2023-06-05 14:46:04
በአጭር አመት ቡድናቸውን ስኬታማ ካረጉ አሰልጣኞች ውስጥ አንዱ ነው።
በ 2015 ዓም የኢትዮጵያ አንደኛ ሊግ ውድድር በአጭር ጊዜ ስኬታማ ከሆኑት ጥቂት አሰልጣኞች ውስጥ ግንባር ቀደሙ ወጣቱ የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሌጅ ዋና አሰልጣኝ ደጀን ተሾመ ነው።
ወጣቱ አሰልጣኝ ክለቡን ኦሮሚያ ፖሊስ ኮሌጅን ከኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ውድድር ባደገበት አመት አንደኛ ሊጉን ጥሩ ውጤት በማምጣት አሁንም ወደ ከፍተኛ ሊጉ ማሳደግ ችሏል።
አሰልጣኝ ደጀን በውድድር አመቱ ከቡድኑ ጋር ያሳካቸው ስኬቶች
ክለቡን ወደ ከፍተኛ ሊግ አሳደገ
የማጠቃለያ ውድድሩ 3ኛ ደረጃ በማጠናቀቅ የ ነሐስ ሜዳልያ አሸናፊ
የማጠቃለያ ውድድሩ የስፖርታዊ ጨዋነት ዋንጫ አሸናፊ
በሊጉ ምድብ መ አሸናፊ 1ኛ ደረጃ
የዋንጫ አሸናፊ
የወርቅ ሜዳልያ አሸናፊ
ቡድኑን ወደ ማጠቃለያ ውድድር አሳልፏል
ወጣቱ አሰልጣኝ በተጨዋችነት ዘመን አንደኛ ሊግ በመጫወት ጥሩ የአጥቂ ስፍራ ተጨዋች ነበር ኦሮሚያ ፖሊስ ኮሌጅን በተጨዋችነት የተቀላቀለ ሲሆን በደረሰበት በጉልበት ጉዳት ምክንያት ከእግር ኳስ ተጨዋችነት ጫማውን የሰቀለ ቢሆንም ኦሮሚያ ፖሊስ ኮሌጅ ውስጥ ክለቡን ከማዋቀር ጀምሮ የክለቡ ቡድን መሪ ሆኖ ያገለገለ እና ከ2014 ጀምሮ ደግሞ የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሌጅ ዋና አሰልጣኝ በመሆን በዛው ዓመት ቡድኑን ከኦሮሚያ ሊግ ወደ አንደኛ ሊግ ማሳደግ ችሏል፡
በዘንድሮ ዓመት 2015 በመጀመሪያ ዓመት የአንደኛ ሊግ ቆይታው በመጀመሪያውና ሁለተኛውን ዙር ቡድኑ አንደኛ ሆኖ እንድያጠናቅቅ እና የዋንጫ ባለቤት እንድሆን አስችሏል፡፡
በ2015 የኢትዮጵያ አንደኛ ሊግ ማጠቃለያ አዳማ በተረገው ውድድር በጥሩ ብቃት ወደ ኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ኦሮሚያ ፖሊስ ኮሌጅ ማሳደግ ችሏል፡፡
በውድድሩን ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ በሜሊያ ውስጥ ገብቶ እንድያጠናቅቅ ከመስቻሉም በላይ ከፍተኛ ግምት የሚሰጠውን የስፖርት ጨዋነት ዋንጫ ክለቡ እንድያገኝ ያስቻለ በተጨማሪም በጥሩ ስነ ምግባር ሁልጊዜም አዲስ ነገር ለማወቅ የሚጥር አሰልጣኝ ነው፡፡
በከፍተኛ ሊግ ቆይታውም በወጣቶች ላይ የተመሰረተ ክለብ እንድኖር የሚሠራና በማጥቃት ላይ የተመሰረት እግር ኳስ የሚከተል አሰልጣኝ ነው፡፡
ኦሮሚያ ፖሊስ በዝህ ዓመት
ተጫወተ 28
አሸነፈ 17
አቻ ወጣ 6
ተሸነፈ 5
አስቆጠረ 45
የተቆጠረበት 16
አሰልጣኝ ደጀኔ የሚመራው ቡድን በማጥቃት ላይ የተመሰረት እግር ኳስ እንደሚከተል ቁጥራዊ መረጃዎች ማሳያ ናቸው።
ወጣቱ አሰልጣኝ በ 2015 ዓም በአንደኛ ሊጉ ባደጉበት አመት ወደ ከፍተኛ ሊግ ካደጉት ሁለት ስኬታማ ክለቦች ውስጥ አንዱ የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሌጄ ሲሆን አሰልጣኝ ደጀን የዚህ ታሪክ ባለቤት ነው።
አሰልጣኝ ደጀን በከፍተኛ ሊጉ ይህንን ታሪክ ያስቀጥል ይሆን ?
2.8K viewsDagu Sport Nuru, 11:46