Get Mystery Box with random crypto!

📖✏️Dilachin General Secondary School 📚📝ድላችን አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት🔔🇪🇹

የቴሌግራም ቻናል አርማ dilachingeneralsecondaryschool — 📖✏️Dilachin General Secondary School 📚📝ድላችን አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት🔔🇪🇹 D
የቴሌግራም ቻናል አርማ dilachingeneralsecondaryschool — 📖✏️Dilachin General Secondary School 📚📝ድላችን አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት🔔🇪🇹
የሰርጥ አድራሻ: @dilachingeneralsecondaryschool
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.00K

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2022-10-03 10:56:59
773 views07:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-03 10:56:48 Bus schedule for grade 12 exam
616 views07:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-28 14:50:09 ለ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች በሙሉ
ከመስከረም 18-20/2015ዓ/ም የሚሰጠውን የከተማ ሞዴል ፈተና ያልተፈተነ/ች ተማሪ የሀገር አቀፍ ፈተናን በፈቃዱ መፈተን የማይፈልግ መሆኑን አውቆ/ቃ ወደ ፈተና ጣቢያ/የተመደቡበት ዩኒቨርስቲ/ የማንወስድና ት/ቤቱ ሀላፊነት የማይወስድ መሆኑን እየገለፅን ፈተናውን ተፈትነው ያጠናቀቁ ተማሪዎች ግን
1. አጠቃላይ የፈተናን ሁኔታ
2. ወደ ፈተና ጣቢያ የሚደረግን የትራንስፖርት አግልግሎት
3. የጉዞ መነሻና መመለሻ ቀንና ሰዓት
4. ወደ ፈተና ጉዞ መነሻ ቦታ
5. የሚያዙ ቁሳቁሶችንና የሚከለከሉ ነገሮችን ጨምሮ በሌሎች ጉዳዮች ዙሪያ አርብ ከፈተና በኃላ ገለፃ የሚደረግ ይሆናል።
ት/ ቤቱ
798 views11:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-26 13:25:02 ለ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ተፈታኝ ተማሪ ወላጆች በሙሉ
ከመስከረም 30/2015 ዓ/ም ጀምሮ ለሚሰጠው ሀገር አቀፍ ፈተና ስለ ልጆቻችሁ የአፈታተን ሁኔታ በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ት/ፅ/ቤት ገለፃ ስለሚሰጥ እሮብ በ18/01/2015ዓ/ም በየካቲት 23 ትምህርት ቤት አዳራሽ ጠዋት 5:00 ላይ እንድትገኙ እናሳስባለን።
ት/ቤቱ
553 views10:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-26 13:15:56 የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የፈተና ዝግጅት እና አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ዲናኦል ጫላ የተፈታኞችን መብትና ግዴታዎች እንዲሁም ለተፈታኞች የተፈቀዱ እና የተከለከሉ ነገሮች ያቀረቡ ሲሆን በዚህም
የተፈታኞች መብቶች የሆኑት፡- 
ከፈተና ጥያቄ ውጪ ማንኛውንም ያልተረዳውን ነገር ጠይቆ የመረዳት መብት
በየኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ ምግብ፣ የህክምና አገልግሎት፣ የማደሪያ ክፍል፣ ፍራሽና ትራስ የማግኘት መብት
ማንኛውም ተፈታኝ በዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ ያለውን የቤተ መጽሐፍት፣ የመጸዳጃ ቤቶች፣ የሻወር፣ የካፍቴሪያዎች፣ የሚኒ ሱፐር ማርኬቶች፣ የተለያዩ ሱቆች፣ የመናፈሻና መዝናኛ አገልግሎቶችን የመጠቀም መብት
የኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ የጋራ የደህንነት ጥበቃ የማግኘት መብት
. በፈተና ሰዓት መፈተኛ ክፍል ገብቶ ብርሃናማ የመፈተኛ ቦታ፣ ወንበር፣ መጻፊያ ጠረጴዛ የማግኘት መብት
ፈተና ከመጀመሩ አንድ ቀን ቀድሞ ስለፈተናው ገለጻ (ኦሬንቴሽን) የማግኘት መብት
የተፈታኞች ግዴታ የሆኑት፡-
.  ማንኛውም ተፈታኝ በፈተና ማዕከልም ይሁን መፈተኛ ክፍል አድሚሽን ካርድ ይዞ የመገኘት ግዴታ
  ማንኛውም ተፈታኝ ወደ ዩኒቨርሲቲ ሲመጣ የትምህርት ቤት ወይም የነዋሪነት መታወቂያ ይዞ መገኘት
ማንኛውም ተፈታኝ ወደ ግቢ ከመግባቱ በፊትና ወደ መፈተኛ ክፍል ከመግባቱ በፊት ሙሉ አካላዊ ፍተሻ የመፈተሽ ግዴታ
ማንኛውም ተፈታኝ በዩኒቨርሲቲ ግቢና በመፈተኛ ክፍል የተከለከሉ ቁሳቁሶችን/ዕቃዎችን መያዝ የለበትም
ማንኛውም ተፈታኝ እርሳስ፣ ላጲስና የእርሳስ መቅረጫ ይዞ መገኘት
ማንኛውም ተፈታኝ የፈተና ደንብን የማክበር ግዴታ
ማንኛውም ተፈታኝ በፈተና ማዕከል ውስጥና በመፈተኛ ክፍል ውስጥ የፈተና አስፈጻሚዎች የፈተና አስተዳደር ሥራን ውጤታማ ለማድረግና ሁኔታዎችን ለማመቻቸት የሚያደርጉትን ጥረት የመተባበር ግዴታ አለበት
ማንኛውም ተፈታኝ ፈተና ከመጀመሩ በፊት መፈተኛ ክፍል የመገኘት ግዴታ አለበት
ተፈታኙ ፈተናው ሳይጠናቀቅ ከፈተና ክፍል የሚወጣ ከሆነ የፈተና ጥያቄ የያዘውን ቡኩሌት ለፈታኙ የማሰረከብ ግዴታ አለበት
ማንኛውም ተፈታኝ ወደ ተመደበበት ዩኒቨርሲቲ  ሲመጣ  አንሶላ፣  ብርድልብስና  የትራስ  ጨርቅ ይዞ የመምጣት ግዴታ አለበት
ዩኒፎርም ለብሶ መገኘት አለበት
ለተፈታኞች የተፈቀዱ ነገሮች
አዲስ  ወይም  ቀድሞ  ለመማርና   ለማጥናት   ሲጠቀሙበት  የነበሩ  ማስተወሻ   ደብተር ፣ የትምህርት መጽሐፍ፣ መንፈሳዊ/ኃይማኖታዊ መጽሐፍት፣ ባዶ ወረቀት
  ደረቅ ምግቦች ወይም ሰንዱች ምግቦች (ጩኮ፣ በሶ፣ ዳቦ ቆሎ፣ ቆሎ….)
ገንዘብ (ብር)
    የልብስ ወይም የእጅ ቦርሳ፣ የግል ልብስ፣ ጫማ
የግል ንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁስ (ሳሙና፣ ሞዴስ፣ የጥርስ ብሩሽ፣ የጥርስ ሳሙና፣ የገላ ማድረቂያ ፎጣ፣ ሶፍት፣ ሻምፖ፣ ኮንዲሽነር፣ ሎሽን፣ ቻፕስቲክ፣ የጸጉር ቅባት፣ የፊት ቅባት)
ለተፈታኞች የተከለከሉ ነገሮች
ማንኛውንም ዓይነት የጦር መሣሪያ ይዞ መገኘት የተከለከለ ነው፡፡
ማንኛውንም ዓይነት ስለት እና ሹልነት ያላቸውን ብረታ ብረቶችና ጠንካራ ፕላስትኮች ይዞ መገኘት የተከለከለ ነው
ማንኛውም ድምጽ የሚቀዳ፣ ፎቶ የሚያነሳ፣ ቪዲዮ የሚቀርጽ፣ ከቴሌ መስመርም ሆነ ከቴሌ መስመር ውጭ መልዕክት በዲጂታል መንገድ የሚሰጥ ወይም የሚቀበል የግል ዕቃ/መሳሪያ /ቴክኖሎጂ ውጤት፣ ስልክ፣ አይ-ፓድ፣ ታብሌት፣ ኮምፕዩተር፣ ላፕቶፕ፣ ስማርት ሰዓት፣ ማጂክ ብዕር/እስክሪብቶ፣ ማጂክ ኮት/ጃኬት እና  ሌሎች  ማንኛቸውም  ፎቶ፣  ምስል  እና  ድምጽ የሚቀርጹ የኤሌክትሮኖክስ መሣሪያዎችን በዩኒቨርሲቲው ግቢ ውስጥም ሆነ ግቢ  ዙሪያ  ይዞ መገኘት ወይም መጠቀም የተከለከለ ነው፡፡
በዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ ማንኛውንም ዓይነት የግል ፍላሽ ዲስክ፣ ሃርድ ዲስክ፣ ሲዲ፣ ሚሞሪ፣ ሚሞሪ ሪደር፣ ኦ-ቲጂ ኮንቨርተርና መሰል ዕቃዎችን ይዞ መገኘት  ወይም  መጠቀም  የተከለከለ ነው፡፡
ማንኛውም አደንዛዥ እጾች (ጫት፣  ሲጋራ፣  በሓኪም  ማዘዣ  የሌለው  መድኃኒት  (በሽሮፕም ይሁን በታብሌት፣ ህክምና መስጫ መርፌ)) መያዝ ወይም መጠቀም የተከለከለ ነው፡፡
ማንኛውም ዓይነት የአልኮል መጠጥ ይዞ መገኘት ወይም መጠቀም የተከለከለ ነው፡፡
ማንኛውም ዓይነት የአንገት ሐብል፣ የጸጉር ጌጥ፣ የጆሮ ጌጥ፣ የጣት ቀለበት፣ የእጅ አንባር፣ አድርጎ ወይም ይዞ መገኘት የተከለከለ ነው፡፡ (ከልሙጥ የጋብቻ ቀለበት በስተቀረ)
ፈተና ከተጀመረ ከ30 ደቂቃ በኋላ ወደ ፈተና ክፍል  መግባት  እና  ፈተናው  ተጀምሮ  45 ደቂቃ   ሳይሞላ  ከፈተና ክፍል መውጣት የተከለከለ ነው፡፡
ተፈታኙ ፈተናው ሳይጠናቀቅ ከፈተና ክፍል የሚወጣ ከሆነ የፈተና ጥያቄ የያዘውን ቡኩሌት ይዞ መውጣት ተከለከለ ነው፡፡
በፈተና ሰዓት በመፈተኛ ክፍል ውስጥ ማስቲካ መያዝም ሆነ መጠቀም የተከለከለ ነው፡፡
በዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ በግልም ሆነ በቡድን መጮህ ወይም በጣም ከፍተኛ ድምጽ ማሰማት የተከለከለ ነው፡፡
የሚሉት ተጠቃሽ ናቸዉ፡፡

በአዲስ አበባ 49,203 ተማሪዎች ፈተናውን ለመውሰድ መመዝገባቸውንና ፈተናውም ከመስከረም 30 ጀምሮ በቅድሚያ የሶሻል ሳይንስ ተማሪዎች ተፈትነው ሲጨርሱ የናቹራል ሳይንስ ተማሪዎች ቀጥለው እንደሚፈተኑ የተገለጸ ሲሆን ተፈታኝ ተማሪዎች በፈተና ወቅት የምግብና የመኝታ አገልግሎቶችን በየተቋማቱ እንደሚያገኙም ተጠቁማል፡፡
2.0K views10:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-26 13:14:26 ቀን 16/1/2015 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ኮማንድ ፖስት በፈተናው ቅድመ ዝግጅት ዙሪያ ውይይት አካሄደ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ቅድመ ዝግጅት ላይ ፈተናዉን ለማስተግበር ከተቋቋመዉ ኮማንድ ፖስት አባላት ጋር ውይይት አካሄደ፡፡ በውይይቱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ማኔጅመንት አባላት ፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፣ የኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፣ የኢትዮጵያ የሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ፣ የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና የፌደራል ቴክኒክና እልጠና ኢንስቲትዩት ሀላፊዎች እና የክፍለ ከተማ የትምህርት ጽፈት ቤት ሀላፊዎች  ተሳታፊ ሆነዋል፡፡

ዘንድሮ ፈተናው በሀገር አቀፍ ደረጃ ከመስከረም 30/2015 ዓ.ም ጀምሮ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እንደሚሰጥ ቀደም ብሎ በትምህርት ሚኒስቴር የተገለጸ ሲሆን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርም ፈተናውን አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፤ ኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፤ ኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ፣ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና ፌደራል ቴክኒክና እልጠና ኢንስቲትዩት ለመስጠት የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተሰሩ መሆኑ ተገልጻል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ ዘንድሮ ፈተናው ለመጀመሪያ ጊዜ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ቅጥር ግቢ ውስጥ የሚሰጥ እንደመሆኑ መጠን ፈተናዉ የሚሰጥባቸው ተቋማትም ሆኑ ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገቢዉን ቅድመ ዝግጅት ሁሉ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል፡፡ ሀላፊዉ አክለዉም ለተፈታኝ ተማሪዎች የሚሰጠዉ ኦረንቴሽንም በአግባቡ መከናወን ይኖርበታል ብለዋል፡፡
2.0K views10:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-26 13:08:58 ለ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች
409 viewsedited  10:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-25 09:35:45 ለተማሪዎች በሙሉ
ነገ በ16/01/2015 ዓ/ም ትምህርት የሌለ መሆኑን አውቃችሁ እሮብ በ18/01/2015 ዓ/ም ግን መደበኛው ትምህርት የሚቀጥል መሆኑን እንገልፃለን።
ት/ቤቱ
548 views06:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ