Get Mystery Box with random crypto!

ETHIO-MEREJA®

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethio_mereja — ETHIO-MEREJA®
ርዕሶች ከሰርጥ:
Ethiopia
የሰርጥ አድራሻ: @ethio_mereja
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 131.05K
የሰርጥ መግለጫ

Addisababa, Ethiopia🇪🇹
News & Media Company®
.
USA : Washington
.
.
.
ለጥቆማ እና ማስታወቂያ ለማሰራት
ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ!!
👉 @ethio_merejabot ✔

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 292

2022-05-20 17:02:17 የዋጋ ንረትን ለመቆጣጠር ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ አስታወቁ !!

የገንዘብ ሚኒስቴር ከልማት አጋር ሀገሮች አምባሳደሮችና የልማት ድርጅቶች የስራ ኃላፊዎች ጋር በሀገሪቱ የዘጠኝ ወር የማክሮ ኢኮኖሚ አፈፃፀም ላይ ዛሬ ውይይት አድርጓል።

ለውይይቱ መነሻ የዘጠኝ ወር የማክሮ ኢኮኖሚውን አፈፃፀም ሪፖርት የፕላንና ልማት ሚንስትሯ ዶ/ር ፍፁም አሰፋ ሲያቀርቡ እንዳሉት፣ ባላፉት ዘጠኝ ወራት ኢኮኖሚው በየዘርፉ ዕድገት በማስመዝገብ ላይ መሆኑን ጠቅሰው በተለይ በውጭ ቀጥተኛ የመዋዕለ ንዋይ ፍሰት፣ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውን ወደ ሀገር ውስጥ በሚልኩት ዶላር ረገድ ጥሩ ዕድገት አለ ብለዋል።

በአጠቃላይ በ9 ወር ውስጥ ኢኮኖሚው 6 ነጥብ 6 በመቶ አድጓል ያሉት ዶ/ር ፍፁም፤ በዚህ ጊዜ ውስጥ ለ 1 ነጥብ 4 ሚለዮን ዜጎች የስራ ዕድል እንደተፈጠረ፣ የመንግስት ገቢ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ7 ነጥብ 7 በመቶ ዕድገት እንደሳየ፤ እንዲሁም ባንኮች 1 ነጥብ 6 ትሪሊየን ብር ቁጠባ መሰብሰብ እንደቻሉ፣ በአጠቃላይ ከተሰራጨው ብድር ውስጥም 70 በመቶው ለግሉ ዘርፍ አገልግሎት ላይ እንደዋለ ተናግረዋል።

ውይይቱን የመሩት የገንዘብ ሚንስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ እንዳሉት፣ ኢኮኖሚው በወጪ ንግድ፣ በውጭ ቀጥተኛ መዋዕለ ንዋይ ፍሰትና በሌሎችም መመዘኛዎች ጥሩ ደረጃ ላይ እንዳለ ተናግረው ነገር ግን ኢኮኖሚው በሰሜን ኢትዮጵያ ግጭት፣ ድርቅ፣ ኮቪድ 19 እና በሩስያ ዩክሬን ግጭት ምክንያት እየተፈተነ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

መንግስት ኢኮኖሚው የገጠመውን ወቅታዊ ችግር ለመፍታት ቅድሚያ ትኩረት የሚሹ እንደ ድርቅ ፣ በጦርነቱ የደረሱ ጉዳቶችን ለማገገም፣ እንዲሁም መሰረታዊ የመገልገያ ሸቀጦችና መሰል ጉዳዮችን በመለየት እየሰራ እንደሚገኝም አስረድተዋል።

በቀጣይም መንግስት የሀገሪቱን ዜጎች በልማት ተጠቃሚ ለማድረግ የሚደርገው ጥረት ከልማት አጋሮች አላማ ጋር ተመሳሳይ በመሆኑ ግንኙነታችንን ይበልጥ በማጠናከር ልንሰራ ይገባል ሲሉ አቶ አህመድ ሽዴ መናገራቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮመረጃ
13.0K viewsedited  14:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 12:43:58
ዜና እረፍት

እውቁ ኮሜዲያን ወንድወሰን ብርሃኑ (ዶክሌ) በተወለደ በ57 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።

ዶክሌ በሚለው ቅጽል ስሙ የሚታወቀው ወንድወሰን ባጋጠመው የልብ ህመም ምክንያት በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ትናንት በአሜሪካ ዋሽንግተን ሜድስታር ሆስፒታል ውስጥ ማረፉን የሙያ አጋሩ አርቲስት ቴዎድሮስ ለገሰ ገልጿል።

“ዶክሌ ቅንና ታዛዥ ባለሙያ ነበረ” ያለው አርቲስት ቴዎድሮስ ኢትዮጵያውያን ኮሜዲያን ዶክሌን ሲረዳው ቢቆይም ለሁለተኛ ጊዜ ታሞ ሆስፒታል ገብቶ ህክምና እንዲያገኝ ቢደረግም ህይወቱን ማትረፍ እንዳልተቻለ መግለጹን ኢዜአ ዘግቧል።

በስታንድ አፕ ኮሜዲ እጅግ በርካታ አጫጭር ቁምነገር አዘል ቀልዶችን ያቀረበው ኮሜዲያን ዶክሌ በሙሉ ጊዜ የፊልም ሥራዎች ላይ በመሳተፍ ዕውቅናና ዝናን ያተረፈ ነበረ።

በሥራ አጋጣሚ ከስምንት አመታት በፊት ወደ አሜሪካ አቅንቶ ኑሮውን በዚያው አድርጎ የነበረው ኮሜዲያን ወንድወሰን ብርሃኑ (ዶክሌ) ባለትዳርና የአምስት ልጆች አባት ነበር።

ነብስ ይማር
T.me/ethio_mereja
ኢትዮመረጃ
16.8K viewsedited  09:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 12:36:45
ቴሌግራም https://telegram.me/onlineshoppingce
አድራሻችን:- ቦሌ መድሐኔዓለም ቦሌ መሰናዶ ት/ቤት ፊትለፊት አለምነሽ ፕላዛ ሱቅ ቁጥር 05

+251941661030
15.4K views09:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 12:28:06
አሁን ኢትዮጵያ ውስጥ ነን!

አቺባደም በግዝፈቱ በዓለም ሁለተኛው ደረጃ ላይ የሚገኘው የጤና ክብካቤ ቡድን አካል የሆነውን በአዲስ አበባ ጽ/ቤቱን ከፍቷል፡፡

በቦሌ መድሀኒአለም አካበቢ አንበሳ ባንክ ህንፃ አንደኛ ፎቅ በሚገኘው እንግዳ መቀበያችን እናስተናግድዎታለን:: ለህክምናዎ ወደ ቱርክ ለመጓዝ መረጃ ቢሮአችንን ይጎብኙ እና የነጻ የህክምና አስተያየት ያግኙ።

ለተከታታይ ጠቃሚ መረጃዎች የቴሌግራም ቻናላችንን
https://t.me/acibadem_ethiopia ይቀላቀሉ፡፡
14.9K views09:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 12:20:49
Double A፣ ከአጓጊ ሽልማቶች ጋር ተመልሷል

የ“Double A QR Ethiopia” የሞባይል መተግበርያን በስልክዎ  በመጫን በትክክለኛው የ Double A  ወረቀት ካርቶን ላይ የሚገኘውን የ  QR ኮድ የሞባይል መተግበሪያውን ተጠቅመው ስካን በማድረግ ፡-
 የተለያዩ ስጦታዎችን ለምሳሌ፦ የልብስ ማጠቢያ ማሽን፣የውሃ ማጣሪያ፣ ማይክሮዌቭ/የምግብ ማሞቂያ ማሽን፣ የጁስ መፍጫ እና የመሳሰሉትን ልዩ ልዩ ስጦታዎችን ይሸለሙ::

የ QR ነጥብ መሰብሰቢያ ፕሮግራማችንን አሁኑኑ ይቀላቀሉ! ደጋግመው QR ስካን ሲያርጉ ፤ ተጨማሪ ሽልማቶችን ያገኛሉ፡፡

መተግበርያውን ለማውረድ እባክዎን ከዚህ በታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ።

Link: https://bit.ly/3KGYCxC  Or

https://da-cloud.advanceagro.net/index.php/s/WYovIsmE4u2Kz6y

ለተጨማሪ መረጃ: https://DoubleArewards.com/Ethiopia
15.4K views09:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-18 23:31:37
#ጤናመረጃ

ብጉርን መከላከያ እና ማስለቀቂያ ዘዴዎች!

ብጉር የሚከሰተው በቆዳችን የሚመነጭ ቅባት ወይንም የሞቱ ሴሎች የጸጉር መውጫ ቀዳዳዎቻችን ሲደፍኑ ነው። በአብዛኛው በጉርምስና ጊዜ የሚመጣው ብጉር የሆርሞን መለወጥን ተከትሎ ነው።

ብጉርን የሚያስከትሉ ሁኔታዎች ምንድን ናቸው?

*የሆርሞኖች በሰውነታችን መለዋወጥ
*መድሃኒቶች በተለይም ሆርሞኖችን የያዙ ከሆኑ
*ቅባትነት ያላቸውን መዋቢያዎችን መጠቀም
*ጭንቀት እና የወር አበባ መምጣት ናቸው።
*በዘር የመተላለፍ እድሉ ከፍተኛ ነው።

ብጉር እንዳይባባስ ምን እናድርግ?

*ብጉር የወጣበትን ቦታ በስሱ ማጽዳት በውሃና በሳሙና መታጠብ (በቀን 2 ጊዜ)።
*ቅባታማ የሆኑ የመዋቢያ ውጤቶችን መጠቀምን ያስውግዱ።
*በብጉር የተጎዳ ቆዳዎን በእጅዎ አይነካኩ።
*ከባድ የጉልበት ስራ ከሰሩ በሗላ ገላዎንና ፊትዎን ይታጠቡ።

ቡጉርን በ1 ሳምንት ውስጥ የማስለቀቂያ ዘዴዎች!

1-የፈረንጅ እርሾ (baking soda)፦ የፈረንጅ እርሾ የቆዳዎን የሞቱ ሴሎች ያስወግዳል፡፡

ሁለት የሻይ ማንኪያ የፈረንጅ እርሾ ከትንሽ ውሀ ጋር አደባልቀው ይቀቡ። ከዚያም ከትንሽ ደቂቃ በኋላ ይታጠቡ፡፡

2- ገብስ፦ ወዝ የበዛበትን ቆዳ በማፅዳት የሞቱ ሴሎችን ያስወግዳል፡፡

በ1 የሻይ ስኒ ዱቄቱ የበሰለ ገብስ ላይ አንድ የሻይ ማንኪያ ማር ና ግማሽ የሎሚ ጭማዊ መደባለቅ፣ ድብልቆቹን በቆዳ ላይ ማሸት፣ ለ30 ደቂቃ በማቆየት ለብ ባለ ውሀ መታጠብ፣ ይሄንን በሳምንት አንዴ ወይም ሁለቴ ያድርጉት

3- የሎሚ ጭማቂ፦ በሎሚ ውስጥ ያለው አሲድነት ብጉርን ለማስወገድ ጥሩ ጠቀሜታ አለው።የተቆረጠ ሎሚ ቆዳዎትን ይቀቡ ከትንሽ ደቂቃም በኋላ ይታጠቡት።

በተጠቀሱት መከላከያ መንገዶች የማይሻሻል ከሆነ ወደ ሀኪም በመሄድ ያማክሩ።

ጠቃሚ ነውና ለወዳጆ ያካፍሉ!
T.me/ethio_mereja
2.7K views20:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-18 22:38:30
"አህጉር አቋራጭ ሮኬት ሰርቼ የሀገሬን ወታደራዊ ኃይል አጠናክራለው" - ተማሪ ሳሙኤል ዘካርያስ

የ16 ዓመቱ ባለ ልዩ ተሰጥኦ ተማሪ ሳሙኤል ከዋልታ ጋር በነበረው ቆይታ ችግር ፈቺ የሆኑ የምርምርና የፈጠራ ሥራዎችን በመስራት በቴክኖሎጂው ዘርፍ ሀገር ከፍ እንድትል እንደሚሰራ ተናግሯል፡፡ ታዳጊው አህጉር አቋራጭ የሆነ ሮኬት ሰርቼ ሀገሬን በወታደራዊ ኃይል ጠንካራ አንድትሆን አደርጋታለው ሲል ያለውን እቅድ ገልጿል።

የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አስተዳደር (ኢመደአ) ዋና ዳይሬክተር እንዳሉት ታዳጊ ሳሙኤል ዘካሪያስን በመቀበል በአስተዳደሩ በሚገኘው የኢትዮ-ሳይበር ታለንት ማዕከል እንዲታቀፍና የፈጠራ ሥራዎቹን ወደተሻለ ደረጃ እንዲያደርስ እገዛ እየተደረገለት መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

እንዲህ አይነት ትውልድ ነው ለሀገራችን የሚያስፈልጋት። ኢትዮጵያ በጠላት እንዳትደፈር ለሀገር የሚቆም፣ ለሀገሬ ብሎ የሚሰራ ትውልድ ነው የሚያስፈልገን። በርታ ወንድማችን

T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
5.2K viewsedited  19:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-18 21:52:21
ትልቅ እና አደገኛ የተባለ ከሜክሲኮ ወደ አሜሪካ የሚወስድ ዕፅ ማስተላለፊያ ዋሻ ተገኘ!!

ከሜክሲኮ ወደ አሜሪካ አደገኛ ዕፅ ለማስተላለፊያነት የሚያገለግለውና 531 ሜትር የሚረዝመው ዋሻ መገኘቱ ተገልጿል።

ዋሻው
ሐዲድ የተዘረጋለት፣
የአየር መቆጣጠሪያ ስርዓት (ቬንትሌሽን) የተገጠመለት ሁሉን ያሟላ ነው ተብሏል።

የሳውዘርን ካሊፎርኒያ አውራጃ የአሜሪካ አቃቢ ሕግ ጽሕፈት ቤት ዋሻው ከመሬት 18 ሜትር ጠልቆ የሚገኝ እና አንድ ሜትር መጠነ ዙርያ (ዲያሜትር) እንዳለው ተገልጿል።

ወደ ዋሻው የሚጠጉ መኪኖች ላይ በተደረገ ፍተሻ አደገኛ ዕፅ መገኘቱን ተከትሎ በተደረገ ምርመራ አንድ መጋዘን የተገኘ ሲሆን መጋዘኑ ውስጥ ደግሞ ድንበሩን ተከትሎ የተቆፈረ ምሥጢራዊ ዋሻ መግቢያን አግኝተዋል።

የአቃቢ ሕግ ጽሕፈት ቤት እንደሚለው 799 ኪሎ ግራም ኮኬይን፣ 74 ኪሎ ግራም ሜታፌታሚን እና 1.5 ኪሎ ግራም ሄሮይን ከስድስት ተጠርጣሪ ሰዎች ጋር በቁጥጥር ሥር ውሏል። ዕድሜያቸው ከ31 እስከ 55 የሚሆኑት እነዚህ በቁጥጥር ሥር የዋሉት ተጠርጣሪዎች ጥፋተኛ ሆነው ከተገኙ ዕድሜ ይፍታህ ሊፈረድባቸው ይችላል። ከዚህ በላይ የ1 ሚሊዮን ዶላር የገንዘብ ቅጣትም ይጣልባቸዋል።

በካሊፎርኒያ ለመጨረሻ ጊዜ እንዲህ ያለ ምሥጢራዊ ዋሻ የተገኘው ከሁለት ዓመት በፊት ነበር። ያ ዋሻ 1ሺህ 313 ሜትር ርዝመት የነበረው ሲሆን በርዝመቱም ተወዳዳሪ ያልተገኘለት ነው። እንደ አውሮጳዊያኑ ከ1993 ጀምሮ 90 የሚሆኑ አደገኛ ዕፅ ማስተላለፊያ የምድር ውስጥ ድብቅ ዋሻዎች በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ውለዋል። (ምንጭ፦ ቢቢሲ)
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
7.6K viewsedited  18:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-18 20:11:10
ብርጋዴር ጄነራል ተፈራ ማሞ ባህር ዳር መሆናቸው ተሰምቷል!!

ብርጋዴር ጄኔራል ተፈራ ማሞ የደረሱበት ሳይታወቅ ከቆዩ ከ2 ቀናት በኋላ ባሕር ዳር እንዳሉና ደህና መሆናቸውን የሚገልጽ መልዕክት እንደደረሳቸው ባለቤታቸው ተናግረዋል።

ብርጋዴር ጄኔራል ተፈራ ማሞ ሰኞ ግንቦት 08/2014 ዓ.ም. ከቤታቸው ረፋድ ላይ ከወጡ በኋላ የደረሱበት ሳይታወቅ እስከ ረቡዕ አመሻሽ ድረስ ቆይተዋል።

ባለቤታቸው ወ/ሮ መነን ኃይሌ ዛሬ ምሽት ለቢቢሲ አማርኛ አገልግሎት በሰጡት ቃል፤ የጄነራል ተፈራ ጠበቃና የሚያውቋቸው ሰዎች ባለቤታቸው ባሕር ዳር ውስጥ በሚገኘው ዘጠነኛ ፖሊስ ጣቢያ ውስጥ እንዳሉ እንደነገሯቸው ገልፀዋል።

ወ/ሮ መነን ባለቤታቸው በላኩት መልዕክት ደህና መሆናቸውን እና አሁን ያሉበት ቦታ በመግለጽ ቤተሰባቸው እንዲረጋጋ መልዕክት ልከዋል ብለዋል። ከአማራ ክልል የፀጥታና ደኅንነት እንዲሁም ፖሊስ ማብራሪያ ለመጠየቅ የተደረገ ሙከራ አለመሳካቱን ቢቢሲ አስነብቧል።(ቢቢሲ)
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
11.9K viewsedited  17:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-18 19:42:33
“የአማራ ክልል መንግሥት ሕግ የማስከበር ሙሉ አቅም አለው”- ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል ከፋለ

የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ/ር) ክልሉ ሕግ የማስከበር ሙሉ አቅም እንዳለው ገለጹ፡፡

ርዕሰ መሥተዳድር ይልቃል በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በሰጡት መግለጫ ወያኔና የወያኔ ፈረሶች የኢትዮጵያ ሕዝብ ጠላቶች ናቸው ብለዋል። በግንባር አካባቢ የወያኔ ፈረስ ሆነው የሚያገለግሉትን ኃይል አዘጋጅተን እየተፋለምን ነው ሲሉም አክለዋል።

የአማራ ክልል የፀጥታ ምክር ቤት በዝርዝር አጥንቶ ክልሉን ለማዳከም የሚሠሩ ጠላቶች መኖራቸውን አረጋግጧል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ የውስጥ ጠላቶችን ለመዋጋት የውስጥ አንድነታችንን ማጠናከር አለብን ብለዋል፡፡

የኅብረተሰቡ በሰላም ወጥቶ የመግባት እንቅስቃሴ ችግር ውስጥ እየወደቀ መሆኑንም ተናግረው ውስጡን እያዳከመና እየከፋፈለ የሚገኝ ኃይል እንዳለም አረጋግጠናል ነው ያሉት።ሕገወጥ ተኩስ በአጭር ካልተቀጨ በስተቀር ለኅብረተሰቡ ስጋት ይሆና ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ የልማት እንቅስቃሴዎች በሰላማዊ ሁኔታ እንዳይከናወኑ እየተደረገ መሆኑን መገንዘባቸውንም ተናግረዋል።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
11.7K viewsedited  16:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ