2023-04-10 19:08:21
#ባል_አስይዞ_ቁማር
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
"ሰጥሀለው መጀመሪያ ልብስህን አውልቅ ..፡፡››አለችና ጎንበስ ብላ ጫማዋን አወለቀችለት ..ከዛ የሱሪውን ቀበቶ ፈታችና ቁልፍን ከፍተች… ዚፑን ወደታች በማንሸራተት ሁለቱን እግሮቹን ከታች በመያዝ እንደምንም እየጎተተች ከላይ እየሳበች ሱሪውን ከፓንቱ ጋር አንድ ላይ ሞሽልቃ አወለቀች…..እንዲህ ጨርቅ ሆኖ እንትኑ አደባባይ መሀል የቆመ የነፃነት ሀውልት ይመስላል....‹‹ልዩ ይሄን የመሰለ ዕቃ ለሌላ አሳልፈሽ ከመስጠትሽ በፊት አንዴ ብትጠቀሚው?››የሚል ሴጣናዊ ምክር የሆነ መንፈስ በጆሮዬ ሹክ አለባት። ጆሮዋን ደፈነችና ተልዕኮዋን ላይ አተኮረች...አሁን የቀረው ፓካውቱን ማውለቅ ነው ሙሉ በሙሉ አልጋው ላይ ወጣችና እንደምንም ታግላ አወለቅችለት.. አሁን ሙሉ እርቃኑን ቀርቷል..አልጋ ላይ ቆማ ከእግር ጥፍሩ እስከ ራስ ፀጉሩ በትኩረት አይኖቾን እያመላለስች አየችው፡፡ ወንድ ልጅን እንዲህ መለመላውን በአካል ስታይ የመጀመሪያ ጊዜዋ ነው። ጥሩ የተባለ የእስፓርተኛ ሰውነት ከተመጠነ ውፍረትና ቁመት ጋር ነው ያለው ..እንዲያም ሆኖ ግን የወንድ አካላዊ ቁመና እንደሴት ማራኪ አይደለም ስትል አብሰለሰለች። ‹‹አሁን ይሄን ማሰቢ ጊዜ ነው ?››እራሷን ገሰፅችና ወደሳሎን ተመለሰች...ጊፍቲ አሁን ድረስ ሙሉ በሙሉ እጅ አልሰጠችም" አሁንም የመጠጥ ብርጮቆዋን በእጇ እንደያዘች... እያላዘነች ነው፡፡
"ቃልዬ አሁን ናልኝ...ናና ሰውነቴን ዳብሰው...ናና ከንፈሬን ምጠጠው...ናና ጡቶቼን ጭመቃቸው...ናና ጭኖቼን ገነጣጥላቸው...ናና ..››
‹‹..ቃልዬን ፈልገሽው ነው?"
"አዎ ...ቃልዬን አምጪልኝ "
"ቃልዬን እንዳመጣልሽ...መጀመሪያ የያዝሽውን መጠጥ ጠጪ"
"መጠጥ ይሄው"
በአንድ ትንፋሽ ግልብጥ አደረገችው" ይሄው ጨረስኩ በያ አምጪልኝ"
"አመጣዋለሁ ..ግን ከአመጣሁት ትሰጪዎለሽ"
"ለቃልዬ..በደንብ ነዋ ...ለዛውም እንደፈለገው፡፡"
"እንቢ አልፈልግም ካለስ?"
"አንቺ ብቻ አምጪልኝ እንጂ በግድ ነው የምሰጠው..?"
‹‹እንግዲህ ተነሽ...ቃልዬ ልብሱን አወላልቆ ዝግጅ ሆኖ እየጠበቀሽ ነው...››
የእውነት ፈጥና መቀመጫዋን ለቃ ለመነሳት ብትሞክርም መቀመጫዋን ከሶፍው መላቀቅ አልቻለችም...ክንዷን ይዛ በመጎተት አስነሳቻትና እየጎተተች ማለት ይቻላል..ወደራሳቸው መኝታ ቤት ይዛት ገባች... መድህኔን ጠቅልላ እንዳስተኛችው ተኝቷል።
"የተኛ ሰው በማየቷ "ቃልዬ ነው እንዴ?"ስትል በተኮለታተፈ እና በተሰባበረ አረፍተ ነገር ጠየቀች፡፡
‹‹አዎ ግን በመስከርሽ እንዳይበሳጭ ድምፅሽን ቀንሺ አለቻት...በሁለት እጇ አፏን ፡አፈነች...አልጋው ጫፍ አስቀመጥኳት ‹‹...አሁን ልብስሽን ላውልቅልሽ..ተስማማሽ?›› ልክ እንደ መድህኔ እንዳደረገችው እያንዳንድን በሰውነቷ ላይ ያለውን ልብስ አወለቀችላትና መለመላዋን አስቀረቻት‹‹...ፐ ቅርፅ...›› በሚል አድናቆት እየጎተተች ከውስጥ አስገባቻት …እና ወደ ጆሮዋ ጠጋ ብላ ‹‹እንግዲህ እኔ ሄድኩልሽ ..ያው ቃልዬ በደንብ ስጪው" አለቻት፡፡፡
መዲህኔ ላይ እየተጣበቀችበት‹‹ እ…ሺ ››.አለችን
መብራቱን አጠፍችና ከአልጋው ወረደች ..ተራመደችና ከክፍሉ አልወጣችም፤ እዛው መግቢያ ላይ ወዳለ ሶፍ ሄደችና ጋደም አለች...ከዛ የሚፈጠረውን ነገር መከታተል ጀመረች...
"ቃል አንተ ተኛህ እንዴ...?››ጊፍቲ ነች መድሀኔን እየወዘወዘች ያለችው፡፡
"አለው ....ልዪዬ"በሰመመን ውስጥ ሆኗ መለሰላት፡፡
"ከዛ የመተሻሸት ድምፅ ተሰማ ..ልዩ የሞባይሏን መብራት አበራችና ወደእነሱ አተኮረች ..ጊፍቲ እላዪ ላይ ወጥታበት ጎንበስ ብላ ከንፈሩን እየላሰችው ነው...ወገቧን ጨምቆ ይዞታል‹‹...ከደቂቃዎች በፊት ሁለቱም ተዝለፍልፈው እሬሳ መስለው አልነበረ እንዴ?›› ስትል በመገረም በውስጧ ጠየቀች፡፡ እንዲህ ልትል የቻለችው አንደኛው አንደኛውን ሲጨምቅና አንደኛው አንደኛውን በጥንካሬ ሲያንከባልል በማየቷ ነው....ከላይ አልብሳቸው የነበረ አልጋ ልብስም ሆነ ብርድ ልብስ ከላያቸው ተንሸራቶ ወደመሬት ወደቀ...አሁን ሁሉ ነገር በግልፅ ይታያት ጀመር...ሲተሻሹ..ሲሳሳሙ እና ሲዋሰብ በቂ የሆነ ፎቶም ቪዲዬም ቀረፀቻቸው፡፡.
ከዛ እነሱ እስኪረኩ መታገስ ከብዷት መሬት ካዝረከረኩት ልብስ ብድርብሱን ትታላቸው አልጋልብሱን ወሰደችና እሱን ተከናንባ እዛው ሶፋ ላይ ተኝች‹‹..እስቲ ሌሎች ሶስት መኝታ ክፍሎች ነበሩ ለምን እዛ ሄጄ አልተኛሁም..?››ስትል ጠየቀች…ምክንያቱን ግን አታውቀውም ነበር፡፡ወዲያው ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ወሰዳት… ከእንቅልፏ ባና ሰዓቷን ሳታይ 12.10 ሆኖ ነበር..አይኗን አሻሽታ አልጋውን ስትመለከት ማመን አልቻለችም… ጊፍቲ መድሀኔ ክንድ ላይ ተንተርሳ አንደኛውን እግሩን ጭኖቾ መካከል ሰንቅሮ አንደኛውን ደግሞ ከላዬ ጭኖባት ጭልጥ ያለ እንቀለፍ ውስጥ ገብተው ያንኮራፋሉ… ማንኮራፋታቸው እራሱ ተራ በተራ ስለሆነ የራሱ የሆነ ስልተ ምት አለው….ከሶፋዋ ተነሳችና ቆመች.. .መኝታው ሰላልተመቻት ሰውነቷ ድቅቅ ብሏል…ተራመደች…ወደአልጋው ተጠጋችና እሪ ብላ ጩኸቷን ለቀቀችው……በመበርግ ሁለቱም ከእንቅልፋቸው ባነኑና ከተጣበቁበት ተላቀቁ፤ አንዴ እሷን አንዴ እርስ በረስ መተያየት ጀመሩ…፡፡
እሷ እንደድንቅ ብሄራዊ ተያትር ቤት ተዋናዬች ባጠናችውና በተዘጋጀችው መሰረት መድረኩን ተቆጠጣጠረችው፡
‹‹እንዴት እንዲህ ታደርጉኛላችሁ…ሰክራለች ብላችሁ እኔን ሶፋላ ላይ አስተኝታችሁ…?መድሀኒ ይሄ ለእኔ ይገባል.?››እራሷን ነጨች..ኸረ እንባዋ ሁሉ እየረገፈ ነው..መድሀኔ ተነስቶ ከአልጋው ወረደ… መለመላውን ሁለት ሴቶች ፊት ተገተረ….ጊፍቲ አንሶላውን ሰበሰበችና እርቃኖን ሸፈነች…ፊቷ በእፍረትና ግራ በመጋባት በአንዴ ሲገረጣ እየታየ ነው..
‹‹ልዩ ተረጋጊ …ምን እንደተፈጠረ በእውነት አላውቅም..››ወላል ላይ የተበታተነውን ልብሱን መሰብሰብ ጀመረ…ከመሀከል ፓንቱን እነሳና ለበሰ..፡፡
‹‹ሁለታችሁንም ከዛሬ ጀምሮ በአይኔ ማየት አልፈልግም….ያው ከመሀከላችሁ ወጥቼለሁ....እቤቱንም ተጋብታችሁ ልትኖሩበት ትችላላችሁ፡፡››
‹‹አረ ልዩ እንደዛ አይደለም…ይሄ ስህተት ነው››ጊፍቲ ነች እራሷን እንደምንም አበረታታ መናገር የጀመረችው፡፡
‹‹ምንም ስህተት አይደለም...እንደውም አሁን ሳስበው ይሄ ጉዳይ ከእኔም ሆነ ከቃል ጀርባ ሆናችሁ ስትፈፅሙት ዛሬ የመጀመሪያችሁ አይመስለኝም.››ነገሩን አንቦረቀቀችው፡፡
እንደ እብድ እየተወራጨችና እየተራገመች መኝታ ቤቱን ለቃ ወጣች፡፡ ሊለብስ ያዘጋጀውን ሱሪ በእጁ እንዳንከረፈፈ ሊከተላት ሞከረ….አልሰማችውም፡፡ ተንደርድራ ግቢውን ለቃ ወጣችና .ወዲያው ታክሲ ውስጥ ገባችና ከአካባቢው ተሰወረች…ስልኳን አጠፋችው፡፡
ቀጥታ ወደቤቷ ነው የሄደችው…..እናቷን እንኳን በቅጡ ሰላም ሳትል ወደ ክፍሏ ገባችና ከውስጥ ቀርቅሬ አልጋዋ ላይ ወጣች፡፡ድንግርግር ያለ ስሜት ነው እየተሰማት ያለው፡፡ ያሰበችውን ያህል ደስታ አልተሰማትም…ግን ቢሆንም ያሰበችውን በእቅዷ መሰረት ፈፅማዋለች....አሁን የሚቀራት ስህተቱን ተከትሎ መድህኔና ጊፊቲ ግንኙነታቸውን በዛው እንዲቀጥሉ ማድረግ ሲሆን በቀጣይነት ደግሞ ብቻውን የሚቀረውን ቃልን ብቻዋን ወደአለችው ወደራሷ ማምጣት…አዎ የመጨረሻ ግቧ ያ ነው፡፡አሁን መተኛት ስለፈለገች በአልጋ ልብሱ ሙሉ አካሏን ሸፈነች፡፡
ይቀጥላል
755 viewsአትሮኖስ, 16:08