2022-08-31 20:38:37
ያለማስጠንቀቂያ የሥራ ውል ስለሚቋረጥበት ሁኔታዎች /በአሰሪና ሰራተኛ አዋጅ መሠረት/
=======================
የሥራ ውል ከሠራተኛው ጠባይ ወይም የሠራተኛው የመሥራት ችሎታን ከሚመለከቱ ግልጽ ሁኔታዎች ወይም ከድርጅቱ ድርጅታዊ አቋም ወይም የሥራ እንቅስቃሴ ጋር ግንኙነት ባላቸው ምክንያቶች ብቻ ሊቋረጥ ይችላል፡፡
የሚከተሉት የሥራ ውልን ለማቋረጥ ተገቢ ምክንያቶች ሆነው ሊቆጠሩ አይችሉም፡፡
#ሠራተኛው በሠራተኞች ማኀበር አባል መሆኑ ወይም #በማኀበሩ ሕጋዊ ተግባሮች ተካፋይ መሆኑ፤
ሠራተኛው የሠራተኞች ተጠሪ ሆኖ ለመሥራት መፈለጉ ወይም መሥራቱ፤
ሠራተኛው በአሠሪው ላይ ቅሬታ ማቅረቡ ወይም በፍርድ ቤት በቀረበ ክስ ወይም በሌላ ሰው ክስ ተካፋይ መሆኑ፤
የሠራተኛው ብሔር፣ ጾታ፣ ሐይማኖት፣ የፖለቲካ አመለካከት፣ የጋብቻ ሁኔታ፣ ዘር፣ ቀለም፣ የቤተሰብ ኃላፊነት፣ የዘር ሐረግ፣ እርግዝና ወይም ማኀበራዊ አቋም፡፡
በአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156 አንቀጽ 27 ላይ እንደተመለከተው፦
1. በኀብረት ስምምነት በሌላ አኳኋን ካልተወሰነ በስተቀር የሥራ ውልን ያለማስጠንቀቂያ ማቋረጥ የሚቻለው በሚከተሉት ምክንያቶች ብቻ ነው፡፡
2. ሠራተኛው የሥራ ሰዓት ለማክበር የማይችልባቸው ሁኔታዎች ተብለው በኅብረት ስምምነት በሥራ ደንብ ወይም በሥራ ውሉ ከተዘረዘሩት ምክንያቶች ውጪ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ እየተሰጠው በስድስት ወር ውስጥ 3. በጠቅላላው ለስምንት ጊዜ የሥራ ሰዓት አለማክበር፤
በዚህ አዋጅ ከተመለከቱ እረፍቶች እና ልዩ ልዩ ፈቃዶች ውጪ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ እየተሰጠው በስድስት ወር ውስጥ ለአምስት ቀናት ከሥራ መቅረት፤
4. በሥራው ላይ የማታለል ተግባር መፈፀም፤
5. የራሱን ወይም የሌላ ሰው ብልጽግናን በመሻት በማንኛውም የአሠሪው ንብረት ወይም ገንዘብ አለአግባብ መጠቀም፤
6. ሠራተኛው ሥራውን ለመሥራት ችሎታ እያለው የሥራ ውጤቱ ባለማቋረጥ በኀብረት ስምምነት ወይም በሥራ ደንቡ ወይም በሁለቱ ወገኖች መግባባት ከተወሰነው የምርት ጥራትና መጠን በታች ሲሆን፤
6. እንደጥፋቱ ክብደት በሥራው ቦታ አምባጓሮ ወይም ጠብ አጫሪነት ተጠያቂ መሆን፤
7. በወንጀል ጥፋተኛ ሆኖ መገኘትና በጥፋቱም ምክንያት ለያዘው ሥራ ብቁ ሆኖ አለመገኘት፤
8. በአሠሪው ንብረት ወይም ከድርጅቱ ሥራ ጋር በቀጥታ ግንኙነት ባለው ማናቸውም ንብረት ላይ ሆነ ብሎ ወይም በከባድ ቸልተኝነት ጉዳት ማድረስ፤
9. በአንቀጽ 14 ንዑስ አንቀጽ (2) የተመለከቱትን ሕገወጥ ድርጊቶች መፈጸም፤
10. በሠራተኛው ላይ ከ30 ቀናት ለሚበልጥ ጊዜ የእሥራት ፍርድ ተወስኖበት ከሥራ ሲቀር፤
11. ያለማስጠንቀቂያ የሥራ ውል ለማቋረጥ ያስችላሉ ተብለው በኀብረት ስምምነት የተወሰኑ ሌሎች ጥፋቶችን መፈፀም፤
12. አንድ አሠሪ በዚህ አንቀጽ መሰረት የሥራ ውል በሚያቋርጥበት ጊዜ የሥራ ውሉ የሚያቋረጥበትን ምክንያትና ቀን በመጥቀስ ለሠራተኛው በፅሁፍ መግለፅ አለበት፡፡
አንድ አሠሪ በዚህ አንቀጽ መሰረት የሥራ ውሉን ለማቋረጥ ያለው መብት ውሉ የሚቋረጥበት ምክንያት መኖሩን ካወቀ ከ30 የሥራ ቀናት በኋላ በይርጋ ይታገዳል፡፡
በዚህ አንቀጽ መሰረት የሠራተኛው የሥራ ውል እንዲቋረጥ ከመደረጉ በፊት ሠራተኛውን ከሥራ አግዶ ማቆየት ስለሚቻልበት ሁኔታ በኅብረት ስምምነት ሊወሰን ይችላል፡፡ ሆኖም የዕገዳው ጊዜ ከ30 የሥራ ቀናት መብለጥ የለበትም፡፡
Via Tsegaye Demeke - Lawyer
@healthinovation
3.9K viewsAndu Alem, 17:38