2023-03-25 10:56:44
ዶናልድ ትራምፕ ከተከሰስኩ በአሜሪካ ሞትና ውድመት ይከሰታል ሲሉ አስፈራሩ
አወዛጋቢው የአሜሪካ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከተከሰስኩ በአሜሪካ ሞትና ውድመት ይከሰታል ሲሉ ማስፈራራታቸው ተሰምቷል።
ትራምፕ ከአንዲት ተዋናይት ጋር የነበራቸውን ግንኙነትን ለመደበቅ ገንዘብ ከፍለዋል በሚል ሊከሰሱ ይችላሉ ተብሏል።
የቀድሞ ፕሬዝዳንት እንደሚታሰሩ ከተነገረ ከአንድ ሳምንት ገደማ በኋላ በማህበራዊ ትስስር ገጽ ባስተላለፉት መልእክት ደጋፊዎቻቸው ለተቃውሚ እና ለአመጽ እንዲወጡ መግለጻቸው ይታወሳል።
ትራምፕ በተጨማሪም የማንሃተን አቃቤ ህግ ቢሮ እና ጉዳያቸውን የያዘው ዋና አቃቤ ህግ አልሺን ብራግ ላይ ተአጋጋሚ ዛቻዎችን ሲዘነዝሩ ነበረ ተብሏል።
በዚህም በኒውዮርክ፣ ዋሽንግተን ዲሲ እና ሎስ አንጀለስ ያለው የፖሊስ ኃይሎች ስምሪት መጠናከሩ ባለስልጣናት ገልጸዋል።
ትራምፕ በተባለው የወንጀል ድርጊት የሚከሰሱ ከሆነ በአሜሪካ የቀድሞ ፕሬዝዳንቶች ታሪክ በእንዲዘህ አይነት ቅሌት የተከሰሱ የመጀመሪያው መሪ መሆናቸው ነው፡፡
ለፈጣን መረጃዎች
ዩትዩብ: https://youtube.com/@Arifneger24
ቲክቶክ: https://www.tiktok.com/@arifneger24
ቴሌግራም: https://t.me/arifnegermedia
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/Arifnegermedia/
አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን!
212 views07:56