Get Mystery Box with random crypto!

አትሮኖስ

የቴሌግራም ቻናል አርማ atronosee — አትሮኖስ
የቴሌግራም ቻናል አርማ atronosee — አትሮኖስ
የሰርጥ አድራሻ: @atronosee
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 163.71K
የሰርጥ መግለጫ

╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።
Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 13

2023-04-09 20:50:38 #ባል_አስይዞ_ቁማር››


#ክፍል_ሀያ_ስድስት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///

‹‹ምነው…ፒያሳ ይሻላል እንዴ?››ልዩ ነች የጠየቀችው፡፡

‹‹አይ የሆነች ጉዳይ ሳላለችብኝ ነው… ደረስ እንልና እንደውም እዛው ኢሊሊ ራት በልተን ከዛ ወደምትፈልጉበት ጭፈራ ቤት እንሄዳለን..››

ጊፍቲ ፈገግ አለች….ቀጥታ ፒያሳ ወደሚገኙ መደዳ ወርቅ ቤቶች ነበር ይዟቸው የሄደው..ልዩ እራሱ ያልጠበቀችው ነገር ስለሆነ ግራ ተጋባች…እሱ ራሱ ቀድሞ ያሰበበት ጉዳይ አልነበረም..ሰጥሀለው የምትለዋ ቃል ከአንደበቷ ተስፈንጥራ ስትወጣ በውስጡ በተፈጠረ ፍንጠዛና በምርቃና ድንገት ብልጭ ያለለት ሀሳብ ነው፡፡

‹‹ምነው ምን መጣ..?››ጠየቀችው፡፡

‹‹ቀለበታችን ሳንመርጥ የቀለበቱ ቀን ደረሰ እኮ?››

‹‹እንዴ ገና ሁለት ወር ይቀረናል እኮ››

‹‹ሁለት ወር ምን አላት….አይደል ጊፍቲ፡፡›› አለ ወደ እሷ ዞሮ ድጋፍ እድትሰጠው በሚፈልግ ንግግር…

እሷ የሰማችው አይመስልም ቅዝዝ ብላ ጭልጥ ያለ ሀሳብ ውስጥ ገብታለች

‹‹ጊፍቲ፡፡››

‹‹እ..ታድላችሁ…አዎ ትክክል ነው..ሁለት ወር በጣም አጭር ጊዜ ነው…››አለችና ተያይዘው ወደ ውስጥ ገቡ…ተገቢውን ቀለበት አማርጦ ለመግዛት ከሰላሳ ደቂቃ በላይ ነው የፈጀባቸው….በመጨረሻ እንደውም ጊፍቲ አሪፍ ነው ብላ ያሳየቻቸውን የዳይመንድ ፈርጥ ያለበት ቀለበትን ነው ሁለቱም በአንድ ድምፅ ተስማምተው የተገዛው..የሁለቱንም ቀለበት ሰጣትና ቦርሳዋ ውስጥ በመክተት እየተሳሳቁ ተያይዘው ወጡ…

እንዳአለውም ኢልሌ ሆቴል ጎራ አሉና እራታቸውን በልተው ሲወጡ ሶስት ሰዐት አልፎል…

‹‹አሁን ጭፈራ ቤት ለመሄደ ትክክለኛው ሰዓት ነው››አለ መድሀኔ…ፍንድቅድቅ ባለ ድምፅ፡፡
‹‹አዎ ግን እናንተ ብትሄዱ ይሻላል ..ከዚህ በላይ ካመሸው አከራዬቼ የውጭ በራፍ አይከፍቱልኝም…››አለች ጊፍቲ
‹‹እኛም አይከፍቱልንም››ሲል መለሰላት መድህኔ

‹‹አይ ቢሆንም እናንተ የራሳችሁ ማለቴ የወላጆቻችሁ ቤት ነው..ጨክነው አይጨክኑባችሁም እኔ ግን ኪራይ ቤት..››
ክንዷን ያዘችና ‹‹ነይ ባክሽ እስከአራት እስከ ከአምስት ሰዓት ዘና እንልና አዲሱ ቤታችን ሄደን ነው የምናድረው…አይደል መድህኔ?››

‹‹እ አዎ..ጥሩ ሀሳብ ነው….››አለ…..እሱም ያላሰበው አዲስ ሀሳብ ነው ያመጣችው፡፡
መኪና ውስጥ ገብተው መድሀኒ መንዳት ከጀመረ በኃላ…‹‹እንዴ አዲስ ቤት ተከራያችሁ እንዴ ?›› ስትል ጠየቀች

‹‹ አይ የእኔ ፍቅር አሪፍ ቤት ገዝቶ ሰርፕራይዝ አደረገኝ፣››አለችና መልስ ሰጠቻት፡፡ ለቤት ያላትን ፍቅር እሷም ሆነች ቃል ደጋግመው ነግረዋታል፡፡ለዛም ነው አይን አይኗን እያየች አድምቃ እያወራች ያለችው፡፡

‹‹ለእናንተ እኔ ደስ ብሎኛል አለች››የንግግሯ መዝረክረክ ግን ደስ እንዳላላት ያስታውቅባታል፡፡
‹‹ሰዎች የተለየ ሀሳብ አለኝ››ልዩ ነች ተናጋሪዋ፡፡

‹‹ምንድነው?››

‹‹ለምን የሚስፈልገውን መጠጥ ገዝተን ቀጥታ ወደቤታችን አንሄድም…..ግርግሩ ብቻ ነው የሚቀርብን …ሙዚቃው እንደሆነ እቤት አለ …እንቀውጠዋለን…››
መድህኔ ሁለቱንም እያፈራረቀ አያቸው…

‹‹ወይ በቃ ለካ ጊፍትዬ ጭፈራ ቤት ትወዳለች…››አለች ልዩ..አውቃነው እሷን ይሉኝታ ውስጥ ለመጨመር አስባ ይህቺን አረፍተ ነገር የሰነዘረችው፡፡

‹‹አረ በፍፅም.. አሪፍ እና የተለየ ሀሳብ ነው ያመጣሽው..እንደውም ጭፈራ ቤት አድሬ ነገ ጥዋት ተነስቼ ቢሮ መግባት ይከብደኛል.. እያልኩ እያሰብኩ ነው…››

መድህኔ ‹‹እንግዲያው ወደቤት ነዳሁት…››አለና አቅጣጫውን አስተካከለ…

ከሀያት ሪል እስቴት ወደተገዛው ግዙፍ ቪላ ነው የነዳው..መንገድ ላይ ቆሞ ሴቶቹን መኪና ውስጥ አስቀምጦ መአት አይነት መጠጦችንና የተወሰኑ የሚበሉ ነሮችን ገዝቶ ተመለሰ….እቤት ሲደርሱ አራት ሰዓት ተቃርቦ ነበር..የመኪናውን ጡሩንባ ቢያንጣጣም በቀላሉ ሊከፈት አልቻለም..ወርዶ በእጁ ጭምር መቀጥቀጥ የግድ ሆኖበት ነበር..ከዛ ዘበኛው በድንጋጤና በማለክለክ መጥቶ ከፈተና በተደናገጠ ደምፅ..‹‹ጋሺዬ ይመጣሉ ብዬ ስላላሰብኩ እንቅልፊቱ ጣለችኝ፣እንደው ይቅርታ››ተሽቆጠቆጠ፡፡

‹‹…ችግር የለውም…››ብሎ አረጋጋው…ኮፈኑን ከፈተና
‹‹ይህቺን እቃ ወደሳሎን ውሰድልኝ›› አለው…ዘበኛው በታዛዥነት አንከብክቦ ወደሳሎኑ ከነፈ…ጊፍቲ በግቢው ውበት ፈዛ ከግራ ወደቀኝ አይኗን እያስወነጨፈች ታያለች…የምታደርገውን እየተካታተለ እንዳልሆነ ሰው ችላ ብላ ክንዷን ያዘችና ወደቤት ይዛት ገባች…ከሳሎኑ ጀምራ እያንዳንዱን መኝታ ቤት…መታጠቢያ ቤቶችን… ኪችኑን አስጎበኘቻት….

‹‹እንግዲህ ልጅ እስኪመጣ ድረስ ለእኛ ይበቃናል?››አለቻት
‹‹ትቀልጂያለሽ አይደል?››
‹‹ምን እቀልዳለው..እኔና እናቴ ከሰራተኞቻችን ጋር የምንኖርበት ቤት እኮ የዚህን ሶስት እጥፍ ይሆናል…ከዛ ወጥቶ እዚህ መኖር..ብቻ ይሁን አሪፍ ነው››
‹‹እና ከሁለት ወር በኃላ ልትጋቡ ነዋ››ጠየቀቻት፡፡

‹‹አይ ከሁለት ወር በኃላ ምርቃቴ ስለሆነ ቀለበቴ ነው በደባልነት የሚደረገው ሰርጋችን ከሶስት ወር ነው….ምን ይታወቃል… አብረን አንሞሸር ይሆናል?››

‹‹አይ!! ብለሽ ነው?››አለቻት… ትክዝና ቅዝዝ ብላ….፡፡አዎ የፈለገችውም እንዲህ ውስጧን መበጣጠስና ተስፋ ማስቆረጥ ….ወይንም ማስጎምዠት ነበረ…‹.እርግጠኛ ነኝ ይሄኔ ስንቴ ምን አለ ይሄ ቤት የግሌ በሆነ ብላ ተመኝታለች..እንግዲህ ይሄን ቤት ከፈለገች..የቃልዬን እጅ ለቃ የመድህኔን እጅ መያዝ አለባት ማለት ነው…ያንን እንደምታደርግ ደግሞ ከዛሬ ጀምሮ ምልክት ልትሰጠኝ ይገባል….ጊዜ የለንም፡፡››ስትል እሷን ከጎኗ አቁማ በውስጧ አብሰለሰለች፡፡

ጉብኝታቸውን ጨርሰው ወደሳሎን ሲመለስ መድህኔ ጠረጳዛውን በመጠጥና በሚበሉ ቀለል ባሉ ምግቦች ሞልቶት ግዙፍ እስፒከር ያለውን ቴፕ አዘጋጅቶ ጠበቃቸው…
‹‹የእኔ ፍቅር ምርጥ እኮ ነህ›› ብላ ተንጠልጥላበት ጉንጩን ሳመችው፡፡ ‹‹መቼስ ዛሬ ከወትሮ በተለየ ሁኔታ ቁልትልት ብዬበታለሁ……››ስትል እራሷን ታዘበች
ጊፍቲ ሶፋ ላይ ቁጭ አለች……

‹‹ምን ልቅዳለችሁ?›› መድሀኔ ጠየቀ፡፡

‹‹ወይን ቢሆን ደስ ይለኛል…››መረጠች ጊፍቲ፡፡…
‹‹አዎ ከቀላል እንጀምር ለእኔም ወይን››ልዩም ከጊፍቲ ምርጫ ጋር ምርጫዋን አስማማች፡፡
እንግዲያው ቆንጆ የፈረንሳይ ወይን አለኝ….አለና ከተኮለኮሉት ጠርሙሶች መካከል አንዱን መዞ በእያንዳንዳቸው ብርጭቆ ቀዳላቸው …እና የራሱንም ይዞ ከፊት ለፊታቸው ቁጭ አለ፡፡
መጠጡ በወይን ቢጀመርም..ወደውስኪ ሲሸጋገር አንድ ሰዓት አልፈጀበትም። ስድስት ሰዓት ላይ ተኪላ ነበር ሻት እየተደረገ የነበረው ...ዳንስ ..ጭፈራው ቅውጥ ያለ ነበር፡፡ ልዩም ዛሬ እንደው የእነሱን ያህል ችሎታው እንደሌላት ብታወቅም ቁብ ሳይሰጠት ከእነሱ እኩል ስትቀውጠው አመሸች...ልዪነቱ መጠጡ ላይ እየጠጣች በማስመሰል ስትደፍው ..አንዳንዴ ወደእነሱ ስትገለብጥ በተቻለኝ መጠን የሰከረች በመምሰል ግን ሳትሰክር እራሷን ለማቆየት የተቻላትን ጣረች..እናም ተሳክቶላት ሰባት ሰዓት ሲሆን ሁለቱም በዳንስ ብዛት ውልቅልቅ ብለው በላብ ወርዝተው ከላይ የለበሱትን እያወለቁ ጥለው እሱ በነጭ ፓክ አውት እሷ ደግሞ በጥቁር ጡት ማስያዣ ነበሩ...ልዩም ያው እነሱን ለማበረታት በጡት መያዠ ብቻ ቀርታለች...በዳንሱ ሞቅታ መካከል ሁለቱንም አቅፍቸውና አንድላይ አጣብቃ ወዳራሷ ትጨምቃቸዋለች…እንደዛ ሲሆን እርስ በርስ አንዲፍተጉ እያደረገች ቅርበታቸውን እያጠናከረች ነው፡፡..አንዳንዴ ሞቅ ብሏቸው የጋለ የእርስ በርስ
1.5K viewsአትሮኖስ, 17:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-08 15:51:23
የ highschool ትምህርት ጊዜ ትዉስታ አለቦት ታድያ ምን ይጠብቃሉ ተቀላቀሉን እና ዘና ይበሉ
426 viewsPapa , 12:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-08 15:51:02
የጠበሳ ዘዴዎች ለወንድም ለሴትም ሴቶች ደፍረዉ የማይናገሩት ግን ከወንዶች የሚጠብቋቸዉ 7 ነገሮች
OPEN
410 viewsPapa , 12:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-07 23:12:20 ከፍቶኛል
300 viewspetelare Stay true, 20:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-07 18:08:06 #ባል_አስይዞ_ቁማር


#ክፍል_ሀያ_አምስት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///

ከምሽቱ 5 ሰዓት እቤት ክፍሌ አልጋዬ ላይ ተኝቼ ስለቃል እያሰብኩ ነው….መቼስ ቃል ቃል ብዬ እናንተንም አሰለቸዋችሁ አይደል  ምን ላድርግ..ተለክፌ እኮ ነው….እንቅልፌ መጥቷል ግን ከመተኛቴ በፊት አሱን ማየት ፈለኩ…ማለቴ በተለያየ ቀን ከመተኛቱ በፊት የፀለያቸውን ያልተለመዱ አይነት ፀሎቶችን እሱ ቤት በቀበርኩት ስውር ካሜራ አማካይነት ቀድቼ ላፕቶፔ ውስጥ አሉ..ከእነሱ መካከል አንድ ሁለቱ ማድመጥ ፈለኩ በዛውም ለእኔም እንደፀሎት ሀኖ ይቆጠልርልኝ ይሆናል…
ይሄ ከዛሬ አስር ቀን በፊት የፀለየው ነው፡፡
///

የዛሬ ሳምንት የፀለየው ደግሞ በእኔ ላይ እየሆነ  ያለው ሁሉ ትክክል ነው…በዙሪዬ ምንም  ገደል የለም…የመታኝ እንቅፋት በንቃት እየተራመድኩ እንዳልሆነ ሊያስታውሰኝ እንጂ ሊያደማኝ ፈልጎ አይደለም፡፡ እየበሰበሰ ያለው ነገር ከመበስበስ ቡኃላ ህይወት መስጠት ስላለ ነው…እየረገፈ ያለው የጠወለገና ደረቅ ቅጠል ለአዲሱና እንቡጠቹ ቅጠሎች ይበልጥ እንዲያቡብና እንዲያፈሩ ነው፡፡በዚህ አለም ላይ  ምንም አይነት የተዘበራረቀ ነገር የለም..እሆነ ያለውነገር ሁሉ አንተ ስለፈቀድክና መሆን ስለሚገባው የሆነ  ነው…ለምለሰሙ ዝናብ ከሰመይ በመርገፍ ምድርን ከጥሞና እንዴያረካት ቀድሞ ሰማዩ በጥቁር ደመና መሸፈንና መዝጎርጎር አለበት…ጨለማው ከሌለ ብሩሆ ጨረቃ የምትተፋውን ብርሀን ፈፅሞ ማየትም ማድነቅም አንችልም….ሁሉ ነገር ድንቅ ነው..ሁሉ ነገር ብሩህ ነው፡፡
አሜን.ብዬ ላፕቶፔን ዘጋሁና መብራቱን አጥፍቼ ተኛሁ፡

///
ከሶደሬ ከተመለሱ ሀያ  ቀን አልፏቸዋል፡፡ዛሬ ለሳምንታት ያቀደችውን ነገር የምትፈፅምበት ቀን ነው፡፡አዎ የምትፈፅመው  ነገር የጽድቅ ስራ አይደለም…አእምሮ የሚጨመድድ ከሳጥናኤል አእምሮ ካልተቀዳ በሰው ሀሳብ የማይታሰብ ነገር እንደሆነ ታውቃለች….ግን ደግሞ በነፃ ሚገኝ  ነገር የለም በሚል እራሷን ለማፅናናት ገፍታበታለች….፡፡‹‹አዎ    ቃልን የራሷ ለማድረግ እሷም መክፈል የሚገባትን መስዋዕትነት በፍቃደኝነት ለመክፈል ቆርጣለች….የልጅነት ጓዳኛዋን፤ የረጅም ጊዜ እጮኛዋ የሆነውን መድህኔን በፍቃደኝነት አሳልፋ ልትሰጥ ነው….አዎ ያንን ለማድረግ ደግሞ የመጨረሻውን ማስፈንጠሪያ የምትጫንበት ቀን ነው…ብቻ እንዲቀናትና ነገሮች በእቅዷ መሰረት እዲከወኑ ለማን መፀለይ እንዳለባት አታውቅም ‹‹እግዚያብሄርን እርዳኝ ብዬ እንዴት ጠይቀዋለሁ….?አረ ያሳፍራል፡፡››አለች ..ብቻ እንዲሁ እንዲቀናት ለራሷ ስኬትን ተመኘች…..በዛው ቅፅበት መኝታ ቤቴ ተንኳኳ፡፡

‹‹ማን ነው?››

‹‹እኔ ነኝ ልዩ..››አለች ከሰራተኛቸው አንዷ፡፡

‹‹እ ..ምን ፈለግሽ?›››

‹‹መድህኔ መጥቷል››

‹‹መጣው ጨርሼያለሁ በይው››

‹‹እሺ….››ብላ ተመልሳ ሄደች፡፡በጣም ተጨንቃ ዝንጥ ብላ ነው የጠበቀችውኩ፤የሚያስፈልጋትን ነገር ሁሉ በቦርሳዋ መጨማመሯን አረጋግጣ ክፍሏን ለቃ ወደታች ወደሳሎን ስትወርድ መድህኔና እናቷ ልክ እንደወትሮቸው አፍ ለአፍ ገጥመው ሲያወሩ ደረሰች፡፡….
እናትዬው ገና እንዳዮት‹‹ወይ ልጄ መልአክ መስለሻል …››አለቻት … መድህኔም ዞር ብሎ ከስር እስከላይ በገምጋሚ አይኖቹ ቃኛትና ፈገግ አለ…..

ከተቀመጠበት ተነሳና‹‹…በቃ ማሚ ሰሞኑን እመጣና በዝርዝር እናወራበታለን›› አላቸው፡፡

‹‹እሺ የእኔ ልጅ..ነገ ተነገ ወዲያ ቢሆን ደስ ይለኛል…ጊዜ የለንም፡፡››አሉት፡፡
..ምንም እንዳልገባው ሆና‹‹ለምኑ ነው ጊዜ የሌላችሁ?›› ብላ ጠየቀች ..ስለሰራጋቸው እንደሚያወሩ ግልፅ ሆኖላታል፡፡..በዚህ ወቅት በእሷም ሆነ በእሱ ቤተሰቦች ቤት ከእነሱ ሰርግ ውጭ ሌላ አንገብጋቢ አጀንዳ እንደሌለ ታውቃለች፡፡

‹‹አይ የአዋቂ ወሬ ነው….››አላትና አቅፏት ይዟት ወጣ…
ሲሸኞቸው ከኃላ የተከተሏቸው እናቷ‹‹ካደራችሁ ደውሉ››አሏቸው…
‹‹አንደውልም  …ከአሁኑ እወቂው እድራናል›››መለሰችላቸው፡፡
በእሱ መኪና ውስጥ ገብተው ገና ከጊቢ እንደወጡ‹‹በል ጊፍቲ እስቴዲዬም እየጠበቀችን ነው››አለችው..
‹‹እነሱም አብረውን ያመሻሉ እንዴ ..?እኔና አንቺ ብቻ ምንሆን መስሎኝ ?››አላት..ቅር ባለው ፊት፡፡
‹‹አዎ እኔም እንደዛ ነበር እቅዴ ..አሁን ከሀያ ደቂቃ በፊት ደውላ ደብሯት እስቴዲዬም ብቻዋን እዳለች ነገረችኝ ››
‹‹እንዴ  ፍሬንዷ ጋር አትደውልም…?››ሙግቱን ቀጠለ
‹‹ፍሬንዷ ማን ?››
‹‹እያሾፍሽ ነው..?ቃል ነዋ››
‹‹ፍሬንዷ ስትል እኮ ዝም ብሎ ጓደኛዋ የምትል መስሎኝ ነው..ቃልማ ለስራ ክፍለሀገር ወጥቷል….ለዛ እኮ ነው እምቢ ማለት የከበደኝ …አንተ በስራ ቢዚ ሆነህ ችላ በምትለኝ ጊዜ የምታዳብረኝ እሷ አይደለች..አሁን ውለታዬን ልመልስ ነዋ…››አለችው፡፡
‹‹አቤት አቤት..አሁን እኔ መቼ  ነው አንቺ ልታገኚኝ ፈልገሽ ቢዚ የሆንኩት…..ደግሞ የድሮ ጓደኞችሽን እርግፍ አድርሽ  ግንኙነትሽን ጠቅላላ ከእነዚህ ባልና ሚስት ጋር እድርገሻል ምንድነው ?አልገባኝም?…››አላት

በመርማሪ አይኖቹ ፡፡
‹‹ምነው አልተመቹህም እንዴ..?እንደዛ ከሆነ ….››
‹‹እንደዛ ከሆነ ምን…?››
‹‹ካልተመቹህ ቀስ በቀስ አቆማለኋ…››
‹‹አዎ አልተመቹኝም›› ቢል እንደማታቆም በውስጧ ታውቃለች..ግን ደግሞ ማስመሰል አለባት፡፡  አቁሚ ቢላት እንደውም እልክ ይዞት ጨርቋን ጠቅልላ እነሱ ጋር የምትገባ ሁሉ ይመስላታል፡፡እሱም አመሏን በጥልቀት ስለሚያውቅ እንደእዛ አይነት ቅብጠት አይቃብጥም፡፡
‹‹ኸረ..እንደውም ከእነሱ ገር መዋል ከጀመርሽ በኃላ  አሪፍ ሆነሻል፡፡››
‹‹አሪፍ ስትል?››ተበሳጭች
‹‹በቃ ደስተኛ ሆነሻል..በረባ ባረባው መነጫነጭ ትተሻል ባልልም በጣም ቀንሰሻል .ለምትጠየቂው ጥያቄ ቀና መልሶች  መመለስ እየተማርሽ ነው..አረ ከሁሉም በፊት እንድንጋባ ፍቃደኛ የሆንሽው ከእነሱ ጋር ጓደኛ ከሆንሽ በኃላ እኮ ነው፡፡››ብሏት የቅርብ ጊዜ ለውጧቾን ዘረዘረላት….ምንም የተሳሳተው ነገር የለም…ሁሉንም በአስተውሎት ታዝቦል….ችግሩ ከለውጦቹ ጀርባ የሸሸገችውን ድብቅ ሚስጥራዊ ተልዕኮ አለማወቁ ነው፡፡

‹‹ምን አልባት በእነሱ ፍቅር ቀንቼ ይሆናል…››

‹‹አረ እንኳን  ቀናሽ..እኔ ተጠቃሚ ሆኜያለሁ፡፡››
‹‹ዛሬ እንደውም እንዲህ ተቆነጃጅቼ የወጣሁት የሆነ ነገር ሰጥቼ ሰርፕራይዝ ላደርግህ ነበር..ግን አሁን ፀባይህን ሳየው አይገባህም››

‹‹አይኖቹ በሩ…ምንደነበር ልትሰጪኝ ያሰብሽው…?››
‹‹እስከዛሬ ሰጥቼህ የማላውቀውን››
በደስታ ተፍነከነከ …‹‹በአንድ አፍ….አንዴ አስበሽ ወስነሻል……. ትሰጪኛለሽ፡፡››
‹‹እስኪ እስከምሽቱ ያለህ ፀባይ ታይቶ …ምን አልባት?››አንጠልጥላ ተወችው፡፡
…በዚህ ጊዜ ስቴዲዬም ደርሰው ነበር ..ጊዬን ሆቴል በራፍ አካባቢ መኪናቸውን አቆሙና ደወሉላት..ቅርብ ስለነበረች መጥታ ተቀለቀለቻቸ….  ወደፒያሳ ነበር የነዳው፡፡


ይቀጥላል
2.2K viewsአትሮኖስ, 15:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-07 00:18:14 ከፍቶኛል
339 viewspetelare Stay true, 21:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-07 00:02:16
➠ለማመን የሚከብዱ እና ጨርቅዎን ጥለው እንዱያብዱ የሚያደርጉ አስገራሚ እውነታዎች የሚለቀቁበት ብቸኛው የ TELEGRAM ቻናል
═══════════════════
★በ አስገራሚ እውነታዎቻችን እየተዝናኑ እውቀት መጨበጥ ከፈለጉ ይቀላቀሉን JOIN US........

https://t.me/joinchat/5k6wNLiEV6k2YmY0
═══════════════════
572 viewspetelare Stay true, 21:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-06 09:00:57 አትሮኖስ pinned «#ባል_አስይዞ_ቁማር : : #ክፍል_ሀያ_አራት ፡ ፡ #በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ /// በማግስቱ ነው…እሷ ገንዳ ውስጥ ገብታ ትዋኛለች እሱ እየሠረቀ ይመለከታታል.. ‹‹ለምን ገብተህ አብረሀት አትዋኝም?" "አብረሀት ማለት?"ስኳር ሲሰርቅ እንደተያዘ ህፃን በርግጎ ጠየቃት፡፡ "እንዴ በአይንህ እኮ ዋጥካት" "ስርዓት ያዢ እንጂ… የራስሽው ጓደኛ መስላኝ?" "እሱማ እዚህ ከመምጣታችን በፊት ነዋ ..አሁንማ ቀማሀኝ..ለማንኛውም…»
06:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-06 09:00:42 ‹‹አልገባኝም…ታዲያ ይሄ ምኑ  ያስፈራል?››
‹‹ወይ ጉድ!! ስላላየኸው ነው…የሚናገር ሰው እኮ አሪፍ ነው ፡፡ጥፋትህን ወዲያውኑ ያወራርድልሀል..ይሄ ግን ውስጥህን በፀፀት ያከሰለዋል፡፡››
‹‹እሱማ አይቼዋለው እኮ በቀደም አብረን እንዳመሸን እረሳሺው እንዴ?››
‹‹አይ አረሳሁትም..ግን ቃልዬን ለማወቅ አንድ ምሽት አይደለም አንድ አመትም በቂ አደለም›› አለችው…
ልዩ ባለችበት ማጉረምረሟን ጀመረች‹‹በዚህ ንግግርሽ አልስማማም…እኔ ለምሳሌ ቃልዬን ነፍሱ ድረስ ዘልቄ ያወቅኩት አንድ ሰዓት በማይበልጥ ጊዜ ውስጥ ነው….በዛን ቀን እዛ ታክሲ ውስጥ ሞባይሉን ሰርቄ ከተያዝኩበት ጊዜ አንስቶ ሆስፒታል ወስዶኝ እስኪያሳክመኝ ባለው ጊዜ አብዛኛውን የቃልዬን ስብዕና የተረዳሁበት አጭር ግን ዘላለማዊ ያህል ዋጋ ያላቸው መጠነ ጊዜ ናቸው ፡፡ከዛ ወዲህ ያሉት ቀናትና ወራት በሙሉ እነዛን ስብዕናዎቹን ሚያወፍሩና የሚያዳብሩ ብቻ ናቸው……እና ቃልዬን ለመረዳት አመት እንዳማይፈጅ እኔ ምስክር ነች..ይሄን አንድ ቀን ለራስሽ እነግርሻለሁ፡፡›› ስትል ቃል ሰማትና ተደነቀ….ሁለቱ ሴቶች እሱን የሚረዱበት መንገድ እንዲህ መለያየቱ ፈገግ የሚያስብል ነው…‹‹የትኛዋ ነች ግን ትክክል?››ሲል እራሱን ጠየቀ..መልሱ ቀላል ስላልሆነ ጥያቄውን ብቻ በልብ ሰሌዳ ላይ  መዝግቦ ወደሁለቱ የምሽት ጫወታን ወደማመጥ  ተመለሰ፡፡
‹‹አሁን ስልኩን ለምንድነው ያላነሳሽለት?››
‹‹አንስቼ ምን እለዋለሁ….መኝታ ቤቴ ገብቼ  ተኝቸያለሁ ብዬ እዋሸዋለሁ ወይስ  ክፍሌ ውስጥ የጓደኛዬ ባል አስገብቼ አብሬው   ውስኪ እየጠጣሁ ነው ብዬ እውነቱን ነግዋለሁ?››
‹‹እሱን አላውላቅም ደግነቱ እሱም እኮ ከልቡ የደወለ አይመስለኝም….ስልኩ ጠርቶ ሳይጨርስ ነው ያቋረጠው፡፡››
‹አይ እሱ ኮዳችን ነው….ስልክ ደውሎ አራት ጥሪ ድረስ ካልተነሳ አልተመቸኝም ማለት ነው፡፡መልሼ እስክደውልለት ድረስ አይደውልልኝም፡፡››
‹‹እስከነገም ቢሆን?›
‹‹እስከ ሳምንትም ቢሆን አይደውልልኝም..ምን አልባት ድህንነቴ ካሳሰበው  መልዕክት ይልክ ይሆናል?››
ልዩ ፈገግ አለች..ፈገግ ያስባላት..አሁን ከተናገረችው ጋር  የመድህኔ የስለክ አጠቃቀም ልዩነት ትዝ ብሏት ነው የፈገገችው..፡፡ መድሀኔ  አንዴ መደወል ከጀመረ እስከምታነሳለት  ወይም ስልኩን ሙሉ ለሙሉ ዘግታ እስከምትገላገለው አያቆምም…በአንድ ቀን ውስጥ 98 ሚስኮል ስልኳ ላይ የተመዘገበበት ቀን አለ…..አስርና ሀያ…የተለመደ ነው፡፡ ይሄ ማለት ደግሞ ከቃል የስልክ አጠቃቀም ጋር የሰሜን ፖል እና ደቡብ ፖልን ያህል ተቃርኖ አለው ማለት ነው ስትል በንፅፅሩ ተገረመችና ትኩረቷን ወደነጊፊቲ መለሰች፡፡
‹‹ፍቅረኛሽ ነው ግን... ማለት አርግጠኛ ነሽ?››
‹‹እንግዲህ  እንደዘዛ እላለሁ››
በመልሷ በመገረም መሰለኝ መድሀኔ ከትከት ብሎ ሳቀና ‹‹እሱሱ  እንደዛ ይላል?›
‹‹ያው ለሁለተኛ ቀን ስትገናኙ   እራስህ ትጠይቀዋለህ››አለችው እንደማኩረፍ ብላ፡፡
በቃ ከዚሀ ወሬ እንውጣ አሁን ተኚ… ብሎ ከተቀመጠበት ተነሳና ጎንበስ ብሎ ጉንጯን ስሞት በራፍን ከፍቶ ወጣ….
በዚህ አይነት ሁኔታና እንዲህ በቀላሉ ከዛ ክፍል ይወጣል ብለው ቃልም ሆነ ልዩ አላሳቡም ነበር.. ጊፍቲም እራሷ  የመድህኔ ስንብት ከግምቶ ውጭ የሆነባት እንደሆነ ያስታውቃል… የሳማትን ጉንጮቾን በእጇ መዳፍ እያሻሸች….ከተቀመጠችት ተነሳችና በራፉን ቆለፈች..አልጋዋ ላይ ወጣችና አንሶላውን ገልጣ ገባች..ከዛ መብራቱን አጠፋች..ልዩም በንዴት ላፕቶፕን ስታጠፋ በዛኑ ቅፅበት ከቃል ኮምፒተር ጋር የነበረው ግንኙነት ተቋረጠ፡፡ ልዩ ለመተኛት መዘጋጀት ጀመረች፡፡በተመኘችው መጠን ጭን እስከመፈላቀቅ የሚደርስ ግንኙነት ላይ ባይደርሱም   ጥሩ መቀራረብና የስሜት መፈታተሸ ስላደረጉ ለመፅናናት ሞከረች፡፡

ይቀጥላል
906 viewsአትሮኖስ, 06:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-06 09:00:42 #ባል_አስይዞ_ቁማር
:
:
#ክፍል_ሀያ_አራት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///

በማግስቱ ነው…እሷ ገንዳ ውስጥ ገብታ ትዋኛለች እሱ እየሠረቀ ይመለከታታል..
‹‹ለምን ገብተህ አብረሀት አትዋኝም?"
"አብረሀት ማለት?"ስኳር ሲሰርቅ እንደተያዘ ህፃን በርግጎ ጠየቃት፡፡

"እንዴ በአይንህ እኮ ዋጥካት"

"ስርዓት ያዢ እንጂ… የራስሽው ጓደኛ መስላኝ?"

"እሱማ እዚህ ከመምጣታችን በፊት ነዋ ..አሁንማ ቀማሀኝ..ለማንኛውም ይመቻችሁ"አለችውና ከተቀመጠችበት ተነሳች፡፡ጉንጩን ሳመችውና መራመድ ጀመረች፡፡
ደንግጦ"እንዴ! ወዴት ነው?"

"እግሬን ላፍታታ"
‹‹ልከተልሻ"አለ ከመቀመጫው እንኳን ለመንቀሳቀስ ሳይሞክር

"አይ ብቻዬን ይሻለኛል ››

‹‹ እሺ እዚሁ እንጠብቅሻለን›› ብሎ ሸኛት...ደስ አለት።ደስ ያለት ተንኮል ስላሠበች ነው።

ትንሽ እራቅ እንዳለች እንዳያዮት ተጠንቅቃ በዛፍ ተከልላ ተጠማዘዘችና ወደመኝታ ክፍል አመራች፡፡ ...እንደደረሰች  ልብሷን ቀያየረች ።ሻንጣዋን አዘጋጅታ ።ከቦርሳዋ  ዘወትር እንደምታደርገው እነዛን የድመት አይን የመሰሉ ካሜራዎችን ድብቅ ቦታ አስተካክላ አስቀመጠች..ወደጊፊቲ ክፍል ስትሄድ ፅዳቷ እያጸዳች ነበር፡፡

‹‹…ይሄንን ቻርጅ ከጎደኛዬ ተውሼ ልመልስላት ነበር..››አለችና ዝም ብላ ገብታ ኮመዲኖ ላይ ቻርጁን አስቀመጠች… የእሷን እይታ በሰውነቷን ጋርዳ እዛው ኮመዲኖ አጠገብ ካለ የቴሌቪዥን ጠርዝ ላይ የካሜራውን አይን ለጠፈችው….መልሳ ቻርጀሩን አነሳችና‹‹እንደውም ሀሳቤን ቀየርኩ እስክትመጣ ብጠቀምበት ይሻላል›› ብላ ወጥታ ሄደች….ቀጥታ የመኪናውን ቁልፍ እያወዛወዘች ወደ መድሀኔ መኪና ነው ያመራችው..ከፈተችና ገባች… መኪናውን አስነስታ ኩሪፍቱን ለቃ ወጣች ።30 ደቂቃ ከነዳች በኃላ ስልኳን አወጣችና…፡፡
‹‹መኪናህን ይዤ ከጊቢ ወጥቼያለሁ ከሁለት ሰዓት በኃላ እመለሳለሁ ››ብላ መልዕክት ላከችለትና ስልኳን አጠፍችው።
////
አዲስአበባ ገብታ እቤቷ ከደረስች በኃላ ነበር. ስልኳን ስትከፍት ሰዓቱ አንድ ሰዓት አልፎ ነበር ..ከከፈተች ከአስር ደቂቃ በኃላ ተደወለላት።

‹‹አንቺ የት ነሽ?››

"እቤቴ›››

‹‹ ማለት?"

"እቤቴ ነዋ.. አዲስአበባ..."
" ግን ጤነኛ ነሽ...?ምን ሆንኩኝ ብለሽ ነው?"ከንዴቱ ብዛት ድምፁ እየተቆራረጠ እና እየተርገበገበ ነበር..፡፡
"ምንም ..አሰኘኝ አደረኩት ..ለማንኛውም ለሹፌርህ ነግሬልሀለው...አሁን እቤት መጥቶ መኪናህን ወስዷል …ጥዋት እስከሁለት ሰዓት ይደርስልሀል፡፡"

"በጣም ታበሳጪያለሽ…  እኔስ ይሁን አንዴ ፈርዶብኛል.. የሠው ሠው ከቤቷ አክለፍልፈሽ አምጥተሽ  ባዶ ሜዳ ላይ ጥለሻት ትሄጂያለሽ?››

"ባዶ ሜዳ ላይ አይደለም  አንተ ላይ ነው ጥያት የመጣሁት...አንተ ማለት ደግሞ እኔ ነህ...ምነው ተሳሳትኩ እንዴ?››
"አሽሟጠጥሽ ማለት ነው...በይ ቻው"ብሎ ጠረቀመባት ።

እሷ ግን ሁሉም ነገር በእቅዷ መሠረት እየሄደ ስለሆነ  ደስ አላት።
///
"ሶስት ሰዓት የጀመረች ይሄው እስከአራት ሰዓት ተኩል ላፓቶፖን  አስተካክላ ወደክፍላቸው እስኪገብ እየጠበቀች ነው። ‹‹ውይ ተመስገን››አለች…
የጊፍቲ ክፍል ተከፈተና ገባች ...የእሱም ተከፈተ ገባና ዘጋው።ልዩ መልሳ ተበሳጨች…፡፡እቅዴ አልሰራም ወይም ግምቶ ትክክል አልነበረም፡፡ በተለይ እስከእዚህን ሰዓት ድረስ ወደ ክፍላቸው ሳይመለሱ መቆየታቸው ተስፍ ሰጥቷት ነበር ፡፡እነሱ ግን ይሄው ጨዋነታቸውን እንደጠበቁ በየክፍላቸው ገቡ..፡፡ይሄ ጉዳይ ደግሞ ልዩን ተስፋ ሲያስቆርጣት …የእሷን ላፕቶፕ ሀክ በምድረግ እሷንም ሰደሬ ያሉትን እነጊፍቲንም እየተመለከተ ያለው ቃል ደግሞ ፈገግ አለ፡፡
ልዩ‹‹ቆይ ቆይ እስኪ… ››ብላ ትኩረቷን መድሀኔ ክፍል ውስጥ ትኩረት ደረገች፡፡ እሱ ላይ ምንም የመረጋጋት መንፈስ አይታይበትም፡፡ ዝም ብሎ ወለሉ ላይ ከወዲህ ወዲያ እየተመላለሠ ደቂቃዎችን አሳለፈ... ጊፍቲ ምንም የሚነበብባት የተለየ ስሜት የለም፡፡ ልብሷን አወለቀችና በፓንት ብቻ እርቃኗን ቆመች‹‹...ዋው ሰውነቷ ለእኔ ለሴቷም ያጓጓል..፡፡እርግጥ ከመጠን ትንሽ ተረፍረፍ ያለ ውፍረት ይታይባታል ቢሆንም ታምራለች፡፡››በማለት አድናቆቶን ተናገረች …ቃል ደግሞ በግማሽ ትኩረት የሚያውቀውን ገላ እየተመለከተ በገማሽ ቀልቡ ደግሞ የልዩን ጉሩምሩምታና መቁነጥነጥ እየታዘበ ቀጣዩን ትዕይንት ለማየት በጉጉት መከታተሉን ቀጠለ...
ጊፍቲ ከሻንጣዋ ውስጥ ሙሉ ቢጃማ ቀሚስ አወጣችና ለበሰች..ከዛ ሎሺን አወጣችና አልጋው ጠርዝ ላይ ቁጭ ብላ ከባቷ ጀምሮ ወደታች እግሮቾን መቀበባት ጀመረች...
መድህኔ  አሁንም ክፍሉ ውስጥ ሆኖ መንጎራደድን አላቆመም ..በውስጡ ከፍተኛ የሀሳብ ፍጭት እየተደረገ ይመስላል.. ድንገት እንደመባነን አለና ወደ ጠረጰዛው ሄደ ..ብዙም ያልተጠጣለት ብላክ ሌብል ውስኪ ነበር ..አንስቶ ያዘው..ትናንት ማታ ልዩ ይሄን መጠጥ ስለምትወድ  ለእሷ ብሎ ነበር  የገዛላት። ሊያንደቀድቀው ነው ብላ ስትጠብቅ ሁለት ብርጭቆ ይዞ ከክፍሉ ወጣ...የቃልም ሆነ የልዩ ልብ በየአሉበት ተንጠለጠለ… ሁለቱም የሚቀጥለውን ትዕይንት ለማየት ተነቃቁ ..የጊፍቲ ክፍል ተንኳኳ

"ማነው?"

"ጊፍቲ መድህኔ ነኝ"
ያለምንም ማቅማማት ቀልጠፍ ብላ ሄዳ ከፈተችለትና በራፍን ይዛ ቆመች..ከካሜራው ስለራቁ የሚያወሩት እየተሠማቸው አይደለም .ከደቂቃዎች ብኃላ ከበራፉ ገለል አለችና እሱን አስገባችው፡፡ በራፍን ዘግታ ወደነበረችበት የአልጋ ጠርዝ ተመልሳ ተቀመጠች...እሱ ውስኪውን ከነጠርሙሶቹ እንደያዘ ቆሟል።

‹‹እንዴ ቁጭ በል እንጂ?››

"እሺ"አለና በሁለቱም ብርጭቆ ቀዳና አንዱን አቀብሏት አንዱን ይዞ ከፊት ለፊቷ ያለ ደረቀ ወንበር ላይ ተቀመጠ...፡፡

"የጠጣሁት ወይን እራሱ አድክሞኛል..."

"አይዞሽ ምንም አይልሽ...ደግሞ አልጋሽ ላይ ነው ያለሽው ከደከመሽ ወደኃላ ክንብል ብሎ መተኛት ነው፡፡"

"እኔስ ክፍሌ ነኝ ክንብል ብዬ ተኛው...አንተስ በሰለም ወደቤትህ መግባትህን ቅድሚያ ማረጋገጥ የለብኝም?።››አለችው፡፡
"ለዛ አታስቢ  ..ከእዚህ ክፍሌ እስከሚደርስ ምን ያጋጥመዋል ብለሽ የምትሰጊ ከሆነ እዚሁ ከእግርሽ ስር እጥፍጥፍጥፍ ብዬ እተኛለሁ›› አላት፡፡
ጊፍቲ ከት ብላ የመገረም ሳቅ ሳቀች ."ይህቺ ጠጋ ጠጋ እቃ ለማንሳት ነው ...ሰውዬ በል ጠጣ ጠጣ አድርግና ወደ ክላስህ" አለችው ….
መልስ ሊመልስላት አፉን ሲከፍት የእሷ ስልክ ጠራ…እርብትብት አለች….መድህኔ  እየተከታተላት ነው…ስልኩን አላነሳችውም፡፡ ስልኩም እስከመጨረሻው ድረስ አልጠራም…በመሀከል ተቋራጠ፡፡ስልኩን የደወለው ቃል ነው..ይሄንን ያደረገው ሆነብሎ ስሜቱ እንደዛ እንዲያረግ ስለገፋፋው ነው፡፡
‹‹ወይ….በፈጣሪ!!›አለች፡፡
‹‹ምነው ?ማነው የደወለልሽ?››
ልዩም በላችበት ሆነ የዚህን ጥያቄ መልስ ለማወቅ ፈልጋ ነበር
‹‹ጓደኛዬ ነው፡፡››መለሰች ጊፍቲ፡፡
‹‹ጓደኛሽ ማለት ፍቅረኛሽ?››
‹‹በለው.. አዎ ፍቅረኛዬ››
‹‹ይሄን ያህል አደገኛ ነው እንዴ;?››
‹‹አዎ….ማለቴ ምንም ብታደርግ ምንም አይናገርህም…አያኮርፍህም ..አይቆጣህም..በቃ ዝም ብሎ ነው የሚያልፍህ››
879 viewsአትሮኖስ, 06:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ