2022-06-16 12:00:14
ዓለም አቀፍ የቤተሰብ ሐዋላ ቀን
International Day of Family Remittances (IDFR)
==========
ዓለም አቀፍ የቤተሰብ ሐዋላ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ8ኛ ጊዜ ‘በዲጂታልና እና በፋይናንስ አካታችነት መልሶ ማገገም እና ተቋቁሞ ማለፍ’ ‘Recovery and resilience through digital and financial inclusion’ በሚል መሪ ቃል በመከበር ላይ ይገኛል፡፡
ዓለም አቀፍ የቤተሰብ ሐዋላ ቀን በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ የውሳኔ ቁጥር (A/RES/72/281) የፀደቀ ሲሆን እ.ኤ.አ ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ በየአመቱ ሰኔ 9 ቀን (ጁን 16) ይከበራል፡፡
ቀኑ ከ800 ሚሊዮን በላይ ቤተሰቦቻቸውን ሕይወት ለማሻሻል እና የልጆቻቸውን የወደፊት ተስፋ ብሩህ ለማድርግ እጅግ አስቸጋሪ በሚባል ሁኔታ ውስጥ ሳይቀር እያለፉ ወደሃገር ቤት ገንዘብ የሚልኩ ከ200 ሚሊዮን በላይ ስደተኞች (ግማሽ ያህሉ ሴቶች ናቸው) አስተዋፅዖ የሚዘከርበት ነው፡፡
ዓለም አቀፍ ሐዋላ በታዳጊ ሃገራት ዜጎች ህይወት ውስጥ እጅግ ወሳኝ የሆነ ለውጥ የሚያመጣ ነው፡፡ ጥናቶች እንደሚያሳዩት በሐዋላ መልክ ወደ ታዳጊ ሀገራት የሚላከው ገንዘብ ሀገራቱ ከዓለም አቀፍ ለጋሾች ከሚያገኙት ይፋዊ የልማት ዕርዳታ በሦስት እጥፍ የሚበልጥ ነው።
ባለፉት ሀያ ዓመታት በሐዋላ የሚላከው የገንዘብ መጠን በአምስት እጥፍ ያደገ ሲሆን፣ ይህም በተቀባይ ሀገራት በኢኮኖሚያዊ እድገት መቀዛቀዝ ምክንያት ያጋጠሙ ችግሮችን ለመቋቋም አግዟል፡፡ በዓለም ባንክ ሪፖርት መሠረት በ2021 ዝቅተኛና መካከለኛ ገቢ ወዳላቸው ሀገሮች 605 ቢሊዮን ዶላር በሐዋላ መልክ ተልኳል፡፡
ወደሃገራችን በሐዋላ የሚላከው የውጭ ሃገር ገንዘብ በአብዛኛው በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በኩል የሚገባ ሲሆን፣ ባንኩ የውጭ ምንዛሪ ግኝት ለሀገር ኢኮኖሚ ያለውን ከፍተኛ ፋይዳ መሠረት በማድረግ የውጭ ምንዛሬ ግኝትን ለማሳደግ የሚረዱ የተለያዩ ስትራቴጂዎችን ተግባራዊ በማድግ ላይ ይገኛል፡፡
ከዚሁ ጋረ በተያያዘ በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በሀገራቸው ቤት ለመስራትና ሌሎች ቋሚ ንብረቶችን ለማፍራት የሚያስችላቸውን ብድር (የዳያሰፖራ ሞርጌጅ፣ የግልና ቢዝነስ ብድር) ባንኩ ያመቻቸ ሲሆን፣ ይህም በርካታ የውጭ ምንዛሬ ወደሃገር ውስጥ እንዲገባ እያገዘ ይገኛል፡፡
በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ህብረተሰቡ በጥቁር ገበያ የሚያደርገውን የውጭ ምንዛሪ ዝውውር በማስቀረት ወደባንክ እንዲመጣ ለማበረታታት የተለያዩ ሥራዎችን የሚሠራ ሲሆን፣ ከውጭ ሀገር የሚላክላቸውን ገንዘብ ከባንኩ የሚቀበሉ እና በባንኩ የሚመነዝሩ ደንበኞችን በዕጣ የሚሸልምበት መርሀ-ግብር (ይቀበሉ፤ ይመንዝሩ፤ ይሸለሙ!) ተጠቃሽ ነው፡፡
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዓለም አቀፍ የቤተሰብ ሐዋላ ቀንን በማስመልከት ሁሉም ህብረተሰብ ወደ ሀገር ቤት የሚልከውን የውጭ ሀገር ገንዘብ በባንክ በኩል ብቻ በማድረግ ለሀገር ልማት የበኩሉን አስተዋጻኦ እንዲያበረክት መልእክት ያስተላልፋል፡፡
5.2K viewsedited 09:00