2022-12-15 20:17:19
#NationalExam
2ኛው ዙር የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከታህሳስ 18 እስከ 21/2015 ዓ.ም በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ይሰጣል።
በሁለተኛው ዙር ለፈተና የሚቀመጡ የሁሉም ክልል ተማሪዎች መለየታቸውን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።
በሁለተኛው ዙር የ12ኛ ክፍል ፈተና የሚወስዱ ፦
• የመጀመሪያውን ዙር ፈተና በወሊድ ወይም በእርግዝና ምክንያት መፈተን ያልቻሉ፣
• በሕግ ጥላ ስር ወይም በማረሚያ ቤት ሆነው ለመፈተን ያልቻሉ፣
• የሀገር መከላከያ ሠራዊት ወይም የፌዴራል ፖሊስ ወይም የክልል ልዩ ኃይል አባል ሆነው በወቅቱ በግዳጅ ላይ በመሆናቸው ያልተፈተኑ፣
• በህመም ወይም ተቀባይነት ባገኘ ችግር ምክንያት ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል ፈተና ያልወሰዱ፣
• ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በደረሰው የድልድይ መደርመስ አደጋ ምክንያት ያልተፈተኑ፣
• በደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ በተፈጠረው ችግር ምክንያት አንድ ፈተና እንዲፈተኑ የተወሰነላቸው፣
• ተቀባይነት ባገኙ ችግሮች ምክንያት ፈተና እንዲወስዱ የተወሰነላቸው።
763 views17:17