Get Mystery Box with random crypto!

Ethiopia 24

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiopia_24 — Ethiopia 24 E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiopia_24 — Ethiopia 24
የሰርጥ አድራሻ: @ethiopia_24
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.87K
የሰርጥ መግለጫ

2015/ 2023 አስተያየት መስጫ @Ethnewbot

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 13

2022-09-18 13:24:58
#ETHIOPIA  በነገው ዕለት የ2015 የትምህርት ዘመን ይጀምራል።

በዚሁ ዕለት ትምህርት ሚኒስቴር 5 ዓመታት ሲያዘጋጅ የቆየው አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት በመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መተግበር ይጀምራል፡፡

በሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ ወደ ሙሉ ትግበራ የሚገባው የአዲሱ የትምህርት ስርዓት ከነገ ጀምሮ በኢትዮጵያ በሚገኙ 80 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ በሙከራ ደረጃ ይሰጣል።

SUBSCRIBE ON YOUTUBE
https://www.youtube.com/c/Ethiopia24
https://www.youtube.com/c/Ethiopia24

አስተያየት ለመስጠት @Ethnewbot

➹share &Join Us
                  
@ethiopia_24     @ethiopia_24
@ethiopia_24     @ethiopia_24
7.6K viewsedited  10:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-17 13:53:56 አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ይዟቸው የመጡ አዳዲስ ነገሮች ምን ምን ናቸው ?

አምስት ዓመታትን በፈጀውና ከ3 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ የማህበረሰብ ክፍሎች የተሳተፉበት ስርዓተ ትምህርት ክለሳ የያዛቸው አዳዲስ ነገሮች ፦

ስርዓተ ትምህርቱ በሁሉም የአገሪቱ ክፍል ባሉ የግል እና  የመንግስት ትምህርት ቤቶች የሚተገበር ቢሆንም፤ ኢንተርናሽናልና የማህበረሰብ አቀፍ ትምህርትቤቶችን አያካትትም፤

በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ግብረ ገብ፣ አገር በቀል ዕውቀት፣ ሙያና የቀለም ትምህርት፣ ቴክኖሎጂ፣ ምርትና ተግባር፣ ጥናትና ምርምር ትኩረት ተደርጎባቸው እንዲሰጡ ይሆናሉ፤

ከአንደኛ እስከ ስድስተኛ ክፍል ላሉ የክፍል ደረጃዎች ትምህርት በአፍ መፍቻ ቋንቋ  ይሰጣል፤

ከሰባተኛ ክፍል እስከ12ኛ ክፍል ያሉት ደግሞ ሁሉም ተማሪ በእንግሊዘኛ ቋንቋ ይማራል፤

ከአንደኛ ክፍል ጀምሮ እስከ12ኛ ክፍል ድረስ ያሉት ተማሪዎች የእንግሊዘኛ ቋንቋን እንደ አንድ የትምህርት ዓይነት ይወስዳሉ፤

ሦስተኛ ክፍል ላይ ተጨማሪ ቋንቋዎችን መስጠት ይጀመራል፤  በክልሎቹ ውስጥ በስፋት የሚነገረውን ተጨማሪ ቋንቋ በመምረጥ ተማሪዎቹ እንደ አንድ የትምህርት አይነት እንዲወስዱት ይደረጋል፤ 

በቀድመው የትምህርት ሥርዓት 10ኛ ክፍል ይሰጥ የነበረው አገራዊ የመልቀቂያ ፈተና ይቀርና በምትኩ አጠቃላይ ፈተናው በክልል ደረጃ ስድስተኛ ክፍል እንዲሁም በአገር አቀፍ ደረጃ ስምንተኛ እና 12ኛ ክፍል ላይ ይሰጣል፤

ከዚህ ቀደም ሦስት ዓመት የነበረው የተማሪዎች የዩኒሸርስቲ ቆይታ ደግሞ ዝቅተኛዉ አራት ዓመት ይደረጋል፤
ለሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋም ተማሪዎች በመጀመሪያ ዓመት ከሚሠጡ ትምህርቶች ውስጥ እንደ ጂኦግራፊ፣ አንትሮፖሎጂ፣ ሶሺዮሎጂና ሥነ-ምግባር የመሳሰሉት ይካተታሉ፤

ከአንደኛ እስከ ስድስተኛ ክፍል የግብረገብ ትምህርት ይሰጣል፤  በተጨማሪም የማህበራዊና የተፈጥሮ ሳይንስ ውህድ የሆነ ትምህርት ይሰጣል፤ 

ሰባተኛና ስምንተኛ ክፍል በተናጠል ይሰጡ የነበሩት ፊዚክስ፣ ኬሚስትሪና ባይሎጂ  አጠቃላይ ትምህርት ወይም ጀነራል ሳይንስ ተብለው እንዲሁም ጆግራፊና ሂስትሪም ተቀናጅተው የሚሰጡ ይሆናል፤

የሰባተኛና ስምንተኛ ክፍል ተማሪዎች የእርሻ ትምህርት፣ አካውንቲንግ፣ ቢዝነስና ጀነራል የሆነውን የሥራና ክህሎት ትምህርት በሙያ ትምህርት ተካቶላቸው የሚሰጣቸው ይሆናል፤

11ኛ እና 12ኛ ክፍሎች ላይ ደግሞ ጤና ፣ ግብርና፣ የእርሻ ትምህርት፣ ማኒፋክቸሪንግ፣ ኮንስትራክሽን፣ ቢዝነስ፣ አካውንቲንግ የመሳሰሉት የሙያ ትምህርትነቶችን እንዲማሩ ይደረጋል፤

የዘጠነኛና የአስረኛ ክፍልን እንዲሁም  ከአንድ እስከስምንተኛ ክፍል ያሉ የተመረጡ አምስት የትምህርት አይነቶችን መጸሐፍት ዝግጅት ትምህርት ሚኒስቴር ያከናውነዋል፤  

ከአንደኛ እስከ ስምንተኛ ክፍል ያለውን የትምህርት መፀሐፍት ክልሎች በራሳቸው ባህልና አካባቢያዊ ሁኔታ ቃኝተው ያዘጋጁታል፤ ( የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት )

SUBSCRIBE ON YOUTUBE
https://www.youtube.com/c/Ethiopia24
https://www.youtube.com/c/Ethiopia24

አስተያየት ለመስጠት @Ethnewbot

➹share &Join Us
                  
@ethiopia_24     @ethiopia_24
@ethiopia_24     @ethiopia_24
8.3K views10:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-16 19:24:47 #አስቸኳይ_መልዕክት  በአማራ ክልል በቅርቡ ለሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች የተላለፈ አስቸኳይ መልዕክት፡፡

የ2014/2015 ዓ.ም በአማራ ክልል የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች ከመስከረም 30/2015 ዓ.ም ጀምሮ በክልሉ ባሉ ዩኒቨርስቲዎች ፈተናው እንደሚሰጥ መገለፁ ይታወሳል፡፡

በመሆኑም ተፈታኝ ተማሪዎች ቀድመው ሊዘጋጁባቸው  የሚገቡ ዋና ዋና ነጥቦች እንደሚከተለው ይቀርባሉ፡፡

1. ሁሉም ተፈታኝ ተማሪዎች በፈተና ማዕከልም ይሁን በመፈተኛ ክፍል አድሚሽን ካርድ ይዞ መገኘት ግዴታ በመሆኑ አድሚሽን ካርድ ፎርም ከሞሉበት  ትምህርት ቤት እና ወረዳ በአካል በመገኘት እስከ መስከረም 10/2015 ዓ.ም እንዲረከቡ፡፡

2. በአድሚሽን ካርዱ ላይ የስም፣ የስትሪም እና የጾታ ወዘተ..ስህተት ካለ በአስቸኳይ ለትምህርት ቤቱ እና ለወረዳው ሪፖርት እንድታደርጉ በጥብቅ እያሳሰብን ይህንን የማያደርጉ ተማሪዎች ካሉ ፈተና ለመውሰድ እንደሚቸገሩ፤

3. ሁሉም ተፈታኝ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ ሲመጡ የትምህርት ቤት ወይም የኗሪነት መታወቂያ ይዞ መገኘት የሚገባ መሆኑ፤

4. ሁሉም ተፈታኝ ተማሪዎች በፈተና ጊዜ እርሳስ፣ ላጲስና የእርሳስ መቅረጫ  ይዘው መገኘት ያለባቸው መሆኑ ከዚህ ዉጭ ሌሎች ቁሳቁሶችን በዩኒቨርሲቲ ግቢ እና በመፈተኛ ክፍል መያዝ የተከለከለ መሆኑ፤

5. ሁሉም ተፈታኝ ተማሪዎች ትምህርት ቤቱ፣ ወረዳው እና ዞኑ በሚያዘጋጀው የጉዞ ፕሮግራም መሰረት ወደ መፈተኛ ዩኒቨርሲቲ የሚጓዙ መሆኑን በመረዳት ዝግጅት ማድረግ ያለባቸው መሆኑን፤

6. ሁሉም ተፈታኝ ተማሪዎች ወደ ተመደበበት ዩኒቨርሲቲ ሲሄድ አንሶላ፣ ብርድልብስና የትራስ ልብስ ይዞ የመምጣት ይኖርባቸዋል፡፡

ይህን መረጃ ሸር በማድረግ ለተማሪዎችና ተማሪ ወላጆች እንዲሁም የሚመለከታቸው አካላት እንዲደርስ ትብብራችሁን እንድታደርጉ በተፈታኝ ተማሪዎች ስም ቢሮው ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡

(የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ )

SUBSCRIBE ON YOUTUBE
https://www.youtube.com/c/Ethiopia24
https://www.youtube.com/c/Ethiopia24

አስተያየት ለመስጠት @Ethnewbot

➹share &Join Us
                  
@ethiopia_24     @ethiopia_24
@ethiopia_24     @ethiopia_24
8.1K views16:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-16 17:43:22
ለሁሉም #የባሕር_ዳር_ዩኒቨርሲቲ መደበኛና የማታ ተማሪዎች በሙሉ

ከመስከረም 28 ቀን 2015 ዓ/ም እስከ ጥቅምት 17 ቀን 2015 ዓ/ም ድረስ በሚሰጠው #የ12ኛ ክፍል ፈተና ምክንያት ከላይ በተጠቀሱት ቀናት በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ምንም ዓይነት የመማር ማስተማር እንቅስቃሴ የማይኖር መሆኑን አውቃችሁ በዩኒቨርሲቲው ካላንደር መሰረት የመማር ማስተማር ሂደቱ ከጥቅምት 21 ቀን 2015 ዓ/ም ጀምሮ የሚቀጥል መሆኑን እየገለጽን የ1ኛ ዓመት ተማሪዎች የአጋማሽ ፈተና ሲጠናቀቅ ከመስከረም 26 - 27 ባለው ጊዜ ውስጥ ከግቢ ለቃቹህ የምትወጡ መሆኑን ከወዲሁ ማሳወቅ እንወዳለን፡፡ ( ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ )

SUBSCRIBE ON YOUTUBE
https://www.youtube.com/c/Ethiopia24
https://www.youtube.com/c/Ethiopia24

አስተያየት ለመስጠት @Ethnewbot

➹share &Join Us
                  
@ethiopia_24     @ethiopia_24
@ethiopia_24     @ethiopia_24
7.0K views14:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-16 13:42:42 በ2014/2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ለምትወስዱ ተማሪዎች ከዚቀደም (2004 - 2011) የወጡ እንግሊዝኛ ጥያቄዎች

English EUEE QUESTIONS

Comparison


8.0K views10:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-15 19:55:15 በ2015 በአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት (ከ1ኛ እስከ 8ኛ ክፍል) አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ እንደሚሆን ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።

በተመሳሳይ፣ የ9ኛ እና 10ኛ ክፍል አዲሱ ሥርዓተ-ትምህርት ከኹሉም ክልሎች እና ከተማ መስተዳድሮች በተመረጡ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ የሙከራ ትግበራ ይጀመራል ሲሉ የሚኒስቴሩ የህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ሥራ አስፈጻሚ አመለወርቅ ህዝቅኤል ተናግረዋል።

ለዚህም ይረዳ ዘንድ የሙከራ ትግበራ ከሚካሄድባቸው ትምህርት ቤቶች ለተውጣጡ መምህራን ሥርዓተ ትምህርቱን የማስተዋወቅ የአሰልጣኞች ሥልጠና መሰጠቱን ሥራ አስፈጻሚዋ ገልጸዋል።በአገር አቀፍ ደረጃ ሰኞ መስከረም 9 ቀን 2015 ለሚጀመረው ትምህርት የተለያዩ ዝግጅቶች ማድረጉን ሚኒስቴሩ አስታውቋል።ሰኞ ዕለት በይፋ ለሚጀመረው ትምህርት በአብዛኞቹ ትምህርት ቤቶች የመክፈቻ ሥነ ስርዓት እንደሚያካሄድም አመለወርቅ ገልጸዋል።

ተማሪዎች ደስ ብሏቸው የትምህርት ቀኑን እንዲጀምሩ የተለያዩ ዝግጅቶች በየትምህርት ቤቶቹ እንደሚካሄዱ የገለጹት ኃላፊዋ፣ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት እንዲመጡ በክልል ያሉ ትምህርት ቢሮዎች፣ ትምህርት ቤቶች እና የተለያዩ ድርጅቶች በትምህርት ቤት ውስጥ መዝናኛ ዝግጅት አዘጋጅተው ተማሪዎችን የመቀበል ሥነ ስርዓት ያካሄዳሉ ብለዋል።

የክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች፣ መምህራንን እና ማህበረሰቡ በትምህርቱ የጊዜ ሰሌዳ እና በሥርዓተ ትምህርቱ አፈጻጸም ላይ ውይይቶችን እንዳደረጉ ወ/ሮ አመለወርቅ መጠቆማቸውን ኢቢሲ ዘግቧል።ትምህርት ቤቶች የመማር ማስተማር ሥራ ከመጀመራቸው በፊት የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ሲከናወኑ መቆየቱን ያወሱት የኮሚዩኒኬሽን ኃላፊዋ፣ በዚህም የትምህርት ቤቶች እድሳት፣ የአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት የመጽሐፍት ማስተዋወቅ እና የትምህርት ጉባዔ የማካሄድ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን አስረድተዋል። (EBC)

SUBSCRIBE ON YOUTUBE
https://www.youtube.com/c/Ethiopia24
https://www.youtube.com/c/Ethiopia24

አስተያየት ለመስጠት @Ethnewbot

➹share &Join Us
                  
@ethiopia_24     @ethiopia_24
@ethiopia_24     @ethiopia_24
7.7K views16:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-14 16:38:10 በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ለምትወስዱ ተማሪዎች ከዚቀደም (2004 - 2011) የወጡ እንግሊዝኛ ጥያቄዎች

English EUEE QUESTIONS

CONDITIONAL SENTENCES



10.1K views13:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-14 11:35:37
የ12ኛ ክፍል ፈተናን በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ መስጠቱ  ፋይዳው ምንድነው ?

በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በዩኒቨርሲቲዎች መሰጠቱ በርካታ ጠቀሜታዎች እንደሚኖሩት  የፈተናዎች አገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር እሸቱ ከበደ ገልፀዋል፡፡

ዶ/ር እሸቱ ከበደ ፦

- የፈተና ስርቆትና ኩረጃ  ላይ ከፍተኛ ቁጥጥር በማድረግ ተማሪዎች የራሳቸውን ብቻ እንዲሰሩ አስተዋጽኦ ይኖረዋል።

- ፈተናውን በማጓጓዝ ወቅት የሚያጋጥሙ ችግሮችንም ለመፍታት ትልቅ እገዛ ይኖረዋል።

- የፈተናውን ሂደት ለማበላሸት ጥረት ከሚያደርጉ ሰዎች ለመጠበቅ ከፍተኛ ጠቀሜታ ይኖረዋል።

- ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ መፈተናቸው ቀድመው ዩኒቨርሲቲዎቹን በአካል እንዲያውቋቸው ያደርጋል ብለዋል።

ለፈተናው ተማሪዎች ተገቢውን ዝግጅት እንዲያደርጉና ወላጆችም አስፈላጊውን ድጋፍ ለልጆቻቸው እንዲያደርጉ ዋና ዳይሬክተሩ ጠይቀዋል።

የ2014ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በሁለት ዙር በዩኒቨርሲቲዎች ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ እንዳለ ይታወቃል፡፡ (ትምህርት ሚኒስቴር)

SUBSCRIBE ON YOUTUBE
https://www.youtube.com/c/Ethiopia24
https://www.youtube.com/c/Ethiopia24

አስተያየት ለመስጠት @Ethnewbot

➹share &Join Us
                  
@ethiopia_24     @ethiopia_24
@ethiopia_24     @ethiopia_24
8.1K views08:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-11 12:44:19 የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች የመጓጓዣና ሌሎች ወጪዎችን በመንግሥት እንደሚሸፈን ተገለጿል

ከመስከረም 2015 ዓ.ም. መጨረሻ አንስቶ በሁለት ዙር የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚወስዱ አንድ ሚሊዮን ገደማ ተፈታኝ ተማሪዎች፣ ወደ ዩኒቨርሲቲዎች የሚጓጓዙበትን የትራንስፖርትና ሌሎች ወጪዎች በመንግሥት እንደሚሸፈኑ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አስታወቀ፡፡

ዩኒቨርሲቲዎች ለተፈታኝ ተማሪዎች የሚያስፈልጉ የምገባና መኝታ አገልግሎቶችን ለመስጠት ቁሳቁሶችን እያሟሉ መሆኑን አስታውቆ፣ ፈተናውን በዩኒቨርሲቲዎች ለማከናወን የሚያስችለውን ወጪ ለመሸፈን ተጨማሪ በጀት እንዲፈቀድለት ንግግር ላይ መሆኑን ገልጿል፡፡

የ12ኛ ክፍል ፈተናን በተመለከተ ከዚህ ቀደም ከነበረው ልምድ የተለየ አሠራር ለመዘርጋት ያቀደው ትምህርት ሚኒስቴር፣ ፈተናው በትምህርት ቤቶች ሳይሆን በዩኒቨርስቲዎች እንደሚሰጥ አስታውቋል፡፡ ለዚህም ሲባል ተፈታኝ ተማሪዎችን በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ መመደቡን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ምክትል ኃላፊ አቶ ይልቃል ወንድሜነህ ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡

ምደባው ሲዘጋጅ በተቻለ መጠን ተማሪዎች በአቅራቢያቸው በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ እንዲመደቡ መደረጉን ያስረዱት አቶ ይልቃል፣ ‹‹በአቅራቢያቸው ያለው ዩኒቨርሲቲ በመኝታ ወይም በመፈተኛ ክፍሎች ብዛት ውስንነት ካለበት ወደ ሌላ ዞንና ክልል የመሄድ ዕድል ይኖራል፤›› ብለዋል፡፡

በተለይ ገጠር አካባቢዎች ላይ ያሉ ተማሪዎች ወደ ተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ ለመጓዝ አስቸጋሪ ሁኔታ ሊገጥማቸው እንደሚችል ጠቅሰው፣ አገልግሎቱ ከክልል ትምህርት ቢሮዎች ጋር በመሆን ተማሪዎቹን ወደ ዩኒቨርሲቲ እንደሚያጓጉዝ አስረድተዋል፡፡

‹ተማሪዎቹን እንዴት እናጓጉዛቸው?› የሚለው ላይ ውይይት እያደረግን ነው፡፡ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲዎች በመፈተናቸው ምክንያት ግን ወደ ተማሪዎችም ሆነ ወደ ወላጆች የሚሄድ ወጪ አይኖርም፤›› ብለዋል፡፡

ምክትል ኃላፊው፣ ተማሪዎቹ የተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ አካባቢ እንዲላመዱት ለማድረግ ሲባል ፈተናው ከሚጀመርበት ቀናት ቀደም ብለው ወደ ዩኒቨርሲቲው እንደሚጓዙ አስታውቀዋል፡፡ ወደ ዩኒቨርስቲ ሲገቡ ድምፅም ሆነ ምሥል የሚቀዳና የሚቀርፅ አሊያም ሌላ የኤሌክትሮኒክስ መሣሪያ ይዘው መግባት እንደማይችሉ ተናግረዋል፡፡ የሚኖሩበት ከተማ ውስጥ በሚገኝ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡ ተፈታኞችም ቢሆኑ በዩኒቨርስቲው ውስጥ እንዲያድሩ ለማድረግ መታቀዱንም ገልጸዋል፡፡ (ሪፖርተር)

SUBSCRIBE ON YOUTUBE
https://www.youtube.com/c/Ethiopia24
https://www.youtube.com/c/Ethiopia24

አስተያየት ለመስጠት @Ethnewbot

➹share &Join Us
                  
@ethiopia_24     @ethiopia_24
@ethiopia_24     @ethiopia_24
397 views09:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-11 12:44:15
383 views09:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ