Get Mystery Box with random crypto!

Arif Neger

የቴሌግራም ቻናል አርማ arifnegermedia — Arif Neger A
የቴሌግራም ቻናል አርማ arifnegermedia — Arif Neger
የሰርጥ አድራሻ: @arifnegermedia
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 7.04K

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 13

2022-08-25 17:44:33
የእስራኤል እና የአሜሪካ F-35 የጦር ጄቶች በተደጋጋሚ ወደ ኢራን የአየር ክልል ሲዘልቁ መቆየታቸው ተሰማ፡፡

የእስራኤል እና የአሜሪካ የጦር ጄቶች በተደጋጋሚ በኢራን የራዳር ሥርዓት ሳይታዩ ወደ አገሪቱ የአየር ክልል በተደጋጋሚ እንደዘለቁ ዋይ ኔት በድረ ገጹ ፅፏል፡፡

አውሮፕላኖቹ በተደጋጋሚ ወደ ኢራን የአየር ክልል የዘለቁት በልምምድ በረራቸው መሆኑ ታውቋል፡፡

እስራኤል በተደጋጋሚ የኢራንን የኒኩሊየር ተቋማት የማደባየት እቅድ እንዳላት በግላጭ ስትናገር መቆየቷን ዘገባው አስታውሷል፡፡

የእስራኤል እና የአሜሪካ ሚስጥራዊ የጦር አውሮፕላኖች የበረራ ልምምድ ከዚሁ ጉዳይ ጋር ተያይዞ እየተነሳ ነው ተብሏል፡፡

ኢራን እና እስራኤል በቀጠናው በከፍተኛ የጠላትነት ስሜት የሚተያዩ አገሮች ናቸው፡፡

የኔነህ ከበደ

#ArifNeger

#Ethiopia #Ethiopiannews #ዜና #News

ለፈጣን መረጃዎች
ዩትዩብ: https://youtube.com/c/Addisnegertop10

ቲክቶክ: https://www.tiktok.com/@arifneger24

ኢንስታግራም: https://www.instagram.com/Arifneger

ቴሌግራም: https://t.me/arifnegermedia

ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/Arifnegermedia/

አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን!
1.4K views14:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 14:44:57
" አሁኑኑ የተሰረቀውን ነዳጅ መልሱ " - WFP

የዓለም ምግብ ፕሮግራም ዋና ዳይሬክተር ዴቪድ ቢዝሊ ድርጅታቸው ለእርዳታ ሥራው የሚያውለውን 570,000 ሊትር ነዳጅ " የትግራይ ባለሥልጣናት ሰርቀዋል " ብለዋል።

" ምግብ ለማድረስ ነዳጅ ከሌለን በሚሊዮኖች ይራባሉ " ያሉት ቢዝሊ ድርጊቱን " የሚያስቆጣ እና አሳፋሪ " ብለውታል።

አሁኑን የተሰረቀው ነዳጅ እንዲመለስ ጠይቀዋል።

#ArifNeger

#Ethiopia #Ethiopiannews #ዜና #News

ለፈጣን መረጃዎች
ዩትዩብ: https://youtube.com/c/Addisnegertop10

ቲክቶክ: https://www.tiktok.com/@arifneger24

ኢንስታግራም: https://www.instagram.com/Arifneger

ቴሌግራም: https://t.me/arifnegermedia

ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/Arifnegermedia/

አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን!
1.4K views11:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 14:44:48
"ህወሓት ዳግም ጦርነቱን የጀመረው ለጦርነቱ የሚያስፈልገውን ሀብት ከየት አግኝቶ ነው
" - ጋዜጠኛና ደራሲ አን ጋሪሰን

መሰረቷን በጀኔቫ ያደረገችው እና ለበርካታ መገናኛ ብዙኃን የምትሰራው አን ጋሪሰን የተሰኘች ጋዜጠኛ ህወሓት "ትግራይ ተከባለች፣ የሰብዓዊ እርዳታ እንዳይገባ ክልከላ ተደርጓል" የሚል ማደናገሪያ እያነሳ ባለበት ሰዓት፣ ጦርነቱን ዳግም ለመጀመር የሚያስችለውን ሀብት ከየት አግኝቶ ነው በሚል የተቃርኖ አመክንዮ በትዊተር ገጿ አንስታለች።

ጦርነት ውድ እና ያልተቋረጠ መሳሪያ፣ ተተኳሽ፣ ተሸከርካሪ፣ የምግብ አቅርቦት፣ የስለላ ቴክኖሎጂ እና ሌሎች አቅርቦቶች እንደሚፈልግ በመጥቀስ፣ "እነዚህ አስፈላጊ ግብዓቶችን ቡድኑ ከየት አገኛቸው?" ስትል ጥርጣሬ አዘል ጥያቄዋን አን ጋሪሰን አጋርታለች።

ትላንት አሸባሪው ህወሓት መቀሌ ከሚገኘው የዓለም ምግብ ድርጅት መጋዘን 570 ሺህ ሊትር ነዳጅ መዝረፉንና የሰብአዊ እርዳታ ስርጭቱን መስራት ከማይችልበት ደረጃ መድረሱን ተመድ መግለፁ ይታወሳል።


#ArifNeger

#Ethiopia #Ethiopiannews #ዜና #News

ለፈጣን መረጃዎች
ዩትዩብ: https://youtube.com/c/Addisnegertop10

ቲክቶክ: https://www.tiktok.com/@arifneger24

ኢንስታግራም: https://www.instagram.com/Arifneger

ቴሌግራም: https://t.me/arifnegermedia

ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/Arifnegermedia/

አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን!
1.3K views11:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 14:44:35
ዩክሬን ከሩሲያ ጋር እያደረገች ባለው ጦርነት 20 በመቶ ግዛቷን ማጣቷ ተገለጸ

የዩክሬን ሩሲያ ጦርነት
ዩክሬን በጦርነቱ 113 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ንብረት ወድሞባታል ተብሏል

ዩክሬን ከሩሲያ ጋር እያደረገች ባለው ጦርነት ከሉዓላዊ ግዛቷ 20 በመቶ የሚሆነውን ማጣቷ ተገልጿል።

በጦርነቱ ዩክሬን 20 በመቶ ግዛቷ በሩሲያ መወሰዱን ኒውዮርክ ታይምስ የዘገበ ሲሆን፤ በጦርነቱ ሳቢያ የሚፈናቀሉ ሰዎች ቁጥር መጨመሩም ተገልጿል።

ዩክሬን ካጣቻቸው ግዛቶቿ መካከል የዶኔስክ እና የሉሃንስ ግዛቶች ተጠቃሾች ሲሆን፤ ሩሲያ ግዛቶቹን ነጻ ሀገራት ናቸው የሚል ዕውቅና መስጠቷ ይታወሳል። ከዚህ ባለፈም ሩሲያ በግዛቶቹ ፓስፖርት መስጠቷም ይታወሳል።

በጦርነቱ እስካሁን 6 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሰዎች ስደተኛ መሆናቸውንም ነው የዓለም መገናኛ ብዙኃን የዘገቡት።

ስድስት ወራትን ባስቆጠረው በዚህ ውጊያ የደረሰው ሰብዓዊ ቀውስና የፋይናንስ መጠን ከሚታሰበውና ከሚገመተው በላይ እንደሆነም ነው የተገለጸው።

ከመጋቢት 24 ቀን 2022 ጀምሮ በተደረገው በዚህ ውጊያ 5 ሺ 587 የዩክሬን ዜጎች ህይወታቸው አልፍል ተብሏል። ምንም እንኳን የሟች ንጹሃን ቁጥር ከ 5 ሺ በላይ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን ትክክለኛ ቁጥሩ ግን ከዚህም ሊልቅ ይችላል ተብሏል።

ኒውዮርክ ታይምስ የስድስት ወራቱን ውጊያ በተመለከተ ባዘጋጀው ጹሑፍ ከዩክሬን ወታደሮች ይልቅ ብዙ የሩሲያ ወታደሮች መሞታቸውን ገልጿል።

ጄነራል ቫልሪ ዛሉዚኒ የተባሉ የዩክሬን ጦር መሪ ከሰሞኑ በሰጡት መግለጫ እስካሁን 9 ሺ ወታደሮች እንደተገደሉባቸው ጠቅሰዋል። ይሁንና ይህ ቁጥር በገለልተኛ አካል አልተረጋገጠም ተብሏል። 25 ሺ የሩሲያ ወታደሮች መገደላቸውን ኒውዮርክ ታይምስ ቢገልጽም ቁጥሩን ከየትኛው ምንጭ እንዳገኘው አልጠቀሰም።
1.2K views11:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ