Get Mystery Box with random crypto!

Gorgora Media

የቴሌግራም ቻናል አርማ gorgoramedia — Gorgora Media G
የቴሌግራም ቻናል አርማ gorgoramedia — Gorgora Media
የሰርጥ አድራሻ: @gorgoramedia
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 5.23K
የሰርጥ መግለጫ

@GorgoraMedia

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2022-07-07 19:30:51 መንግስት በዜጎች ላይ እየፈጸመ ያለውን የተራዘመ እስር እንዲያቆም ኢሰመኮ አሳሰበ!!!

ኢሰመኮ ጋዜጠኞች በስራቸው ምክንያት ለእስር መዳረጋቸውንም አስታውቋል።

መንግስት በህግ ማስከበር ስም በርካታ ዜጎችን በኢመደበኛ ማቆያዎች ማሰሩን እንዲያቆምም ድርጅቱ አሳስቧል።

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን /ኢሰመኮ/ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ባወጣው መግለጫ መንግስት በዜጎች ላይ የተራዘመ እስር እየፈጸመ መሆኑን አስታውቋል።

የፌዴራል እና የክልል የፀጥታ አካላት በአፋጣኝ የተያዙ ሰዎች የሚገኙበትን ቦታ እንዲገልጹና ተዓማኒ ክስ የማይቀርብ ከሆነ በአፋጣኝ ከእስር እንዲለቀቁ አሳስቧል።

ኢሰመኮ ከግንቦት ወር 2014 ዓ.ም. ጀምሮ በተለይም በአዲስ አበባ ከተማ እና በአማራ ክልል፣ እንዲሁም ለበርካታ ወራት በኦሮሚያ ክልል የታሰሩ ጋዜጠኞች እና የሚድያ ሠራተኞች መኖራቸውን እረጋግጫለሁ ብሏል።

በተለይም በአማራ ክልል የሕግ የበላይነትን ለማስከበር በሚል በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች የታሰሩ ሰዎችን አስመልክቶ የፌደራልም ሆነ የክልል የፀጥታ ኃይሎች ተጠርጣሪዎችን ለተራዘመ የቅድመ ክስ እስር ከመዳረግ፣ ጋዜጠኞችን በሥራቸው ምክንያት ከማሰር እና ከፍርድ ቤት ትዕዛዝ ውጭ ሰዎችን ከማሰር፣ ኢመደበኛ በሆኑ ማቆያዎች ከማሰር ሊታቀቡ እንደሚገባም በተደጋጋሚ አሳስቤያለሁ ብሏል።

በተመሳሳይ መልኩ በትግራይ ክልል ጋዜጠኞች ምስግና ስዩም፣ ተሾመ ጠማለው፣ ኃይለሚካኤል ገሰሰ እና ሃበን ሐለፎምን ጨምሮ 15 የሚዲያ ሠራተኞች ከተገባደደው የግንቦት ወር 2014 ዓ.ም. አጋማሽ ጀምሮ ተይዘው በእስር ላይ እንደሚገኙ አረጋግጫለሁም ብሏል ኢሰመኮ በመግለጫውታውቋል።

በተለይም በመገናኛ ብዙኃን አዋጅ ቁጥር 1238/2013 (ሚዲያ አዋጅ) መሰረት በመገናኛ ብዙኃን አማካይነት የወንጀል ድርጊት በመፈጸም የተጠረጠረ ማንኛውም ሰው ወይም አካል፣ በወንጀል ሥነ-ሥርዓት ሕግ ድንጋጌዎች መሰረት ለተጨማሪ ምርመራ በእስር እንዲቆይ ሳይደረግ ክሱ በቀጥታ በዐቃቤ ሕግ አማካኝነት ለፍርድ ቤት መቅረብ ያለበት መሆኑን በማስታወስ ኮሚሽኑ በሚድያ ሠራተኞች ላይ የተጀመሩ የሕግ ሂደቶች በዚሁ መሰረት እንዲተገበሩ ጥሪ አቅርቧል።

እንዲሁም በማናቸውም ጊዜ ቢሆን የተያዙና በእስር ላይ የሚገኙ ሰዎች አያያዝ የሰብአዊ መብቶችን ያከበረ ሊሆን እንደሚገባ እና በክልልም ሆነ በፌዴራል የፀጥታ አካላት የተያዙ ሰዎች የሚገኙበትን ቦታ የማሳወቅ፣ የሕግ አማካሪ እና የቤተሰብ ጥየቃን መብት የማክበር እንዲሁም በአፋጣኝ ፍርድ ቤት የማቅረብ መብቶችን ሊያከብሩ እንደሚገባ ኮሚሽኑ አሳስቧል።

በአዲስ አበባ ከተማ ከግንቦት ወር 2014 ዓ.ም. ጀምሮ ተይዘው የቆዩ የሚድያ ሠራተኞች መካከል በተለያዩ ጊዜያት በፍርድ ቤት የዋስትና መብታቸው ተከብሮ የተለቀቁ መሆኑን ኮሚሽኑ ተመልክቷል።

በአማራ ክልል ከግንቦት ወር 2014 ዓ.ም. ጀምሮ በተለይም የሚገኙበት ቦታ ሳይገለጽ፣ ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ፣ በአብዛኛው ኢመደበኛ በሆኑ እና ከመኖሪያ አካባቢያቸው በራቀ ቦታ ለብዙ ሳምንታት ተይዘው የቆዩ በርካታ ሰዎች በባሕር ዳር ወደሚገኙ ማቆያ ቦታዎች መዛወራቸውን፣ እንዲሁም በእነዚሁ ቦታዎች ከቆዩ ሰዎች መካከል ይገኙ የነበሩ የሚድያ ሠራተኞች ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ መደረጋቸውን ተረድቻለሁ ብሏል፡፡

ኮሚሽኑ ክትትል ባደረገባቸው የተወሰኑ ጉዳዮች በፍርድ ቤት የዋስትና መብት የተጠበቀላቸውን ተጠርጣሪዎች በዋስትና ውሳኔው ላይ ይግባኝ ተጠይቋል ወይም ለሌላ የወንጀል ምርመራ ተጨማሪ ጊዜ አስፈልጓል በሚል ምክንያት የፍርድ ቤት ትዕዛዞችን በመጣስና ታሳሪዎቹን በቁጥጥር ስር በማቆየት ሕገወጥ እስር እየተፈጸመ መሆኑን እንዳረጋገጠ አስታውቋል።

በተጨማሪም በአዲስ አበባ ከተማ ጋዜጠኛ ያየሰው ሽመልስ ሰኔ 21 ቀን 2014 ዓ.ም. ከጠዋቱ 12፡00 ሰዓት፣ እንዲሁም ጋዜጠኛ አበበ ባዩ ከሰኔ 22 ቀን 2014 ዓ.ም. ከምሽቱ 4፡00 ሰዓት የሲቪል ልብስ በለበሱ የፀጥታ ኃይሎች ከተወሰዱ በኋላ ያሉበት ቦታ ያለመገለጹን ኮሚሽኑ በከፍተኛ ሁኔታ እንዳሳሰበው ገልጿል።

እነዚህን እስሮች በተመለከተ የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ “የዘፈቀደ፣ ሕገ ወጥ እና በተለይም ተጠርጣሪዎች የሚገኙበትን ቦታ ሳያሳውቁ የሚደረጉ እስሮች ሰዎችን ለከፍተኛ ስጋት፣ ቤተሰቦችን ለጭንቀት መዳረጉን ተናግረዋል።

በመንግሥት የፀጥታ አካላት እውቅናና ሆነ ተብሎ ሰዎችን ከሕግ እይታ ውጪ እንዲሆኑ ማድረግ የአስገድዶ መሰወር ድርጊት ሊሆን የሚችል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ነው ያሉት ኮሚሽነሩ በፍርድ ቤት ትዕዛዝ በዋስ እንዲፈቱ መብታቸው የተጠበቀላቸውን ተጠርጣሪዎች ከሕግ አግባብ ውጭ በቁጥጥር ስር ማቆየት የሕግ የበላይነትን በከፍተኛ ሁኔታ የሚሸረሽር ነውም ብለዋል።

ኮሚሽኑ የፌዴራል እና የክልል የፀጥታ አካላት በአፋጣኝ የተያዙ ሰዎች የሚገኙበትን ቦታ እንዲገልጹና ተዓማኒ ክስ የማይቀርብ ከሆነ በአፋጣኝ እንዲለቀቁ እንዲያደርጉ፤ እንዲሁም በመገናኛ ብዙኃን አማካይነት ተፈጽሟል ተብሎ ለሚጠረጠር የወንጀል ድርጊት ተጠርጣሪው ለምርመራ በእስር እንዲቆይ ሳይደረግ ክሱ በቀጥታ በዐቃቤ ሕግ አማካኝነት ለፍርድ ቤት መቅረብ እንዳለበት ኮሚሽኑ አሳስቧል።
861 views16:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 16:09:43
1.1K views13:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 16:09:35 #AhaduBank

አሐዱ ባንክ ሐምሌ 9 ቀን 2014 ዓ.ም ሥራውን በይፋ ይጀምራል።

ይህ አስመልክቶ ባንኩ ዛሬ መግለጫ ሰጥቶ ነበር።

የባንኩ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ አንተነህ ሰብስቤ ፤ 10 ሺህ በሚደርሱ ባለአክሲዮኖችንና በ564 ሚሊዮን የተከፈለ ካፒታል እና በ702 ሚሊዮን በተፈረመ ካፒታል ተዋቅሯል ብለዋል።

ሀላፊው እስከ መስከረም 30 ቀን 2015 ዓ/ም የቅርንጫፎቹን ብዛት 50 እደሚያደርስም ተናግረዋል።

ባንኩ ፦

ከሚያቀርበው ብድር እስከ 15 በመቶ የሚሆውን ለስራ ፈጣሪዎች እና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ማቅረቡ

ከተለመደዉ በሰራተኛ ከታገዘ የቅርንጫፍ አገልግሎት በተጓዳኝ ደንበኞች በራሳቸዉ የዲጂታል አገልግሎት የሚያገኙበት የቅርንጫፍ ዉስጥ አገልግሎት አደረጃጀት ማመቻቸቱ

የገጠር የባንክ አገልግሎትን ለአርሶና አርብቶ አደሮች፣ የገበሬ ማህበራት ለማዳረስ መዘጋጅቱ

የውስጥ አሰራሩን ወረቀት አልባ ማድረጉ

ደንበኞች ካሉበትና ቦታ ሆነዉ ራሳቸዉን የባንኩ ደንበኛ ማድረግ የሚችሉበትን አሰራር ማምጣቱ ልዩ ያደርገዋል ተብሏል።

ባንኩ ከሀምሌ 2 እስከ ሀምሌ 7 /2014 የተለያዩ ማህበራዊ ግዴታዎች እንደሚያከናውን የገለፀ ሲሆን " አንድ ቅርንጫፍ ለአንድ ልጅ " በሚል
ባንኩ በሚከፍታቸዉ ቅርንጫፎች ቁጥር ልክ ድጋፍ እና እገዛ ለሚያስፈልጋቸዉ ልጆች ዓመታዊ ወጪያቸዉን እንደሚሸፍን ገልጿል።

ባንኩ በተጨማሪም አዲሱ መለያ ሎጎውንም በይፋ አስተዋውቋል።

@GorgoraMedia
1.1K views13:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 15:03:01 በአርቲ ቡርቲ ንግግር የታጀበው የእለቱ መልዕክት
➔በኢትዮጵያ ውስጥ የተገደለው አማራ ቁጥር ከአሜሪካውያን ጋር ሲወዳደር ኢምንት ነው። ስለዚህ ጭፍጨፋው ይቀጥላል።

➔እናቴ ከሠጠችኝ ዙፋን ላይ ማንም አይነቀንቀኝም።
➔ሰው የሞተበት ቦታ ላይ ችግኝ እንተክላለን
ቢያንስ አስክሬኑ ጥላ እንዲኖረው...
➔እኛ ያደግንበትን ቁማር ተጠቅማችሁ እኔን እና ሽመልስን መነጣጠል የምትሞክሩ አይሳካላችሁም።
1.1K views12:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 14:06:36
1.2K views11:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 14:06:32 "ችግኝ ትከሉ ፥ ቢያንስ ፣ ቢያንስ ለአስከሬኑ ጥላ ይሆናል።"
ጠ/ሚ ዓቢይ አህመድ
ምን አይነት መረገም ነው በሥላሴ

@GorgoraMedia
1.1K views11:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 14:04:14
1.1K views11:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 14:03:51 አስመሳዩ፣ አጭበርባሪው፣ ጨፍጫፊውና አስጨፍጫፊው፣ አሸባሪው የወያኔ ኩሊ አቶ አቢይ አሕመድ ሆይ እነኝህን ዘጠኝ ጥያቄዎች የመመለስ ብቃት፣ ሞራልና ድፍረት አለህ ወይ???

1ኛ. አሜሪካ ውስጥ የሽብር ጥቃት የሚፈጸመው የጥቃት ሰለባዎቹ የአሜሪካ መንግሥትን "በአሸባሪዎች ልንጨፈጨፍ ተከበናል ድረስልን!" እያሉ አስቀድመው የድረሱልን ጥሪ እያሰሙ የአሜሪካ መንግሥት ሳይደርስላቸው ቀርቶ ወይም ለጥቃት አጋልጦ ስለሰጣቸው ነው ወይ የሽብር ጥቃት የሚፈጸምባቸው???

2ኛ. የካውንቲ አመራሮች የሽብር ጥቃት ከመፈጸሙ በፊት ሁልጊዜ የነዋሪውን ትጥቅ ገፈው ነዋሪውን ለጥቃት አመቻችተው ሲያበቁ ካውንቲውን ለቀው ስለሚወጡ ነው ወይ በዜጎች ላይ የሽብር ጥቃቶች የሚፈጸሙት???

3ኛ. የአሜሪካ መንግሥት መዋቅር ከላይ እስከ ታች ከአሸባሪዎቹ ጋር ተባብሮ ስለሚሠራ ነው ወይ አሜሪካ ውስጥ የሽብር ጥቃት የሚፈጸመው???

4ኛ. የአሜሪካ መንግሥት የጸጥታ አካላት "አልታዘዝንም!" እያሉ እዚያው ቆመው እያዩ ዜጎችን በአሸባሪዎች ስለሚያስጨፈጭፉ ነው ወይ አሜሪካ ውስጥ የሽብር ጥቃት የሚፈጸመው???

5ኛ. የአሜሪካ መንግሥት አሜሪካ ውስጥ ከአሸባሪዎች ጋር ተባብረው የሽብር ጥቃት የሚያስፈጽሙ አመራሮችና የጦር መኮንኖች ስላሉና እነሱን ለፍርድ ስለማያቀርብ ወይም ተጠያቂ ስለማያደርግ ነው ወይ አሜሪካ ውስጥ የሽብር ጥቃት የሚፈጸመው???

6ኛ. አሜሪካ ውስጥ ዜጎችን "ክልላቹህ አይደለም!" ብሎ በገዛ ሀገራቸው ስደተኛ የሚያደርጋቸውና ለጥቃት የሚያጋልጣቸው ሕገመንግሥት ስላለ ነው ወይ አሜሪካ ውስጥ በዜጎች ላይ የሽብር ጥቃት የሚፈጸመው???

7ኛ. የአሜሪካ ሕገመንግሥት አንዱን ዘር ለይቶ ሐሰተኛ የጥላቻ ትርክት ስለሚነዛበትና የጥቃት ዒላማ ወይም ሰለባ ስላደረገው ነው ወይ አሜሪካ ውስጥ የሽብር ጥቃት የሚፈጸመው???

8ኛ. አሜሪካን ሀገር ውስጥ ወንጀልን በስሙ የመጥራት የሞራል ብቃት የሌለው፣ በዚህ ድርጊቱም ለአሸባሪዎች ሽፋን የሚሰጥ፣ ትጥቅ የሚያስታጥቅና የሽብር ጥቃቶችን ለመከላከል ቁርጠኛ ያልሆነ ሸፍጠራ፣ ሴረኛ፣ ፀረ ሕዝብ መንግሥት ስላለ ነው ወይ አሜሪካ ውስጥ በዜጎች ላይ የሚፈጸመውን የሽብር ጥቃት ማስቆም ያልተቻለው???

9ኛ. አገዛዙ እርስዎ እንዳሉት እየተፈጸሙ ባሉ የዘር ማጥፋት ጭፍጨፋዎች እጁ ከሌለበት ለምንድን ነው ታዲያ እነዚህን ሁሉ ክፍተቶች የፈጠረውና "የሚፈጸሙ የዘር ማጥፋት ጭፍጨፋዎችን በገልተኛ አካላት ይጣራ!" ሲባል "ከቶ እንዴት ተደርጎ? አንገቴ ይታረዳል እንጅ ፈጽሞ አይደረግም!" የሚሉት???

አዎ በእርግጥ አገዛዙ እየፈጸመውና እያስፈጸመው ያለውን የአማራን ዘር የማጥፋት ጭፍጨፋን እየተከላከለ ያለ መስሎ ለመታየት በሚያደርጋቸው የሴራ ውጊያዎች ውስጥ እንዲገቡና እንዲገደሉ የሚደረጉ ምስኪን የዋሃን ጸጥታ አካላት አሉ፡፡ እነሱ ግን ለእናንተ ቁማራቹህን የምትቆምሩባቸው በጦስ ዶሮዎች ሲሆኑ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ግን መሥዋዕትነት የከፈሉ የግፍ ሰለባ ውድ ልጆቹ ናቸው እንጅ አገዛዙ ሰላምና ጸጥታን የማስከበር ፍላጎት ኖሮት ይሄንን ለማድረግ ሲንቀሳቀስ መሥዋዕትነት እንዲከፍሉ ያደረጋቸው ወታደሮች ወይም የጸጥታ አካላት አይደሉም!!! ይሄ ላለመሆኑ ከላይ የተነሡት የአገዛዙን አሻጥር፣ ቁማርና ሴራ የሚያጋልጡ መስቀለኛ ጥያቄዎች ያረጋግጣሉ!!!

እናም አሸባሪው፣ ጨፍጫፊውና አስጨፍጫፊው እናንተ እራሳቹህ ወያኔ/ኢሕአዴጎችና እንደ ኦነግ ያሉ አጋሮቻቹህ ናቹህ እንጅ ሌላ ማንም አይደለም!!!

ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

@GorgoraMedia
1.1K views11:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 11:18:48 ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀገራቸው አሜሪካ ባለፉት 6 ወራት ያጋጠማትን የሽብር አደጋና የህይወት መጥፋት ሪፖርት እያቀረቡ ነው።

@GorgoraMedia
2.1K viewsedited  08:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 11:10:55 ፓርላማው በእንቶ ፈንቶ ተሞልቷል!!!
ጥያቄው ሌላ መልሱ ሌላ
1.2K views08:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ