2022-11-07 20:32:34
#Nairobi
የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ዛሬ ናይሮቢ ላይ የተናገሩት ፦
" የቴሌኮም፣ የኢነርጂ እና የባንክ አገልግሎቶችን መልሰን ማገናኘት አለብን።
ከዚያ በፊት ግን ሰዎቻችን በቅድሚያ ምግብ እና መድኃኒት ይፈልጋሉ። ይህን ለማፋጠን እየሞከርን ነው።
ክልሎችን ጨምሮ ሁሉም ወገኖች በባለፉ ጉዳዮች ከመዘፈቅ ይልቅ ተስፋ እንዲፈነጥቁ እና መጪውን ጊዜ በጸጋ እንዲቀበሉ መንግስት እያበረታታ ነው። "
አቶ ጌታቸው ረዳ (ከህወሓት) ፦
" በስምምነታችን የተካተቱ ብዙ መደረግ ያለባቸው ነገሮች አሉ።
ከእነዚህ ተግባራት መካከል የአገልግሎቶች መጀመር አንዱ ነው።
የአገልግሎቶቹ ቁጥር ከፍ ሲልም በተደራዳሪ ወገኖች መካከል የሚኖረው መተማመን እና ግንኙነት አብሮ ይጨምራል፤ በሰዎች አዕምሮ ውስጥም ተስፋ ይዘራል ፤ ለማስፈን እየሞከርን ያለውን ሰላም የበለጠ ያጠናክራል።
" ... እኛ የገባነውን ቃል ለማክበር ቁርጠኛ ነን። "
ኡሁሩ ኬንያታ ፦
" በፕሪቶሪያ ጀመርን፣ መንገዳችን እየተጠጋ ፤ አሁን ናይሮቢ ነን ፣ በሚቀጥለው ጊዜ ስብሰባችን መቐለ እንደሚሆን ተስፋ አድርጋለሁ ፤ በመጨረሻም አዲስ አበባ ላይ አብረን እናከብራለን። ይህ ጸሎታችን ፣ ተስፋ የምናደርገው እና የምንፈልገው ነው። "
* ቪድዮው እና የኬንያታ ንግግር ከCitizen TV Kenya እንዲሁም የአምባሳደር ሬድዋን ሁሴንና የአቶ ጌታቸው ረዳ ንግግር በኢትዮጵያ ኢንሳይደር ከቀረበ ዘገባ ላይ የተወሰደ ነው።
ለበለጠ መረጃና ጥቆማ በዚህ ላኩልን፡፡
@ethio27info_bot @ethio27info
500 views17:32