ “የአላህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ ሲሉ ሰምቻለው፦ ማንም በሓይድ ላይ ካለች ሴት ወይም በመቀመጫዋ በኩል ተራክቦ ቢያደርግ *"አሊያም ወደ ተንባይ ቢሄድና የተነገረውን ቢያምን በሙሐመድ”ﷺ” ላይ በተወረደው ክዷል"*። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ ‏ "‏ مَنْ أَتَى حَائِضًا أَوِ امْرَأَةً فِي دُبُرِهَا أَوْ كَاهِنًا فَصَدَّقَهُ بِمَا يَقُولُ فَقَدْ كَفَرَ بِمَا أُنْزِلَ عَلَى مُحَمَّد

"ካሂን" كَاهِن የሚለው ቃል "ከሀነ" كَهَنَ‎ ማለትም "ተነበየ" ከሚል ሥርወ-ቃል የተገኘ ሲሆን "የሩቅ ነገር ተንባይ" ማለት ነው፤ እነዚህ የሩቅ ነገርን ዕናውቃለን የሚሉ ጠንቋዮችንም ያመለክታል። ስለዚህ ትንቢት ተነበዩ የተባሉት በዓለማችን ውስጥ ኖስትራዳመስ"Nostradamus" እንዲሁ በአገራችን እዩ ጩፋ፣ እኅተ ማርያም ሆነ ሼህ ሑሤን ጅብሪል ከአላህ ያልሆነ የሐሳዌ ጽርፈት መሆኑን ከወዲሁ መጠንቀቅ ነው። በተለይ ክርስቲያኖች የሼይኽ ሑሤን ጅብሪል ትንቢት እያሉ የሚያናፍሱት፣ የሚደርሱትና የሚጽፉት እሥልምና ትክክል መሆኑን ለማሳወቅ ሳይሆን ቅቤ አንጓችና አስብቶ አራጅ ስለሆኑ ነው። "አሞኛችሁ ዘንድ ዐይናችሁን ጨፍኑ፥ ጆሮአችሁን ድፈኑ" ብንባል ፍንክች የአባ ቢላዋ ልጅ ብለናል። አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
@islam_ustaz_abuhayder

ወሠላሙ ዐለይኩም
512 viewsedited  10:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-30 13:12:47 የሼይኽ ሑሤን ጅብሪል ትንቢት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

33፥40 ሙሐመድ ከወንዶቻችሁ የአንድንም ሰው አባት አይደለም፤ ነገር ግን የአላህ መልክተኛ እና *”የነቢያት መደምደሚያ”* ነው፤ አላህም በነገሩ ሁሉ ዐዋቂ ነው። مَا كَانَ مُحَمَّدٌ أَبَا أَحَدٍ مِنْ رِجَالِكُمْ وَلَٰكِنْ رَسُولَ اللَّهِ وَخَاتَمَ النَّبِيِّينَ وَكَانَ اللَّهُ بِكُلِّ شَيْءٍ عَلِيمًا

ቁርኣን አንድ ሦስተኛው “ገይብ” غَيْب ማለትም “የሩቅ ወሬ” ነው፤ “ገይብ” በጥቅሉ በሶስት ይከፈላል፦
፦አንደኛው “አል-ገይቡል ማዲ” الغيبه الماضي ሲሆን ያለፈ ክስተት ነው፤ ይህም ድርጊቱ ከዚህ በፊት አላፊ የሆነ ነገር ነው።
፦ሁለተኛው “አል-ገይቡል ሙዷሪዕ” الغيب المضارع ሲሆን እየተፈጸመ ያለ ክስተት ነው፤ ይህም ድርጊቱ በአሁኑ ሰዓት ቀጣይነት ያለው ከህዋስ ባሻገር ያለ ነገር ነው።
፦ሦስተኛው እና የመጨረሻው “አል-ገይቡል ሙሥተቅበል” الغيب المستقبل ሲሆን መጪው ክስተት ነው፤ ይህም ድርጊቱ ገና ያልተፈጸመ ወደፊት የሚሆን ነው። አላህ ከፍጡራን በኃላ ወደ ፊት ምን እንሚከሰት ያውቃል፥ ይህ ለምሳሌ ከአሁን እስከ ትንሳኤ ቀን ክስተቶችን ምን እንሚመከሰቱ ከአላህ በቀር ማንም አያውቅም፦
28፥65 *«በሰማያትና በምድር ያለው ሁሉ ”ሩቅን ምስጢር” አያውቅም፤ ግን አላህ ያውቀዋል*፡፡ መቼ እንደሚቀሰቀሱም አያውቁም» በላቸው፡፡ قُل لَّا يَعْلَمُ مَن فِى ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلْأَرْضِ ٱلْغَيْبَ إِلَّا ٱللَّهُ ۚ وَمَا يَشْعُرُونَ أَيَّانَ يُبْعَثُونَ
6፥59 *”የሩቅ ነገርም” መክፈቻዎች እርሱ ዘንድ ናቸው፡፡ ከእርሱ በቀር ማንም አያውቃቸውም*፡፡ وَعِندَهُۥ مَفَاتِحُ ٱلْغَيْبِ لَا يَعْلَمُهَآ إِلَّا هُوَ ۚ

“ገይብ” በተናጥል ሁለት ደረጃ አለው አንዱ አላህ ብቻ የሚያውቀው ሲሆን “አል-ገይቡል ሙጥለቅ” الغيب المطلق ሲባል፣ ሁለተኛው ደግሞ አላህ ለሚልከው ነቢይ ሲያሳውቅ ያ የሚያሳውቀው የሩቅ ነገር ምስጢር “አል-ገይቡ አን-ኒስቢይ” الغيب النسبي ይባላል፤ አላህ ወደፊት የሚከሰተውን ክስተት አስቀድሞ ለሚወደው ነቢይ ይገልጥለታል፦
72፥26 *«እርሱ ”ሩቁን ምስጢር” ዐዋቂ ነው፡፡ በምስጢሩም ላይ አንድንም አያሳውቅም፡፡»* عَٰلِمُ ٱلْغَيْبِ فَلَا يُظْهِرُ عَلَىٰ غَيْبِهِۦٓ أَحَدًا
72፥27 *ከመልክተኛ ለወደደው ቢኾን እንጅ ለሌላ አይገልጽም*፡፡ إِلَّا مَنِ ٱرْتَضَىٰ مِن رَّسُولٍۢ

አላህ ስለ ራሱ በሦስተኛ መደብ “ኢዝ ቃለ” إِذْ قَالَ ማለትም “ባለ ጊዜ አስታውስ” ወይም በመጀመሪያ መደብ “ኢዝ ቁልና” إِذْ قُلْنَا ማለትም “ባልን ጊዜ አስታውስ” በማለት ከነቢያችን”ﷺ” በኃላ ወደፊቱ የሚከሰተውን ምን እንደሚል ይናገራል፤ ፍጡራንም ምን እንደሚሉ ሲናገር “ኢዝ ቃሉ” إِذْ قَالُوا ማለትም “ባሉ ጊዜ አስታውስ” በማለት ይናገራል። ይህንን የሩቅ ወሬ አምላካችን አላህ ለነቢያችን”ﷺ” “ኑሒሂ ኢለይከ” نُوحِيهِ إِلَيْكَ ማለትም “ወደ አንተ እናወርዳለን” ወይም “ነቁስሱ ዐለይከ” نَقُصُّ عَلَيْكَ ማለትም “እንተርክልሃለን” በማለት ይናገራል። ይህንን የሩቅ ወሬ “ፈዘከር” فَذَكِّرْ ማለትም “አስታውስ” ይላቸዋል። ነቢያችን”ﷺ” ደግሞ “ሙዘከር” مُذَكِّرٌ ማለትም “አስታዋሽ” ናቸው፦
88፥21 *አስታውስም፤ አንተ አስታዋሽ ብቻ ነህና*፡፡ فَذَكِّرْ إِنَّمَا أَنتَ مُذَكِّرٌ

ነቢያችን”ﷺ” የሚያሳታውሱት ከራሳቸው አመንጭተው ሳይሆን በተወረዳቸው “ዚክር” ذِكْر ማለትም “ማስታወሻ” ብቻ ነው፤ ይህም ዚክር ቁርኣን ነው፦
21፥50 *ይህም ያወረድነው የኾነ ብሩክ “ዚክር” ነው*፡፡ ታዲያ እናንተ ለእርሱ ከሓዲዎች ናችሁን? وَهَـٰذَا ذِكْرٌ مُّبَارَكٌ أَنزَلْنَاهُ ۚ أَفَأَنتُمْ لَهُ مُنكِرُونَ
21፥45 *”የማስጠነቅቃችሁ በተወረደልኝ ብቻ ነው”*፡፡ ግን ደንቆሮዎች በሚስጠነቀቁ ጊዜ ጥሪን አይሰሙም» *በላቸው*፡፡ قُلْ إِنَّمَا أُنذِرُكُم بِالْوَحْيِ ۚ وَلَا يَسْمَعُ الصُّمُّ الدُّعَاءَ إِذَا مَا يُنذَرُونَ
50፥45 እኛ የሚሉትን ሁሉ ዐዋቂ ነን፤ አንተም በእነርሱ ላይ አስገዳጅ አይደለህም፡፡ ስለዚህ ዛቻዬን የሚፈራን ሰው *በቁርኣን አስታውስ*፡፡ نَّحْنُ أَعْلَمُ بِمَا يَقُولُونَ ۖ وَمَا أَنتَ عَلَيْهِم بِجَبَّارٍ ۖ فَذَكِّرْ بِالْقُرْآنِ مَن يَخَافُ وَعِيدِ

“አል-ገይቡል ሙሥተቅበል” የመጪው ጊዜ "ትንቢት" ነው፤ "ትንቢት" ተብሎ የተቀመጠው ቃል “ነበእ” نَبَإِ ነው። “ነቢይ” نبي የሚለው ቃል “ነበአ” نَبَّأَ ከሚለው የግስ መደብ እና “ነበእ” نَبَإِ ከሚለው የስም መደብ የመጣ ሲሆን “የሩቅ ወሬ አውሪ” ማለት ነው፤ ነቢያችን"ﷺ" "ነቢይ" ሲሆኑ አላህ ያወረደላቸው ቁርኣን ደግሞ "ነበእ" ነው፦
78፥1-4 ከምን ነገር ይጠያየቃሉ? *ከታላቁ ትንቢት*፤ ከዚያ እነርሱ በእርሱ የተለያዩበት ከኾነው፡፡ ይከልከሉ፤ *ወደፊት በእርግጥ ያውቃሉ*፡፡ عَمَّ يَتَسَآءَلُونَ عَنِ ٱلنَّبَإِ ٱلْعَظِيمِ ٱلَّذِى هُمْ فِيهِ مُخْتَلِفُونَ كَلَّا سَيَعْلَمُونَ
38፥67 በላቸው *«እርሱ ቁርኣን ታላቅ ትንቢት ነው*፡፡ قُلْ هُوَ نَبَأٌ عَظِيمٌ

ቁርኣን ታላቁ ትንቢት ነው፤ ይህንን ትንቢት አምላካችን አላህ፦ "ትንቢቱን በእርግጥ ከጊዜ በኋላ ወደፊትም ታውቁታላችሁ" ይለናል፦
38፥88 *«ትንቢቱንም ከጊዜ በኋላ በእርግጥ ታውቁታላችሁ፡፡* وَلَتَعْلَمُنَّ نَبَأَهُ بَعْدَ حِينٍ
6፥67 *ለትንቢት ሁሉ የሚደርስበት መርጊያ አለው፡፡ ወደፊትም ታውቁታላችሁ*፡፡ لِّكُلِّ نَبَإٍ مُّسْتَقَرٌّ ۚ وَسَوْفَ تَعْلَمُونَ

አምላካችን አላህ ይህንን ትንቢት ነቢያችን"ﷺ" እንዲያስጠነቅቁ "አንተ ነቢዩ ሆይ" በማለት እያናገራቸው ልኳቸዋል፦
33፥45 *አንተ ነቢዩ ሆይ! እኛ መስካሪ፣ አብሳሪና አስጠንቃቂም አድርገን ላክንህ*፡፡ يَا أَيُّهَا النَّبِيُّ إِنَّا أَرْسَلْنَاكَ شَاهِدًا وَمُبَشِّرًا وَنَذِيرًا
418 views10:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-30 13:12:47 ቁርአን የጥበቦች ሁሉ መፍለቂያ ድንቅ እና ታላቅ መለኮታዊ መጽሐፍ ሲሆን ዘላለማዊ ተአምር የሆነ ሙሉ የህይወት መመሪያ ነው።
@islam_ustaz_abuhayder
347 viewsedited  10:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-30 13:12:47 ፀሐይ እና ጨረቃ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

10፥5 እርሱ ያ ፀሐይን "አንጻባራቂ" ጨረቃንም "አብሪ" ያደረገ ነው፡፡ هُوَ الَّذِي جَعَلَ الشَّمْسَ

"ሢራጅ" سِرَاج ማለት በዓይን ለማየት አስቸጋሪ ከመሆኑ የተነሳ "አንጸባራቂ" ማለት ሲሆን "ሙኒር" مُّنِير ማለት ደግሞ "አብሪ" ማለት ነው፥ አምላካችን አሏህ በቅርቢቱ ሰማይ ላይ "ሢራጅ" سِرَاج የተባለችው ፀሐይ እና "ሙኒር" مُّنِير የተባለው ጨረቃ አድርጓል፦
10፥5 እርሱ ያ ፀሐይን ሲራጅ ጨረቃንም ሙኒር ያደረገ ነው፡፡ هُوَ الَّذِي جَعَلَ الشَّمْسَ ضِيَاءً وَالْقَمَرَ نُورًا

አምላካችን አሏህ በቅርቢቱ ሰማይ ላይ ከዋክብትን ያረጋቸው በረጨት ነው፥ “ረጨት” ማለት የከዋክብት ስብስብ”galaxy” ማለት ሲሆን የእኛ ረጨት “ፍኖተ-ሃሊብ”Milky Way” ይባላል። ይህ ረጨት ውፍረቱ 1000 የብርሃን ዓመት እንደሆነ ይገመታል፥ ከአንዱ ጫፍ እስከሌላኛው ጫፍ ያለው ርቀት በዲያሜትር ሲለካ እንኳን እራሱ 100,000 የብርሃን ዓመት ይሆናል። የሚያጅበው በውስጡ ከ100 እስከ 400 ቢልዮን ከዋክብቶች እንደያዘ ይገመታል፥ ይህ አንዱ ኅብረ-ከዋክብት ወይም ማዛሮት”constellation” ደግሞ “ቡርጅ” بُرْج ይባላል። በቅርቢቱ ሰማይ ብዙ ረጨቶች ስላሉ አምላካችን አሏህ “ቡሩጅ” بُرُوج በማለት ነግሮናል፦
37፥6 እኛ ቅርቢቱን ሰማይ በከዋክብት ጌጥ አጌጥናት፡፡ إِنَّا زَيَّنَّا السَّمَاءَ الدُّنْيَا بِزِينَةٍ الْكَوَاكِبِ
25፥61 “ያ በሰማይ ቡሩጆችን ያደረገ እና በእርሷም ፀሐይን ሲራጅ እና ጨረቃን ሙኒር ያደረገ ጌታ ክብሩ በጣም ላቀ”፡፡ تَبَارَكَ الَّذِي جَعَلَ فِي السَّمَاءِ بُرُوجًا وَجَعَلَ فِيهَا سِرَاجًا وَقَمَرًا مُّنِيرًا

"ፊ-ሃ" فِيهَا ማለት "በ-ውስጧ" ማለት ሲሆን "ሃ" هَا የሚለው ተሳቢ ተውላጠ ስም "ሠማኡ አድ-ዱንያ" سَّمَاء الدُّنْيَا ማለትም "ቅርቢቱን ሰማይ" የሚለውን ቃል ተክቶ የመጣ ነው። አሏህ በሌላ አንቀጽ ፀሐይን "ዲያእ" ضِيَاء ጨረቃን ደግሞ "ኑር" نُور ይለዋል፦
71፥16 በውስጣቸውም ጨረቃን ኑር አደረገ፥ ፀሐይንም ሲራጅ አደረገ፡፡ وَجَعَلَ الْقَمَرَ فِيهِنَّ نُورًا وَجَعَلَ الشَّمْسَ سِرَاجًا

"ፊ-ሂነ" فِيهِنَّ ማለት "በ-ውስጣቸውም" ማለት ሲሆን "ሂነ" هِنَّ የሚለው ተሳቢ ተውላጠ ስም "ሰማዋት" سَمَاوَات የሚለውን አንስታይ ብዜት ተክቶ የመጣ ነው፥ ታዲያ ፀሐይ እና ጨረቃ በቅርቢቱ ሰማይ ውስጥ ሆነው ሳሉ ለምን "በሰማያት ውስጥ" ተባሉ? ሲባል ቅርቢቱ ሰማይ ከሰባቱ ሰማያት ውስጥ የመጀመሪያይቱ ሰማይ ናት፦
ሪያዱ አስ-ሷሊሒን መጽሐፍ 1, ሐዲስ 184
ስለ ኢሥራእ በዝነኛ ሐዲስ አነሥ”ረ. ዐ.” እንደተረከው፦ “የአላህ መልክተኛ”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ “ጂብሪል ከእኔ ጋር ወደ ቅርቢቱ ሰማይ ወጣ፥ እንዲከፈት ተጠየቀ። ዘበኛው፦ “ይህ ማን ነው? ብሎ ጠየቀ፥ ጂብሪልም፦ “ጂብሪል” አለ። “ከአንተ ጋር ያለውስ? እርሱም፦ “ሙሐመድ ነው” አለ። ከዚያም በተመሳሳይ ወደ ሁለተኛ፣ ወደ ሦስተኛ፣ ወደ አራተኛ እና ወደተቀሩት ሰማያት ሁሉ ወጣ። የሁሉም ሰማይ በር ላይ “ይህ ማን ነው? ተብሎ ተጠየቀ፥ “ጂብሪል ነው” ተባለ”። عن أنس رضي الله عنه في حديثه المشهور في الإسراء قال‏:‏ قال رسول الله صلى الله عليه وسلم ‏:‏ ‏ “‏ثم صعد بي جبريل إلي السماء الدنيا فاستفتح، فقيل‏:‏ من هذا‏؟‏ قال‏:‏ جبريل، قيل‏:‏ومن معك‏؟‏ قال‏:‏ محمد‏.‏ ثم صعد إلي السماء الثانية والثالثة والرابعة وسائرهن، ويقال في باب كل سماء‏:‏ من هذا‏؟‏ فيقول‏:‏ جبريل‏”‏

ለምሳሌ፦ "እኔ የምኖረው አፍሪካ ውስጥ ነው" ብል "ኢትዮጵያ ውስጥ ነው" ለማለት ፈልጌ እንጂ "ታንዛኒያ፣ አልጄሪያ፣ ናይጄሪያ ወዘተ ውስጥ ነው" ማለት አይደለም፥ በተመሳሳይ "ፀሐይ እና ጨረቃ በሰማያት ውስጥ ናቸው" ሲባል "ከሰባቱ ሰማያት የመጀመሪያይቱ ሰማይ ቅርቢቱ ሰማይ ውስጥ ናቸው" ማለት ነው። በተጨማሪ መላእክት የሚኖሩት በሰባተኛው ሰማይ ላይ እንደሆነ እሙን እና ቅቡል ነው፦
40፥7 እነዚያ ዐርሹን የሚሸከሙት እና እነዚያም በዙሪያው ያሉት በጌታቸው ምስጋና ያወድሳሉ፡፡ በእርሱም ያምናሉ፡፡ الَّذِينَ يَحْمِلُونَ الْعَرْشَ وَمَنْ حَوْلَهُ يُسَبِّحُونَ بِحَمْدِ رَبِّهِمْ وَيُؤْمِنُونَ بِهِ
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 10, ሐዲስ 176
አቢ ሁረይራህ"ረ.ዐ." እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም አሉ፦ "ከእናንተ ውስጥ አንዱ "አሚን" በሚልበት ጊዜ በሰማይ ውስጥ ያሉት መላእክት "አሚን" ይላሉ"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ ـ رضى الله عنه ـ أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ "‏ إِذَا قَالَ أَحَدُكُمْ آمِينَ‏.‏ وَقَالَتِ الْمَلاَئِكَةُ فِي السَّمَاءِ آمِينَ‏.‏

ነገር ግን መላእክት በሰባተኛ ሰማይ ቢኖሩም ሰባተኛ ሰማይ የሰማያት ክፍል ስለሆነ መልአክ በሰማያት ውስጥ እንደሚኖር ተገልጿል፦
53፥26 "በሰማያት ውስጥ ካለ መልአክም" ብዙዎች ሊማለዱለት ለሚሻው እና ለሚወደው ሰው ከፈቀደ በኋላ ቢኾን እንጂ ምልጃቸው ምንም አትጠቅምም፡፡ وَكَم مِّن مَّلَكٍ فِي السَّمَاوَاتِ لَا تُغْنِي شَفَاعَتُهُمْ شَيْئًا إِلَّا مِن بَعْدِ أَن يَأْذَنَ اللَّهُ لِمَن يَشَاءُ وَيَرْضَىٰ

ፀሐይ እና ጨረቃ በሰማያት ውስጥ መደረግን በዚህ ልክ እና መልክ መረዳት ነው እንጂ "ቁርኣን ስለ ሥነ-አጽናፈ ዓለም ጥናት"cosmology" ያለው ምልከታ የተሳሳተ ነው" ብሎ ያለ ዕውቅት የውሸት ድሪቶ በቅሰጣ ስልቻ ውስጥ መደረት ተገቢ አይደለም፥ እኛም "ከባዶ አንድ ሰርዶ" ብለን ከሚነሱ ቅሰጣዎች አንዱ ለሆነውን ቅሰጣ መልስ ሰተናል። ፀሐይ እና ጨረቃ የአሏህ ተአምራት ናቸው፦
41፥37 ሌሊትና ቀንም፥ ፀሐይ እና ጨረቃ ከምልክቶቹ ናቸው፡፡ وَمِنْ آيَاتِهِ اللَّيْلُ وَالنَّهَارُ وَالشَّمْسُ وَالْقَمَرُ
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 16, ሐዲስ 9
አቢ በክራህ" እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም አሉ፦ "ፀሐይ እና ጨረቃ ከአሏህ ተአምራት መካከል ሁለት ተአምራት ናቸው"። عَنْ أَبِي بَكْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏"‏ إِنَّ الشَّمْسَ وَالْقَمَرَ آيَتَانِ مِنْ آيَاتِ اللَّهِ،

"አያህ" آيَة ማለት "ምልክት" "ታምር" ማለት ሲሆን "አያት" آيَتَان ማለት ደግሞ "ምልክቶች" "ታምራት" ማለት ነው፥ በእርግጥም ፀሐይ እና ጨረቃ ከአሏህ ተአምራት መካከል ሁለት ተአምራት ናቸው። አሏህ ቀሳጢዎችን ሂዳያህ ይስጣቸው! ለእኛን ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
@islam_ustaz_abuhayder

ወሠላሙ ዐለይኩም
345 viewsedited  10:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-30 13:12:47 ያክብሩት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

4፥80 መልእክተኛውን የሚታዘዝ ሰው በእርግጥ አላህን ታዘዘ፡፡ مَّن يُطِعِ الرَّسُولَ فَقَدْ أَطَاعَ اللَّهَ

አምላካችን አሏህ የላከውን መልእክተኛ የሚታዘዝ አሏህ ታዘዘ ማለት ነው፥ ለምሳሌ፦ ነቢያችንን”ﷺ” መታዘዝ አሏህን መታዘዝ ነው፥ በነቢያችን”ﷺ” ላይ ማመጽ በአሏህ ላይ ማመጽ ነው፦
4፥80 መልእክተኛውን የሚታዘዝ ሰው በእርግጥ አላህን ታዘዘ፡፡ مَّن يُطِعِ الرَّسُولَ فَقَدْ أَطَاعَ اللَّهَ
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 33, ሐዲስ 46
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ "እኔን የሚታዘዝ በእርግጥ አሏህን ታዘዘ፥ እኔን የሚያምጽ በእርግጥ አሏህን አመጸ"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏”‏ مَنْ أَطَاعَنِي فَقَدْ أَطَاعَ اللَّهَ وَمَنْ يَعْصِنِي فَقَدْ عَصَى اللَّهَ

በተመሳሳይ መልእክተኛውን ኢየሱስን የሚያከብር የላከውን አምላክ ያከብራል፥ መልእክተኛውን ኢየሱስን የማያከብር የላከውን አምላክ አያከብርም፦
ዮሐንስ 5፥23 ሰዎች ሁሉ አብን "እንደ" ሚያከብሩት ወልድን ያክብሩት! ወልድን የማያከብር የላከውን አብን አያከብርም።

New International Version፦ "That all may honor the Son just as they honor the Father. Whoever does not honor the Son does not honor the Father, who sent him".

ግሪክ ካይኔ፦ ἵνα πάντες τιμῶσι τὸν υἱὸν καθὼς τιμῶσι τὸν πατέρα. ὁ μὴ τιμῶν τὸν υἱὸν οὐ τιμᾷ τὸν πατέρα τὸν πέμψαντα αὐτόν.

እዚህ አንቀጽ ላይ "እንደ" ለሚለው ተውሳከ-ግስ አብ የአምልኮ ክብር እንደሚገባው ወልድም የአምልኮ ክብር ይገባዋል ማለት ሳይሆን ወልድ መልእክተኛ ስለሆነ ይዞት የመጣውን መልእክት ታሳቢ በማድረግ መልእክተኛው ማክበር የላከውን ማክበር ነው፥ "ወልድን የማያከብር የላከውን አብን አያከብርም" የሚለው ኃይለ-ቃል ሊሰመርበት ይገባል። ተመሳሳይ ሰዋስው እስቲ እንይ፦
ኤፌሶን 5፥22 ሚስቶች ሆይ! ለጌታ "እንደ" ምትገዙ ለባሎቻችሁ ተገዙ።

እዚህ አንቀጽ ላይ "እንደ" ለሚለው ተውሳከ-ግስ መግባቱ ሚስት ጌታን እንደምትገዛ ባሏን መገዛት ይገባታል እያለ ነውን? ለጌታ በመስገድ እና በማምለክ እንደምትገዛ ለባሏ በመስገድ እና በማምለክ ትገዛ እያለ ነውን? "አይ አይደለም፥ ጌታን የምትገዛ ሴት ባሏን ትገዛ ማለት እንጂ ባሏን ጌታዋን በምትገዛው መጠን እና ይዘት ትገዛው ማለት አይደለም" ካላችሁ እንግዲያውስ ላኪውን የሚያከብር የተላከውን ማክበር አለበት በሚል ስሌት እና ቀመር ተረዱት! እንቀጥል፦
ኤፌሶን 6፥7 ለሰው ሳይሆን ለጌታ "እንደ" ምትገዙ በትጋት እና በበጎ ፈቃድ ተገዙ።

እዚህ አንቀጽ ላይ "እንደ" ለሚለው ተውሳከ-ግስ መግባቱ ባሮች ጌታን እንደሚገዙት ጌቶቻቸውን መገዛት ይገባቸዋል እያለ ነውን? ለጌታ በመስገድ እና በማምለክ እንደሚገዙት ለጌቶቻቸው በመስገድ እና በማምለክ ይገዙ እያለ ነውን? "አይ አይደለም፥ ጌታን የሚገዙ ባሮች ጌቶቻቸውን ይገዙ ማለት እንጂ ባሮች ጌቶቻቸውን በሚገዙበት መጠን እና ይዘት ይገዙት ማለት አይደለም" ካላችሁ እንግዲያውስ ላኪውን የሚያከብር የተላከውን ማክበር አለበት በሚል መልክ እና ልክ ተረዱት! ኢየሱስ፦ "እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል" ብሏል፥ እና ሐዋርያት ኢየሱስ ናቸውን? ተመሳሳይ ሰዋስው ነው፦
ማቴዎስ 10፥40 እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል፥ እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል።

"እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል" ማለት "ሐዋርያትን መቀበል ኢየሱስን እንደ መቀበል ነው" ማለት ከሆነ እንግዲያውስ "ወልድን የማያከብር የላከውን አብን አያከብርም" ማለት "ወልድን አለማክበር አብን እንደ አለማክበር ነው" ማለት ነው፥ "እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል" ማለት "ወልድን መቀበል አብን እንደ መቀበል ነው" ማለት ከሆነ "ወልድን ማክበር አብን እንደ ማክበር ነው" ማለት ነው። በእርግጥም ፈጣሪ እና ፍጡር በአንድ ነጠላ ግሥ ውስጥ ስለመጡ ያ ፍጡር ፈጣሪ ነው ወይም ያ ፍጡር ከፈጣሪ ጋር ይመለካል ማለት በፍጹም አይደለም፥ ምክንያቱም በብሉይ ኪዳን ይህንን የሚያሳይ ናሙና አለ፦
ዜና 35፥3 አሁንም አምላካችሁን ያህዌህን እና ሕዝቡን እስራኤልን አገልግሉ። עִבְדוּ֙ אֶת־יְהוָ֣ה אֱלֹֽהֵיכֶ֔ם וְאֵ֖ת עַמֹּ֥ו יִשְׂרָאֵֽל׃

"ዒብዱ" עִבְדוּ֙ ማለት "አገልግሉ" "ተገዙ" "አምልኩ" ማለት ነው፥ እና የእስራኤል ሕዝብ ከያህዌህ ጋር ይመለካል ማለት ነውን? "አይ የእስራኤል ሕዝብ ይገለገላል የተባለው ያህዌህ በሚገለገልበት ሒሣብ አይደለም" ካላችሁ እንግዲያውስ ወልድ የሚከበረው አብ በሚከበርበት ሒሣብ በፍጹም አይደለም። በተጨማሪም ተወዳጁ ነቢያችን"ﷺ" "ሰውን ያላመሰገነ አሏህን አያመሰግንም" ብለዋል፥ ያ ማለት ሰው የሚመሰገነው አሏህ በሚመሰገንበት መጠን እና ይዘት አይደለም፦
ሡነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 43, ሐዲስ 39
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ "ነቢዩም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ሰውን ያላመሰገነ አሏህን አያመሰግንም"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ "‏ لاَ يَشْكُرُ اللَّهَ مَنْ لاَ يَشْكُرُ النَّاسَ ‏"‏ ‏.‏

አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
@islam_ustaz_abuhayder

ወሠላሙ ዐለይኩም
296 viewsedited  10:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-30 13:12:46 ፨ሲያረብብ በ 376 ድኅረ-ልደት የተነሱት ኮልይሪዲያን"collyridian" ክርስቲያኖች ኢየሱስ "ቴዎስ" θεός ብለው ባሉበት አፋቸው ማርያምን በግልጽ "ቴአ" θεά ማለትም "ሴት አምላክ" ይሏታል፥ ካቶሊክ፣ ኦርቶዶስ፣ አንግሊካን ኢየሱስን "ኩሪዮስ" κύριος ብለው ባሉበት አፋቸው ማርያምን በግልጽ "ኩሪያ" κυρία ማለትም "ሴት ጌታ" ይሏታል። በአገራችን ኦርቶዶክሶች ደግሞ ኢየሱስን "እግዚእ" ብለው ባሉበት አፋቸው ማርያምን በግልጽ "እግዚኢት" ማለትም "ሴት ጌታ" ይሏታል፥ ኢየሱስን "እግዚኢነ" ማለትም "ጌታችን" እንደሚሉት ሁሉ ማርያምን "እግዚኢትነ" ማለትም "ጌታችን" ይሉአታል። "አምላክ" ለሚለው ነጠላ ቃል ብዜት "አማልክት" ሲሆን ጸያፍ ርቢው "አምላኮች" ነው፥ እናማ ከዚህ የበለጠ ማርያምን አምላክ አድርጎ መያዝ አለን? ይህ አምልኮ ካልሆነ ምን ይባላል? ይህ አምልኮተ ማርያም ከልጇ የተገኘ ትምህርት ስላልሆነ አምላካችን አሏህ ኢየሱስን፦ "አንተ ለሰዎቹ፡- "እኔን እና እናቴን ከአላህ ሌላ አማልክት አድርጋችሁ ያዙ ብለሃልን? ብሎ ይጠይቀዋል፦
5፥116 አላህም፡- «የመርየም ልጅ ዒሣ ሆይ! አንተ ለሰዎቹ፡- "እኔን እና እናቴን ከአላህ ሌላ አማልክት አድርጋችሁ ያዙ ብለሃልን?» በሚለው ጊዜ አስታውስ ፡፡ وَإِذْ قَالَ اللَّهُ يَا عِيسَى ابْنَ مَرْيَمَ أَأَنتَ قُلْتَ لِلنَّاسِ اتَّخِذُونِي وَأُمِّيَ إِلَـٰهَيْنِ مِن دُونِ اللَّهِ

እርሱም፦ "በእርሱ ያዘዝከኝን ቃል ጌታዬን እና ጌታችሁን አላህን ማለት ማለትን እንጂ ለእነርሱ ሌላ አላልኩም" በማለት መልስ ይሰጣል፦
5፥117 በእርሱ ያዘዝከኝን ቃል ጌታዬን እና ጌታችሁን አላህን ማለት ማለትን እንጂ ለእነርሱ ሌላ አላልኩም፡፡ مَا قُلْتُ لَهُمْ إِلَّا مَا أَمَرْتَنِي بِهِ أَنِ اعْبُدُوا اللَّهَ رَبِّي وَرَبَّكُمْ

"አምላክ" የሚለውም ቃል "መለከ" ማለትም "አመለከ" ከሚል የግዕዝ ቃል የመጣ ሲሆን "የሚመለክ" ማለት ነው። ከሣቴ ብርሃን ተሰማ የዐማርኛ መዝገበ ቃላት (2005) ገጽ 708)

ከዚህ አንጻር ዐበይት ክርስትና ማርያምን አያመልኳትምን? እንዴታ! ድብን አርገው ያመልካሉ። አንድ ሰው ፍላጎቱን አምላኩ አድርጎ ያዘ ማለት ፍላጎቱን አምላኬ ብሎ ጠራ ማለት ሳይሆን ለአምላክ የሚሰጠውን የአምልኮ ክፍል ለፍላጎቱ ቅድሚያ ሰጠ ማለት ነው፦
25፥43 ፍላጎቱን አምላኩ አድርጎ የያዘውን ሰው አየህን? አንተ በእርሱ ላይ ጠባቂ ትሆናለህን? أَرَأَيْتَ مَنِ اتَّخَذَ إِلَـٰهَهُ هَوَاهُ أَفَأَنتَ تَكُونُ عَلَيْهِ وَكِيلًا

የማርያምን አምላክ አርጎ መያዝ በዚህ ሒሳብ መረዳት ይቻላል። በተመሳሳይ ጳውሎስ፦ "ሆዳቸው አምላካቸው ነው" ብሏል፦
ፊልጵስዩስ 3፥19 መጨረሻቸው ጥፋት ነው፥ ሆዳቸው አምላካቸው ነው።

ያ ማለት ማለት ሆዳቸውን "አምላኬ" ብለው ጠሩ ማለት ሳይሆን ለአምላክ የሚሰጠውን የአምልኮ ክፍል ለሆዳቸው ቅድሚያ ሰጡ ማለት ነው፥ የማርያምን አምላክ አርጎ መያዝ በዚህ ስሌት መረዳት ይቻላል። በዐበይት ክርስትና አምልኮተ ማርያም የተዘፈቃችሁ ካላችሁ ሞት ሳይመጣባችሁ አሊያም የፍርዱ ቀን ከመምጣቱ በፊት ወደ አሏህ በንስሓ ተመለሱ!
አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
@islam_ustaz_abuhayder

ወሠላሙ ዐለይኩም
271 viewsedited  10:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-30 13:12:46 አምልኮተ ማርያም

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

5፥116 አላህም፡- «የመርየም ልጅ ዒሣ ሆይ! አንተ ለሰዎቹ፡- "እኔን እና እናቴን ከአላህ ሌላ አማልክት አድርጋችሁ ያዙ ብለሃልን?» በሚለው ጊዜ አስታውስ ፡፡ وَإِذْ قَالَ اللَّهُ يَا عِيسَى ابْنَ مَرْيَمَ أَأَنتَ قُلْتَ لِلنَّاسِ اتَّخِذُونِي وَأُمِّيَ إِلَـٰهَيْنِ مِن دُونِ اللَّهِ

እኛ ሙሥሊሞች፦ "ዐበይት ክርስቲያኖች ማለትም ኦርቶዶክስ፣ ካቶሊክ እና አንግሊካን ማርያምን ያመልካሉ" ስንል በተቃራኒው እነርሱ፦ "እናከብራታለን እንጂ አናምልካትም" ብለው ዓይናቸውን በጨው አጥበው ይዋሻሉ፥ ምክንያቱም "እናመልካታለን" ካሉ አምልኮ የሚገባው አንድ አምላክ እንደሆነ ባይብል ላይ በቅጡ ሰፍሯል፦
1ኛ ሳሙኤል 7፥3 ልባችሁንም ወደ ያህዌህ አቅኑ፥ እርሱንም ብቻ አምልኩ።
ማቴዎስ 4፥10 ለጌታህ ለአምላክህ ስገድ እርሱንም ብቻ አምልክ።

"እርሱንም ብቻ አምልኩ" "እርሱንም ብቻ አምልክ" የሚል ጥብቅ ትእዛዝ አስምርበት! "እርሱ" ተብሎ የተቀመጠ ነጠላ ተሳቢ ተውላጠ ስም አንድ ቀዋሜ ማንነትን ቁልጭ እና ፍንትው አርጎ ያሳያል፥ አምልኮ የሚገባው ይህ አንዱ ማንነት ብቻ ነው። ይህንን ጥቅስ ሲያዩ ጭራሽ ወደ ማርያም፦ "ከልጅሽ ጋር አስታርቂን ብለን እጠይቃታለን እንጂ ወደ እርሷ አንጸልይም" የሚል ቅጥፈት ይቀጥፋሉ።

፨ሲጀመር ሁሉን ዐዋቂ፣ ሁሉን ሰሚ እና ሁሉን ተመልካች አንዱ አምላክ ሆኖ ሳለ የማወቅ፣ የመስማት እና የመመልከት ውስንነት ያለበትን ፍጡር በሌለበት መለማመን ሆነ መጠየቅ ሺርክ ነው።

፨ሲቀጥል ወደ ማርያም ድብን አርጋችሁ ትጸልያላችሁ፥ የአዋልድ መጻሕፍቶቻችሁ ይህንን ያሳብቃሉ፦
መጽሐፈ አርጋኖን ዘሰኞ ምዕራፍ 2 ቁጥር 1
"እኔ በዚህ ጸሎት በጸለይሁ ጊዜ ወደ አንደበቴ ነገር ጆሮሽን ዘንበል አድርገሽ ስሚ፥ ሰምተሽም ቸል አትበይ። በብሩኅ ልቦና በንጹሕ አሳብ የአንደበቴን ነገር ተቀበይው እንጂ"።
ክብረ ድንግል ማርያም 1
"እርሷን "ደስ ይበልሽ" እያልን ይቅርታ እንድትሰጠው ወደ እርሷ እንጸልያለን"።

፨ሢሰልስ በግልጽ እና በማያሻማ መልኩ ለማርያም አምልኮ እንደሚገባት ኢትዮጵያዊ ቄርሎስ ተብሎ የሚሽሞነሞነው አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ተናግሯል፦
እንዚራ ስብሐት ምዕራፍ 12 ቁጥር 98, "ለአንቺም የምስጋና እጅ መንሻን አቀርባለሁ፣ በመፍራት እገዛልሻለሁ፣ በመስገድም እጅ እነሣሻለሁ። የአምልኮ መሥዋዕትንም ለአንቺ እሠዋለሁ"።

የአምልኮ መሥዋዕት ሊሰዋለት የሚገባው አንድ አምላክ ሆኖ ሳለ ለማርያም መሠዋቱ በራሱ ዓይን ያስፈጠጠ እና ጥርስ ያስገጠጠ ሺርክ ነው።
250 views10:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-30 13:12:46 በአፋን ኦሮሞ ደርሥ ተለቋል። ያንብቡ፦ https://t.me/Wahidomar1/39
240 views10:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-30 13:12:46 ባሪያ በባይብል

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

90፥13 እርሱም ባሪያን መልቀቅ ነው፡፡ فَكُّ رَقَبَةٍ

በባይብል ዕብራዊ ባሪያ በገንዘብ ከተገዛ ስድስት ዓመት አገልግሎ በሰባተኛው ዓመት ነጻ ይወጣል፥ ዕብራዊ ባሪያ ብቻውን በገንዘብ ተሽጦ ከሆነ ብቻውን ነጻ ይወጣል፥ ከእነ ሚስቱ ተሽጦ ከሆነ ሚስቱም በሰባተኛው ዓመት ከእርሱ ጋር ነጻ ትወጣለች፦
ዘጸአት 21፥2 ዕብራዊ ባሪያ የገዛህ እንደሆነ ስድስት ዓመት ያገልግልህ፥ በሰባተኛውም በከንቱ አርነት ይውጣ።
ዘጸአት 21፥3 ብቻውን መጥቶ እንደሆነ ብቻውን ይውጣ፤ ከሚስቱ ጋር መጥቶ እንደሆነ ሚስቱ ከእርሱ ጋር ትውጣ።

ቅሉ ግን ባሪያው ብቻውን ከተሸጠ በኃላ ገዢው ጌታ ሚስት ከዳረው እና ልጆች ከወለደ እርሱ በሰባተኛው ዓመት ነጻ ሲወጣ ሚስቱ እና ልጆቹ ግን ለገዛው ጌታ ባሪያ ይሆናሉ፥ በሰባተኛው ዓመት ይህ በገንዘብ የተገዛው ባሪያ ሚስቱ እና ልጆቹን ጥሎ ላለመሄድ ከፈለገ በገንዘቡ የገዛው ጌታ ወደ ፈራጆቹ ወስዶ ጆሮውን በወስፌ በስቶ ለዘላለም ባሪያ ያረገዋል፦
ዘጸአት 21፥4 ጌታው ሚስት አጋብቶት እንደ ሆነ ወንዶች ወይም ሴቶች ልጆች ብትወልድለት፥ ሚስቱና ልጆችዋ ለጌታው ይሁኑ፥ እርሱም ብቻውን ይውጣ።
ዘጸአት 21፥5 ባሪያውም፦ "ጌታዬን ሚስቴን ልጅቼንም እወድዳለሁ፥ አርነት አልወጣም" ብሎ ቢናገር፥ ጌታው ወደ "አማልክቱ" הָ֣אֱלֹהִ֔ים ይውሰደው፥ ወደ ደጁም ወደ መቃኑ አቅርቦ ጆሮውን በወስፌ ይብሳው፤ ለዘላለምም ባሪያው ይሁን።

እዚህ አንቀጽ ላይ "ሃ- ኤሎሂም" הָ֣אֱלֹהִ֔ים የተባሉት ፈራጆች ሲሆኑ ሰውን በዚህ ደረጃ ማሰቃየት ተገቢ ነውን? ከዕብራዊ ውጪ ያለ ባሪያ ደግሞ ባርነቱ የጊዜ ገደብ የለውም፥ ምክንያቱም እንደ ቦታ ርስት ናቸውና፦
ዘሌዋውያን 25፥44 ወንድ ባሪያና ሴት ባሪያ መግዛት ብትፈልግ ግን በዙሪያችሁ ካሉት ከእነርሱ ከአሕዛብ ወንድና ሴት ባሪያዎችን ግዙ።
ዘሌዋውያን 25፥45 ደግሞም በእናንተ መካከል ከሚቀመጡት መጻተኞች፥ በምድራችሁም ውስጥ ከወለዱአቸው በእናንተ መካከል ከሚቀመጡት ከዘራቸው ውስጥ ባሪያዎችን ግዙ፤ ርስትም ይሁኑላችሁ።

ሰውን ባሪያ አርጎ እንደ ሸቀጥ መግዛት እና መሸጥ በባይብል መደበኛ ሕግ ነው፥ እንግዲህ ከበርቴ መሸጥ የሚቻለው የሌላ ሰው ልጅ ብቻ ሳይሆን የገዛ ሴት ልጅን ጭምር ነው፦
ዘጸአት 21፥7 ሰውም ሴት ልጁን ለባርነት ቢሸጥ ባሪያዎች እንደሚወጡ እርስዋ አትውጣ።

በባይብል ባሪያ እንደ ሰው አይታይም፥ ሰው ሰውን ቢገድል ይገደላል፥ ነገር ግን ሰው ባሪያውን ቢገድል ይቀጣል እንጂ አይገደልም፦
ዘጸአት 21፥12 ሰው ሰውን ቢመታ ቢሞትም፥ እርሱ ፈጽሞ ይገደል።
ዘጸአት 21፥20 ሰውም ወንድ ባሪያውን ወይም ሴት ባሪያውን በበትር ቢመታ፥ ቢሞትበትም፥ ፈጽሞ ይቀጣ። የተመታው ግን አንድ ወይም ሁለት ቀን ቢቈይ ገንዘቡ ነውና አይቀጣ።

ሰው ባሪያውን ደብድቦት ባይሞት ምንም አይቀጣም። ባሪያ መግረፍ መደበኛ ሕግ መሆኑን የምናየው በኢየሱስ ትምህርት ውስጥ በተሰጠው ምሳሌ ነው፦
ሉቃስ 12፥47 የጌታውንም ፈቃድ አውቆ ያልተዘጋጀ እንደ ፈቃዱም ያላደረገ ያ ባሪያ እጅግ ይገረፋል።

"ሎሌ" ማለት "ወንድ ባሪያ" ማለት ሲሆን "ገረድ" ደግሞ "ሴት ባሪያ" ማለት ነው፥ በአዲስ ኪዳን እንኳን ባርነት ሊቀር ይቅርና ባሮች ለጠማማ ጌቶቻቸው በፍርሃት እንዲገዙ ወፍራም ትእዛዝ አለ፦
1 ጴጥሮስ 2፥18 ሎሌዎች ሆይ! ለበጎዎችና ለገሮች ጌቶቻችሁ ብቻ ሳይሆን ለጠማሞች ደግሞ በፍርሃት ሁሉ ተገዙ።
ኤፌሶን 6፥5 ባሪያዎች ሆይ! ለክርስቶስ እንደምትታዘዙ በፍርሃት እና በመንቀጥቀጥ በልባችሁ ቅንነት በሥጋ ጌቶቻችሁ ለሆኑ ታዘዙ።

ባሮች ለጌቶቻቸው መታዘዝ ያለባቸው ልክ ለክርስቶስ በፍርሃት እና በመንቀጥቀጥ እንደሚታዘዙት መሆን እንዳለበት ጳውሎስ አስረግጦና ረግጦ ይናገራል። መገዛት ያለባቸው ለታይታ ሳይሆን ከልባቸው መሆን አለበት፥ ከቀንበር በታች ያሉቱ ባሪያዎች ሁሉ ለገዙአቸው ጌቶች መገዛታቸው እና መታዘዛቸው እንደ ክብር መቁጠር አለባቸው፦
ቆላስይስ 3፥22 ባሪያዎች ሆይ፥ በቅን ልብ ጌታን እየፈራችሁ እንጂ፥ ለሰው ደስ እንደምታሰኙ ለታይታ የምትገዙ ሳትሆኑ በሥጋ ጌቶቻችሁ ለሆኑ በሁሉ ታዘዙ።
ቲቶ 2፥9-10 ባሪያዎች ስለ መድኃኒታችን ስለ እግዚአብሔር የሚሆነውን ትምህርት በሁሉ ነገር ያስመሰግኑ ዘንድ ለገዛ ጌቶቻቸው እንዲገዙ፣ በሁሉም ደስ እንዲያሰኙ፣ ሳይቃወሙና ሳይሰርቁም በጎ ታማኝነትን ሁሉ እንዲያሳዩ ምከራቸው።
1 ጢሞቴዎስ 6፥1 የእግዚአብሔር ስምና ትምህርቱ አንዳይሰደብ ከቀንበር በታች ያሉቱ ባሪያዎች ሁሉ ለገዙአቸው ጌቶች ክብር ሁሉ እንደ ተገባቸው ይቍጠሩአቸው።

ጥቁር ሰው በተለምዶ "ባሪያ" "ባሪዬ" "ባርች" የሚል ስያሜ የመጣው ምዕራባውያን አፍሪካውያንን በባርነት ከገዙበት ወዲህ ነው፥ ምዕራባውያ ክርስቲያኖች የባሪያ ንግድ ያጧጧፉት ብሉይ እና አዲስ ኪዳን ላይ ያሉትን አናቅጽ መሠረት አድርገው ነው። ስሌቭ"slave" የሚለው የእንግሊዙ ቃል እራሱ የመጣው ጀርመን ክርስቲያኖች ስላቭ"slavonic" ሕዝቦችን ወደ አሜሪካ አህጉር በባርነት መግዛት ከጀመሩበት ወዲህ ነው፥ ደቡብ አሜሪካን ያሉትን 642 ሚልዮን ሕዝቦች የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን በባርነት እና በጉልበት በመግዛት ላቲን አሜሪካ ያደረገችበት እና ዛሬ ከላቲን አሜሪካ ሕዝብ 69% ካቶሊክ የሆነው በባርነት ነው። በኢሥላም ባሪያን ከባርነት ማላቀቅ የከፍታ ማማ ነው፦
90፥11 ዓቀበቲቱንም አልወጣም። فَلَا اقْتَحَمَ الْعَقَبَةَ
90፥12 ዓቀበቲቱም መውጣቷ ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ? وَمَا أَدْرَاكَ مَا الْعَقَبَةُ
90፥13 እርሱም ባሪያን መልቀቅ ነው፡፡ فَكُّ رَقَبَةٍ

ክርስቲያኖች ሆይ! የቱን ትመርጣላችሁ? በሕጉ ውስጥ ባሪያን ነጻ ለማውጣት የሚያስተምረውን እሥልምናን ወይስ ባርነትን የሚያጠናክር እና የሚያበረታታ ክርስትና? አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
@islam_ustaz_abuhayder

ወሠላሙ ዐለይኩም
235 viewsedited  10:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ