Get Mystery Box with random crypto!

Bekulu Entertainment

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethio27info — Bekulu Entertainment B
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethio27info — Bekulu Entertainment
የሰርጥ አድራሻ: @ethio27info
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 12.54K
የሰርጥ መግለጫ

ትኩስ መረጃወች በየደቂቃ የሚለቀቁበት channel እዲሁም:-
፠ አጫጭር ታሪኮች
፠ስፖርት እና ወቅታዊ ጉዳዮች ይዘገቡበታል።

https://t.me/joinchat/AAAAAEdTBZdXx8xrHyomTg
ለበለጠ መረጃና ጥቆማ በዚህ ላኩልን፡፡
@ethio27info_bot @ethio27info_bot

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 64

2022-07-15 21:16:47
ከክልልነት ጥያቄ ጋር በተያያዘ የተሰጠ ማስጠንቀቂያ !

የፌዴራል የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል ዛሬ ምሽት ባወጣው መግለጫ ፤ የክልልነት ጥያቄዎች በሰላማዊ መንገድ ምላሽ እንዲያገኙ ከመንቀሳቀስ ይልቅ ጉዳዩን የአመጽና የሁከት መነሻ ለማድረግ በሚሞክሩ አካላት ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ አስጠንቅቋል።

ከመግለጫው የተወሰደ ፦

" የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልላዊ መንግሥት በስሩ የሚገኙ ዞኖችን በአዲስ መልክ ለማዋቀር እንቅስቃሴ እያደረገ ይገኛል፡፡

ጌዲኦም በአዲስ መልክ ከሚዋቀሩ ዞኖች አንዱ ሲሆን፤ የኅብረተሰቡን ተሳትፎ በተጨባጭ ለማረጋገጥ ይቻል ዘንድ ሰሞኑን የማወያያ ሰነዶች ተዘጋጅተው የዞኑ ነዋሪ እየመከረበት ነው።

ይሁንና የጌዲኦ ዞን የክልልነት ጥያቄ መፍትሔ የማይሰጠው ከሆን ጥያቄያችንን በኃይል እናስፈጽማለን የሚሉ አካላት በህቡዕ ተደራጅተው እየተንቀሳቀሱ መሆኑ በተጨባጭ ተረጋግጧል።

በህቡዕ የተደራጁት አካላት የጥፋት እቅዶቻቸውን ለማሳካት ሀሰተኛ የማህበራዊ ትስስር ገጾች በመክፈት የተዛቡና የፈጠራ መረጃዎችን እያሰራጩ ሲሆን ማኅበረሰቡንም በተሳሳቱ መረጃዎች ለማደናገር እየሞከሩ ይገኛሉ።

እነዚህ አካላት ያደራጇቸው ግለሠቦችና ቡድኖች #ቤት_ለቤት ጭምር እየተንቀሳቀሱ ቅስቀሳ እያደረጉ ይገኛሉ፤ ይህም ባግብረኃይሉ ተደርሶበታል።

ለዚህ እኩይ ዓላማ የተደራጁና የተሰለፉ ግለሠቦችንና ቡድኖችን በደኅንነትና በጸጥታ መዋቅር አማካኝነት ተለይተው ክትትል እየተደረገባቸው ነው። ይህን በማስገንዘብ፤ ከጥፋት ተልዕኳቸው እንዲቆጠቡ በጥብቅ እናሳስባለን።

ይህን ተላልፈው በሚገኙ ላይ ተገቢውን ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ እናስጠነቅቃለን። "

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

ለበለጠ መረጃና ጥቆማ በዚህ ላኩልን፡፡
@ethio27info_bot @ethio27info
1.4K views18:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ