2023-06-03 20:24:29
#የአማራ_ሊግ_ማጠቃለያ_ውድድር በዛሬው ዕለት ፍፃሜውን አግኝቷል።
ከግንቦት 17- 26 በባህር ዳር ከተማ አስር ቡድኖች በ3 ምድብ ተከፍለው ውድድራቸውን ሲያደርጉ ቆይተው ወደ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና የሚሄዱ 5 ክለቦች ተለይተዋል።
በመዝጊያ ፕሮግራሙ ላይ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ም/ፕሬዘዳንት ዶ/ር #ዳኛቸው_ንግሩ እና ሌሎች የክልሉ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ አመራሮች ተገኝተዋል።
በፍፃሜው የተገናኙት #ጎንደር_አራዳ እና #ደምበጫ_ከተማ ቀደም ሲል በምድብ ጨዋታ ተገናኝተው ጎንደር አራዳ በደምበጫ ከተማ 5 ለ 0 ተሸንፎ በዕጣ ግማሽ ፍፃሜውን የተቀላቀለ ክለብ ቢሆንም በፍፃሜው ግን ጠንካራውን ደምበጫ ከተማን 2 ለ 1 በማሸነፍ ሻምፒዮን ሆኗል።
#ጎንደር_አራዳ
#ደምበጫ_ከተማ
#ቲሊሊ_ከተማ
#ቦረና_መካነሰላም እና
#ደብረታቦር_ከተማ ወደ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ማለፋቸውን ያረጋገጡ የክልሉ ክለቦች ሆነዋል።
ውድድሩ ዛሬ ሲጠናቀቅ
1. #ጎንደር_አራዳ ( ) የወርቅ ሜዳሊያ
2. #ደምበጫ_ከተማ የብር ሜዳሊያ
2. #ቲሊሊ_ከተማ የነሀስ ሜዳሊያ
የውድድሩ ኮከብ ግብ አግቢ
#እንድሪያስ_ያዕቆብ ከደምበጫ ከተማ
የውድድሩ ኮከብ አሰልጣኝ
#አማኑዔል_ስዩም ከጎንደር አራዳ
የውድድሩ ኮከብ ተጨዋች
#አባይ_ማሩ ከጎንደር አራዳ
የውድድሩ የስፖርታዊ ጨዋነት ዋንጫ አሸናፊ
#ቲሊሊ_ከተማ
የውድድሩ የዋንጫ አሸናፊ
#ጎንደር_አራዳ እግር ኳስ ክለብ
በመጨረሻም ውድድሩን ለመሩ የጨዋታ አመራሮች የወርቅ ሜዳሊያ እንዲሁም ለተሳታፊ ክለቦች የተሳትፎ የምስክር ወረቀት እና ለውድድሩ መሳካት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱ ተቋማትና ግለሰቦች የምስጋና የምስክር ወረቀት ከአማራ ክልል እግር ኳስ ፌደሬሽን ተበርክቶ ፕሮግራሙ ተጠናቋል።
ዳጉ ስፖርት ውድድሩ ከተጀመረበት ጊዜ እስከ ፍፃሜው ላበረከትነው የሚዲያ ሽፋን የምስጋና የምስክር ወረቀት ከፌደሬሽኑ ተበርክቶላታል።
https://t.me/Dagu_Sport
4.1K viewsAbuchu, edited 17:24