Get Mystery Box with random crypto!

Gorgora Media

የቴሌግራም ቻናል አርማ gorgoramedia — Gorgora Media G
የቴሌግራም ቻናል አርማ gorgoramedia — Gorgora Media
የሰርጥ አድራሻ: @gorgoramedia
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 5.23K
የሰርጥ መግለጫ

@GorgoraMedia

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-09-01 14:30:18 ባለፈው ሳምንት የኢትዮጵያ አየር ሃይል ቀንድቦ ከጣለው የግብጽ አውሮፕላን ውስጥ ኢትዮጵያውያን ( የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የቀድሞ ከፍተኛ አመራሮች የነበሩ እና በስራ አጋጣሚ ወደ ትግራይ ልዩ ሃይል ተዛውረው መከላከያን ለመውጋት የወሰኑ ) እንዳሉበት እየተሰማ ነው።

መቼም አየርሃይል ታሪካዊ ጠላታችን የሆነችውን የግብጽን አውሮፕላን ሲመታ ውስጡ የትግራይ ጀነራሎች ይኖራሉ ብሎ አልገመተም ነበር። ከግብጽ ጋር የሚሰራ ኢትዮጵያዊ ይኖራል ብሎ ማን ይገምታል?!

ለሟች ቤተሰቦች መጽናናትን እመኛለሁ!!
Andualem Buketo Geda
1.3K views11:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 14:12:39
1.2K views11:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 14:12:36 የትግራይ ኃይሎች ከአማራ ክልል እንዲወጡ የብሪታንያ የአፍሪካ ጉዳዮች ሚኒስትር ጠየቁ
የትግራይ ኃይሎች በአማራ ክልል የጀመሩትን ውጊያ አቁመው ወደ ትግራይ ክልል እንዲመለሱ የብሪታንያ የአፍሪካ ጉዳዮች ሚኒስትር ቪኪ ፎርድ ጠየቁ። ሚኒስትሯ በትግራይ የሚገኙ የኤርትራ ኃይሎች ክልሉን ለቀቅው መውጣት አለባቸው ብለዋል።
ቪኪ ፎርድ ይህን ያሉት የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) እና የኢትዮጵያ መንግስት ኃይሎች ዳግም ወደ ግጭት መመለሳቸውን በተመለከተ ዛሬ ሐሙስ ነሐሴ 26፤ 2014 ባወጡት መግለጫ ነው። ሁለቱ ኃይሎች እንደገና ወደ ግጭት መግባታቸው ለኢትዮጵያ ህዝብ “መከራ የሚያመጣ” ነው ያሉት የብሪታንያ የአፍሪካ ጉዳዮች ሚኒስትር፤ በክስተቱ በአስር ሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ህይወታቸውን የማጣት አደጋ እንደተጋረጠባቸው ገልጸዋል።
በሁለቱ ኃይሎች ውጊያ ምክንያት በቀጥታ ከሚደርሰው የሰዎች ሞት ባሻገር፤ በአሳሳቢ ሁኔታ ላይ የሚገኘው ሰብዓዊ ሁኔታ በግጭቱ ምክንያት ይበልጥ ስለሚባባስ የሰዎችን ሞት ሊያስከትል እንደሚችል ፎርድ በመግለጫቸው ጠቁመዋል። የሰሜን ኢትዮጵያው ግጭት በትግራይ፣ በአማራ እና አፋር የሚገኙ 13 ሚሊዮን ሰዎችን የሰብዓዊ እርዳታ ፈላጊ እንዳደረጋቸው ያስታወሱት ሚኒስትሯ፤ የአሁኑ ውጊያ እና በህወሓት የተያዘው የዓለም የምግብ ድርጅት ነዳጅ፤ የሰብዓዊ ድርጅቶችን ስራ “ይበልጥ አስቸጋሪ ያደርገዋል” ብለዋል።
የብሪታንያ መንግስት፤ ህወሓት የያዘውን ነዳጅ ለእርዳታ ማከፋፈል እና ለሌሎች አንገብጋቢ አገልግሎቶች እንዲውል እንዲያደርግ ጥሪ ያቀርባል ሲሉም የአፍሪካ ጉዳዮች ሚኒስትሯ አክለዋል። የኢትዮጵያ መንግስት በትግራይ መሰረታዊ አገልግሎቶቹን በአስቸኳይ ወደነበሩበት እንዲመለሱ እንዲያደርግ የብሪታንያ መንግስት ተመሳሳይ ጥሪ እንደሚያቀርብም ፎርድ በመግለጫቸው አስፍረዋል።
1.2K views11:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 13:03:41
1.1K views10:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 13:03:36 ለአማራ ህዝብ የተከፈለ ዋጋ!!!

የአማራ ካድሬዎች ለህውሓት በሚያሸረግዱበት ወቅት የመግስት አሰራር ትክክል አይደለም በማለቱ ከአመራርነት ታግዶ ነበር። አብይ ወደ ስልጣን ሲመጣ በአዴን የቀድሞ የቁርጥ ልጆችን ወደ አመራር እመልሳለሁ ባለው መሰረት አቶ ዮሃንስ ቧያለው ወደ አመራርነት መጡ።

የኦሮሞ ብልጽግና የበላይነቱን እና ተረኝነቱን ሲጀምር ፊት ለፊት ትክክል አይደለም በማለት መቃወም ጀመሩ። በመጨረሻ በአብይ መሩ ቡድን የአማራ ህዝብ የቁርጥ ቀን ልጅ የሆነው አቶ ዮሐንስ ቧያለው መንግስታዊ በደል ተፈጸመበት።

መንግስታዊ ስርዓቱ የአማርና የኢትዮጵያን ህዝብ ለጭፍጨፋ እና ለውድመት ዳርጓል በማለት እና ተረኛውን ስርዓት በማውገዙ ምክንያት በደሉ እንደተፈጸመበት ለማረጋገጥ ችለናል።

ፋኖነት በሚለው መጸሃፍ ላይ ስለ ጥቁር ክላሽ ባደረጉት ንግግር ከፍተኛ አመራሩ አቶ ዮሐንስ እንዲታፈን ቢወስኑም ያለመከሰስ መብት እንዳለው ስለተገነዘቡ ለግዜው እንደተውት ሰምተናል።

በደል 1: ሞጋች እና ትክክል ያልሆ ስራን ፊት ለፊት ስለሚቃወም የአብይ መንግሰት አቶ ዮሃንስን ከማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነት አባረረው።

በደል 2: በአዲስ መልክ በብቃት ቢያደራጅም  የውጭ ጉዳይ ጥናት በዳይሬክተርነትን ስልጣን ነጥቆ ደመወዝ ፣ መኪና እና ጥቅማጥቅሙን አገደበት። ጥበቃዎቹን አንስተው በደህንነት ስጋት ውስጥ ጣሉት።

በደል 3: ወደ ውጭ ጉዞ ለማድረግ ኤርፖርት ቢገኝም አቶ ተመስገን የሚመራው የደህንነቱ ቢሮ እና ጠቅላይ ሚኒስትሩ ትዕዛዝ በማስተላለፋቸው ከኤርፖርት ነሀሴ 25/2014 ዓ.ም አስመለሱት። ወደ ቤቱ ሲመለስ የመጨረሻውን በደል ፈጸሙበት።

በደል 4: የመኖሪያ ቤቱን አሽገው ልጆችን ሜዳ ላይ ጥለው አገኛቸው። ይህም የተፈጸመው በከፍተኛ አመራሩ ቀጥተኛ ትዕዛዝ ነው።  ቤቱ በግሉ ያገኝው የመንግሰት ቤቶች አስተዳደር ነው። ውል ይዞ ክራይ የሚከፍልበት ሲሆን፣ አመራር በመሆኑ የተሰጠው እንዳልሆነ አረጋግጠናል ።

የትግራይ የቀድሞ ጀነራሎች፣ እነ ጃዋር መሃመድ፣ የኦነግ መሪዎች እነ ዳውድ ኢብሳ፣ እነ ሌንጮ ለታ፣ እነ ዲማ ነገዎ ቤትና መኪና  አጃቢ ተመድቦላቸው በሚንቀሳቀሱበት ሀገር የአማራን ታጋይ ቅስም ለመስበር የብልጽግና መንግሰት የፈጸመው ሴራ ነው።

አማራ የቁርጥ ቀን ታጋይ ልጆችህን ታደግ!!!
1.2K views10:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 08:39:46 #Amhara #Harbu

በሐርቡ ትናንት ከምሽቱ1:37 ሰዓት 13 ሰርጎ ገቦች በአማራ ፋኖና ሚሊሻ ተይዘዋል።
ይህም የሚያሳየው በጣም ብዙ ሰርጎ ገቦች በተለያዩ የአማራ ቦታውች ተበትነው እንደገቡ ነው።
1.3K views05:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 21:24:34
659 views18:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 21:24:30 ታዳጊዋ የ10,000.00 ዶላር ሽልማቷን ለብፁዕነታቸው አበረከተች!
ይችን ድንቅ ብላቴና ሎዛ ትባላለች። በትምህርቷ እጅግ ድንቅ ብቃት በማስመዝገቧ የ10ሺ ዶላር ሽልማት ትምህርት ቤቷ ይሸልማታል።
ልበ በርሀኗ ሎዛ በአሜሪካ በተለያዩ ከተሞች እየዞሩ ለፈረሰችው ወልድያ እና ላሊበላ ገንዘብ እየሰበሰቡ ለሚገኙት ብፁዕ አቡነ ኤርሚያስ ቃል ገብታ ሰነበተች።

ታዲያ ዛሬ በቅዱስ ገብርኤል ዲሲ የተገኙት ብፁእነታቸው እዚህም በመሰብሰብ ላይ እያሉ ይች ትንሽዬ ብላቴና "ካለኝ ላይ ቀንሼ ሳይሆን የተሸለምኩትን ሙሉ ብር ይሄው እውቀቱን የሰጠኝ አምላክ ነው እሱ የሰጠኝን ለሱ" ብላ ሙሉውን ሰጠች።

እንዴት መባረክ መመረጥ ነው?!
የዘመኑ ሰው እንኳን ያለውን ካለው ላይ ማካፈል በማይፈልግበት በዚህ ዘመን ልበ ብርሀኑዋ ሎዛ ሙሉ የሽልማት ገንዘቧን ለግሳለች።
10,000.00$ ዶላር አሜሪካ ላይ ትልቅ ገንዘብ ነው ።ይህ ለኛ ንፉጎቹ ትልቅ ትምህርት ነው

እባካችሁ ሎዛን መርቁልኝ ከዚህ በላይ እውቀቱን ያድልሽ በሉልኝ ተባረኪ እህታችን!!

(ዘሐበሻ)

@GorgoraMedia
655 viewsedited  18:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 20:26:26 #Amhara #ወርቄ

በወርቄ ሰዱ ግንባር ብቻ ዛሬ ሙሉ ቀን በተደረገ እልክ አስጨራሽ ትግል የወርቄ ወጣቶች ህወሓት አድርሶት ማንሳት የቻለው ብቻ ከ3 መኪና በላይ የጠለት ኃይል ጥለዋል። ይህ አስደናቂ ጀብድ የተሰራው ዲሽቃና ስናይፐር በታጠቀ የሰለጠነ ወታደር ሳይሆን አሮጌ የነፍስ ወከፍ መሳሪያ በያዙ ግን ደግሞ በአይበገሬው ወኔያቸውና አልሞ ተኳሽነታቸው ወደር በማይገኝላቸው የወሎ ልጆች ነው። ወርቄዎች እስካሁን በሰው ላይ የደረሰባቸውን ጉዳት በዝርዝር ማወቅ ባንችልም በትንሽ መስዋዕትነት የፈጸሙት ጀብድ ስለመሆኑ ማረጋገጥ ችያለሁ።
857 views17:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 18:46:12 አንድ ነገር ልለምናችሁ!

( ዘሪሁን ገሠሠ )

ምንም ዝርዝር ሳያስፈልገው ፥ ለአማራ ህዝብ ብሎም ለወንድሞቻችን የምታስቡ ከሆነ ፋኖን በተናጠልም ሆነ በቡድን አብሮት እየተዋደቀ ካለው የሀገር መከላከያ ሰራዊትና ልዩ ሀይል ነጥላችሁ ከማወደስና ሌላውን ከማንኳሰስ ትታቀቡ ዘንድ በተማፅኖ ጭምር ላሳስባችሁ እወዳለሁ!

ሌላው…!

በተረጋገጠ መረጃ ወያኔ በሰው ማዕበል በራያ ግንባር ያለውን ሜካናይዝድ ጦር ለመማረክና በወልቃይት በኩል የተቀናጀ ጥቃት ለመጀመር ያቀደችው እቅድ በጀግኖቹ የኢትዮጵያ ልጆች መስዋትነት እንዳሰበችው ሊሳካ አልቻለም!

እንደተለመደው ሠውን እንደጥይት ማብረጃ እየተጠቀሙ የመጡበት መንገድ በጎብዬ ፣ በቃሊምና በመሳሰሉት በሁሉም የግንባሩ አቅጣጫዎች በደም ዋበላ እንዲታጠቡ አድርጓቸዋል፡፡ ከፍተኛ ዋጋን ከፍለውበታል!

ይህ ማለት አንድ ሙከራ ሞክረው ሲከሽፍ ሌላኛውን አይቀጥሉም ማለት ባለመሆኑ ፥ ሁሉም ለህዝባዊ ሀይሉ ደጀን በመሆን ፥ በግንባር ካለው ሀይል ጋር በመሠለፍና በፐርሶኔልም ሆነ በሎጂስቲክስ ረገድ እጅግ ትልቅ አቅም በመፍጠር ወያኔ በወልቃይት በኩል ያቀደውን እቅድ ራያ መሬት ላይ ከአፈር መቀላቀል ይገባል!
1.0K views15:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ