Get Mystery Box with random crypto!

Gorgora Media

የቴሌግራም ቻናል አርማ gorgoramedia — Gorgora Media G
የቴሌግራም ቻናል አርማ gorgoramedia — Gorgora Media
የሰርጥ አድራሻ: @gorgoramedia
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 5.23K
የሰርጥ መግለጫ

@GorgoraMedia

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-08-30 17:50:37
833 views14:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 17:50:37 #Amhara #Worke

በባለ ሽርጣሞቹ በሀሰን ከረሙ በሚመራው የምሥራቅ አማራ ፋኖ #ወርቄ ላይ የተማረኩ  የወያኔ ሰላቢ ታጣቂ ባንዳዎች ናቸው።
ዞር አድርጋችሁ ቦታ ቦታ ስጧቸው የምን ማሽኮርመም ነው።

@Fanotv24
801 views14:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 17:41:08 #Update  #Kombolcha

ሰርጎ ገብን እንጠብቅ ትናንት የመከላከያ ሬንጀር የለበሱ የወያኔ ሰላዮች በክምር ድንጋይ ዛሬ ደግሞ  ኮምቦልቻ ከተማ ከተፈናቃይ ጋር የገቡ 3 የወያኔ ተላላኪዎች ተይዘዋል።

@Fanotv24
1.1K views14:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 16:26:56
1.2K views13:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 16:26:52 ኤፍሬም ከስፍራው ሆኖ ይናገራል

እዚህ እየመጣህ አታላዝንብኝ እኔ ይህን ፀጉሬ ተንጨባሮ ከንፈሬ ደርቆ ኦነግ ሸኔ መስዬ የተነሳሁትን ፎቶ የመልቀቅ አባዜ ኖሮብኝ ሳይሆን፤ ሽብሩ ቢበዛ ወሬው ቢናፈስ ደሴን አልፎ ኮምቦልቻ ሱቅ እየተዘጋ፣ ባንክ በወረፋ ተጨናንቆ ለመቶ ሃያ ኪ.ሜ ከወልዲያ ደሴ በግድያ፣ በድብድብ፣ በባጃጂ ጭምር ለአንድ ሰው ሶስት ሽህና አራት ሽህ ብር እየተከፈለ፤ ህዝብ እየተንገላታ ባለበት ሰዓት አካባቢው ሰላም መሆኑን በመግለጽ ህዝብን ለማረጋጋት እንጂ ድሉንማ አፍኘ ይዥዋለሁ።

ለማንኛውም ባንዳው ይህኛው ያልተዋጠልህ ትልቁን ድል ልቦናህ ስለሚያውቀው ነው፤ ሌሎቻችሁ ማወቅ ካለባችሁ ድሉን በደንብ ለማብሰር ይቆየኝ የህወሓት ወራሪ ቡድን ግን እመኑኝ በየትኛውም መንገድ ወልዲያን ድጋሚ ሊረግጥ አይችልም።

"የመነን ዘር አይሸጥ አይመነዘር!"
ዳጊ ነኝ ከአለውሃ ወንዝ ማዶ!
1.1K views13:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 15:42:40
1.1K views12:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 15:42:36 የሰቆጣ ከተማ አሥተዳደር የፀጥታ ምክር ቤት በወቅታዊ የፀጥታ  ሁኔታ በማስመልከት የሚከተሉትን ውሳኔዎች አስተላልፏል።
ጥምር ጦራችን በሁሉም ግንባር በሙሉ ብቃትና ወኔ ጠላትን እየመከተ ይገኛል ፤ የሰቆጣ ከተማ አሥተዳደር የፀጥታ ምክር ቤት ማህበረሰባችን በተለያዩ ሁኔታዎች ስጋት ውስጥ እንዳይገባና የከተማችንን ሰላምና ደህንነት ለመጠበቅ ሲባል የሚከተሉት ውሳኔዎች አስተላልፏል ፡፡
1.  ማንኛውም እግረኛ ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ንጋቱ 12፡00 ሰዓት ድረስ መንቀሳቀስ በጥብቅ የተከለከለ ነው ።
2.  ለጸጥታ ስራ ስምሪት ከተሰጣቸው ተሸከርካሪዎች ውጭ ማንኛውም ተሸከርካሪ ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ንጋቱ 12፡00 ሰዓት ድረስ መንቀሳቀስ በጥብቅ የተከለከለ  ነው።
3.  ከጸጥታ መዋቅሩ ውጭ በየትኛውም ሰዓትና ቦታ የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ በጥብቅ የተከለከለ ነው፡፡
4.  ማህበረሰቡን የሚያውኩ የሃሰት አሉባልታዎች ወይም የሃሰት መረጃዎችን ማሰራጨት በጥብቅ የተከለከለ ነው።
5.  በከተማችን የሚገኙ ተፈናቃዮች ከተሰጣቸው የመጠለያ ካምፕ ውጭ መንቀሳቀስ በጥብቅ የተከለከለ ነው።
6.  ለሕዝብ አገልግሎት የሚሰጡ ማለትም ባንክ ቤቶች፣ ሱቆች፣ ሆቴል እና መስል የመንግስትና የግል ድርጅቶችን መዝጋት በጥብቅ የተከለከለ ነው።
7.  በከተማችን የሚገኙ የመንግስትና የግል ታጣቂዎች መንግስት በሚያሰማራው የፀጥታ ስራ ላይ ተሳታፊ የመሆን ግዴታ አለባቸው።
8.  ማንኛውም ማህበራዊ ሚዲያ  ተጠቃሚ ግለሰብ ሆነ ድርጅት የትኛውንም  ሚዲያ ተጠቅሞ የሃሰት መረጃዎችን ማሰራጨት፣ በተለይ ስለጦርነቱ አሉቧል  መዘገብ ሆነ መግለጫ መስጠት በጥብቅ የተከለከለ ነው።
9.  ማንኛውም የቤት አከራይ ወይም አልጋ ቤቶች ተከራዮቻቸውንና ተጠቃሚዎቻቸውን የመለየትና ማንነታቸውን የሚለይ ህጋዊ መታወቂያ ስለመኖራቸው የማረጋገጥ ግደታ አለባቸው ፡፡ አጠራጣሪ ሁኔታዎች ከተፈጠሩ ለፀጥታ መዋቅሩ ጥቆማ የመስጠት ሃላፊነት አለባቸው።
10.  ማንኛውም የከተማችን ማህበረሰብ ከፀጥታ መዋቅሩ ጋር የመቀናጀትና የመተባበር  ግዴታ አለበት ።
ከላይ የተጠቀሱት ነጥቦች በማያከበር ማንኛውም አካል የፀጥታ መዋቅራችን አስፈላጊውን  እርምጃ የሚወስድ  መሆኑን በአጽንኦት  ያሳውቃል።
የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ምክር ቤት
ነሀሴ 24/2014 ዓ/ም
        ሰቆጣ
1.1K views12:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 15:38:33
998 views12:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 15:38:29 ከደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ምክር-ቤት የተላለፈ ወቅታዊ መልዕክት!

የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ምክር ቤት ወቅታዊ የፀጥታ ስጋትን አስመልክቶ የሚከተሉትን ውሳኔዎች አስተላልፏል።

1ኛ. በከተማ አስተዳደሩ በተፈናቃይ መጠለያ ጣቢያ ውስጥ የሚኖር ተፈናቃይ ከምሽቱ 12:00 በኋላ ወደ መጠለያ ጣቢያውም  ሆነ ወደ ከተማው መግባት ክልክል ነው።

2ኛ. በከተማው የሚገኙ የባጃጅ ተሽከርካሪዎች  ከምሽቱ 2፡00 በኋላ መንቀሳቀስ አይችልም  ክልክል ነው ይህን ሲያደርግ የተገኘ ባለባጃጅ ህጋዊ እርምጃ ይወሰድበታል።

3ኛ. በከተማው የሚገኙ መጠጥ ቤቶች ምግብ ቤቶች ምሽት ጭፈራ ቤት እስከ ምሸት 2:00 ሰአት ብቻ አገልግሎት እንዲሰጡ ወስኗል።

4ኛ.  በከተማው በሚገኙ የንግድ ቤቶች የምርት የዋጋ ጭማሪ ማድረግ በጥብቅ የተከለከለ ነው።

5ኛ. ከተፈቀደላቸው የፀጥታ ሀይሎች ውጭ የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ ፈፅሞ የተከለከለ ነው

6ኛ. ከመንግስት ዕውቅና ውጭ የሚደረጉ ማናቸውም አይነት ውይይቶችና ስብሰባ ማድረግ በጥብቅ የተከለከለ ነው፡፡

7ኛ. የጠላትን ሀሳብና እንቅስቃሴ በመደገፍ አሉባልታና ወሬን ማሰራጨት በህብረተሰቡ ላይ ሽብር መንዛት በጥብቅ የተከለከለ ነው።

8ኛ. አዳር የሚሰሩ በከተማችን ያሉ ፍብሪካዎችና ድርጂቶች ድርጁቱ በሚሰጣቸው ህጋዊ  መረጃ ና በፀጥታ መዋቅሩ የተረጋገጠ የይለፍ ከያዘ ብቻ መንቀሳቀስ ይችላል፡፡

9ኛ. መላው የከተማው  ማህበረሰብ በአደረጃጀት አካባቢውን ቀንና ሌሊት ከሰርጎ ገቦች በንቃት መጠበቅ አለበት።

10ኛ. በከተማ አስተዳደሩ ፀጉረ ልውጥ ሲያጋጥም በፍጥንት ለህግ አካል ጥቆማ በመስጠት በህግ ቁጥጥር ስር እንዲውል  ማድረግ ከማህበረሰቡ ይጠበቃል።

11ኛ. የከተማው ባለሆቴሎች እና አልጋ አከራዮች ማንነቱ ያልታወቀ የታጠቀ ግለሰብ በድርጅታችሁ ሲያጋጥማችሁ ለህግ አካላት ጥቆማ እንድትሰጡ።

12ኛ. በከተማ አስተዳደሩ ያላችሁ የቤት አከራይዎች የምታከራዩትን ግለሰብ ማንነትት መታወቂያ በመጠየቅ ለይታችሁ እንድታከራዩ የተከራዩንም መረጃ በፎርም በመሙላት  ለከተማው ሰላምና ፀጥታ መምሪያ እንድታሳውቁ መልዕክት አስተላልፏል።

ይህ የውሳኔ ሀሳብ ከዛሬ ጀምሮ  ተግባራዊ  የሚደረግ ሲሆን ከላይ በዝርዝር የተቀመጡትን የውሳኔ ሀሳቦች የሚጥስ ማንኛውም አካል ህጋዊ እርምጃ እንደሚወስድበትም የከተማ አስተዳደሩ  አስታውቋል።

የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር

@GorgoraMedia
992 views12:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 15:34:02
979 views12:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ