Get Mystery Box with random crypto!

Arif Neger

የቴሌግራም ቻናል አርማ arifnegermedia — Arif Neger A
የቴሌግራም ቻናል አርማ arifnegermedia — Arif Neger
የሰርጥ አድራሻ: @arifnegermedia
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 7.04K

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 11

2023-01-25 01:59:10

797 views22:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-23 00:30:16
ሩሲያ አውሮፓን በስደተኞች የማጥለቅለቅ እቅድ መንደፏ ተገለጸ
እንደ ዓለም አቀፉ ስደተኞች ማዕከል ከሆነ ሩሲያ በፖላንድና ሉትንያ በኩል ስደተኞችን ወደ አውሮፓ ትልካለች ተብሏል

የሰሜን አፍሪካ እና መካከለኛው ምስራቅ ስደተኞች ወደ ሩሲያ በካሊኒንግራድ በኩል ወደ ሀገሯ እንዲገቡ ፈቅዳለች ተብሏል
ሩሲያ አውሮፓን በስደተኞች የማጥለቅለቅ እቅድ መንደፏ ተገለጸ።
ዓለም አቀፉ የስደተኞች ፖሊሲ ልማት ኢንስቲትዩት እንዳስታወቀው ሩሲያ አውሮፓን በስደተኞች የማጥለቅለቅ እቅድ እንዳላት ገልጿል።
ዩሮ ኒውስ የኢንስቲትዩቱን መግለጫ ዋቢ እንደዘገበው ከሆነ ሩሲያ በካሊኒንግራድ አውሮፕላን መረፊያ በኩል ስደተኞችን ወደ አውሮፓ እንዲገቡ ልታደርግ ትችላለች ተብሏል።
1.1K viewsedited  21:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-22 22:49:10

1.0K views19:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-22 12:39:57

1.2K views09:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-05 13:05:48 የሩስያን አዲስ ዘመቻ ተከትሎ ፖላንድ የመዘዘችው አንቀፅ አምስት


1.3K views10:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 11:05:43
ትራምፕ መኖሪያ ቤታቸው በኤፍ.ቢ.አይ ከተበረበረ ወዲህ የመጀመሪያ ንግግር አድርገዋል:: ዶናናድ ትራምፕ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን “የአሜሪካ ጠላት ነው” አሉ

የአሜሪካ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ
ጆ ባይደን “ጽንፈኛ” ያሏቸውን ዶናልድ ትራምፕን እና ደጋፊዎቻቸውን ማስጠንቀቀቸው ይታወሳል

የአሜሪካ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በስልጣን ላይ ያሉት ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን “የአሜሪካ ጠላት ናቸው” ማለታቸው ተደምጧል።

ዶናልድ ትራምፕ በፎሎሪዳ የሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው በኤፍ.ቢ.አይ ከተበረበረ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ለደጋፊዎቻቸው ንግግር አድርገዋል።

ትራምፕ በፔንሲልቫኒያ በተሰበሰቡ በሺዎች ለሚቆጠሩ ደጋፊዎቻቸው ባደረጉት ንግግር “የመኖሪያ ቤት ብርበራው በአሜሪካ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ስልጣንን ያለአግባብ መጠቀም ነው” ብለዋል።

የ76 ዓመቱ ዶናልድ ትራምፕ ሁለት ሰዓት በፈጀው ንግግራቸው በአብዛኛው በመኖሪያ ቤታቸው የተደረገውን ብርበራ በመተቸት የተጠናቀቀ ሲሆን፤ በኋላ ላይ የዴሞካራት ተቀናቃኛቸው የሆኑትን ጆ ባይደንን ወደ መተቸት ተመልሰዋል።

በንግግራቸውም በ2020 የተደረገው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ መጭበርበሩን እና አሸናፊነትን እንደነጠቁ መናገራቸውም ተሰምቷል።
#ArifNeger

#Ethiopia #Ethiopiannews #ዜና #News

ለፈጣን መረጃዎች
ዩትዩብ: https://youtube.com/c/Addisnegertop10

ቲክቶክ: https://www.tiktok.com/@arifneger24

ኢንስታግራም: https://www.instagram.com/Arifneger

ቴሌግራም: https://t.me/arifnegermedia

ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/Arifnegermedia/

አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን!
3.8K views08:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-03 22:29:00
ቱርክ በዩክሬኑ የዛፖሪዝሂያ ኒውክሌር ጣቢያ ግጭት ጉዳይ ማሸማገል ትችላለች- ፕሬዘዳንት ኤርዶሃን

ቱርክ በጦርነት ውስጥ ካሉት ዩክሬንና ሩሲያ ጋር መልካም የሚባል ወዳጅነት እንዳላት ይታወቃል

ቱርክ በዩክሬኑ የዛፖሪዝሂያ ኒውክሌር ጣቢያ ግጭት ጉዳይ መሸምገል ትችላለች ሲሉ ፕሬዘዳንት ረሲፕ ጣይብ ኤርዶሃን ተናገሩ፡፡

ፕሬዝዳንቱ ቱርክ የማሸማገል ሚናውን መጫወት እንደምትፈልግ ለሩሲያው አቻቻው ፑቲን እንዳሳወቁም ከቱርክ ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት የተገኘ መረጃን ዋቢ በማድረግ ኤኤፍፒ ዘግቧል፡፡

ኤርዶሃን ቱርክ፤ ሩሲያ እና ዩክሬን መካከል የዩክሬይንን የእህል ወደ ውጭ ገበያ ለማቅረብ የሚያስችል ታሪካዊ ስምምነት ላይ እንዲደርሱ ትልቅ ሚና እንደተጫወተች ሁሉ ፤አሁንም ትልቅ ሚና መጫወት ትችላለች ማለታቸውንም ተገልጿል፡፡

"ፕሬዝዳንት ኤርዶሃን ቱርክ በእህል ስምምነት ውስጥ እንዳደረጉት በዛፖሪዝሂያ የኑክሌር ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ውስጥ የአመቻችነት ሚና መጫወት እንደምትችል ተናግረዋል" ነው ያለው ፕሬዝዳንቱ ጽ/ቤት፡፡

ባለፈው ወር ከዩክሬን አቻቸው ቮሎዲሚር ዘሌንስኪ ጋር ለመነጋገር ወደ ኪቭ አቅንተው ነበሩት ኤርዶሃን፤ አሁን ላይ የዬክሬን-ሩሲያ የውጥረት ማዕከል የሆነውን የኒውክሌር ጣቢያ ጉዳይ ከባድ ጣጣ ሊስከትል የሚችል ጉዳይ መሆኑ ማስጠንቀቃቸው አይዘነጋም፡፡

ኤርዶሃን በወቅቱ" ተጨንቀናል፤ ሌላ ቼርኖቤል (እንደፈረንጆቹ በሚያዚያ 26 ቀን 1986 የተከሰተ አስደንጋጭ የኒውክሌር አደጋ) አንፈልግም” ማለታቸውም ሚታወስ ነው፡፡

እናም አሁን በአውሮፓ ትልቁ በሂነው የዛፖሪዝሂያ የኒውክሌር ጣቢያ ላይ ያለው ውጥረት እጅግ አሳሳቢ እየሆነ መምጣቱ ከፍተኛ ስጋት ፈጥሯል፡፡

#ArifNeger
3.1K views19:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 01:30:27
የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ቱርክ እና ሌሎችም አገራት ከአፍሪካ ጋር ሊያቀያይሙን አፍራሽ ፕሮፓጋንዳ እየነዙብን ነው ማለታቸውን ቱርክ አጥብቃ ነቀፈችው፡፡

የቱርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማክሮን እኛን ከመክሰስ አገራቸው በቅኝ አገዛዝ ዘመን የፈፀመቻቸውን ጥፋቶች ቢያርሙ ይሻላቸዋል የሚል መግለጫ ማውጣቱን ዴይሊ ሳባሕ ፅፏል፡፡

ማክሮን ከቱርክ በተጓዳኝ እንደ ሩሲያ እና ቻይና ያሉ አገሮች የፈረንሳይን ስም እያጠፉ ነው ያሏቸው አገሮች ናቸው፡፡

የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት በዚህ ጉዳይ ላይ የተናገሩት በአልጀሪያ የሰሞኑ ጉብኝታቸው ወቅት ነው ተብሏል፡፡

የማክሮንን አስተያየት በተመለከተ ከሩሲያ እና ከቻይና በኩል የተሰጠ ምላሽ በዘገባው አልተጠቀሰም፡፡

#ArifNeger

#Ethiopia #Ethiopiannews #ዜና #News

ለፈጣን መረጃዎች
ዩትዩብ: https://youtube.com/c/Addisnegertop10

ቲክቶክ: https://www.tiktok.com/@arifneger24

ኢንስታግራም: https://www.instagram.com/Arifneger

ቴሌግራም: https://t.me/arifnegermedia

ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/Arifnegermedia/

አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን!
3.2K views22:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 01:30:18
ታዋቂው ኢራቃዊ ፓለቲከኛ አል ሳድር፤ ራሱን ከፖለቲካው እንዳገለለ ማስታወቁን ተከትሎ በሃገሪቱ ከፍተኛ ውጥረት ነግሷል

የአል ሳድር ደጋፊዎች ቤተ መንግስት ሠብረው መግባታቸውን ተከትሎ በባግዳድ ሰዓት እላፊ ታውጇል

ኢራቃዊው የሺዓ እስልምና መሪ እና ፖለቲከኛ ሙቅታዳ አል ሳድር
አል ሳድር ጥቅምት ላይ የተካሄደውን ምርጫ ቢያሸንፍም መንግስት ለመመስረት አልቻለም

ኢራቃዊው የሺዓ እስልምና መሪ እና ፖለቲከኛ ሙቅታዳ አል ሳድር ራሱን ከፖለቲካው እንዳገለለ ማስታወቁን ተከትሎ በኢራቅ ከፍተኛ ህዝባዊ ቁጣ ተቀሰቀሰ።

በሺዎች የሚቆጠሩ የፖለቲከኛው ተከታዮች ውሳኔውን በመቃወም ወደ ብሔራዊ ቤተመንግሥት ሰብረው ገብተዋል። አዲስ ፕሬዝዳንት እና ጠቅላይ ሚኒስትር ለመሰየም ተሰብስቦ የነበረውን የሃገሪቱን ፓርላማም ተቆጣጥረዋል።

ይህን ተከትሎ በአስቸኳይ የካቢኔ ስብሰባ ላይ የነበሩት ጠቅላይ ሚኒስትር አል ካዲሚ ስብሰባውን በትነው ወጥተዋል። በቤተ መንግስቱ እና በአካባቢው ከባድ ጥበቃ እየተደረገም ሲሆን በባግዳድ ሰዓት እላፊ ታውጇል።

ስልጣን ባይዝም በፖለቲካ ተሳትፎው ረጅም ዓመታትን ያስቆጠረው አል ሳድር "በፖለቲካ ጉዳዮች ውስጥ ላለመግባባት ወስኛለሁ” በሚል ነበር ራሱን ከፖለቲካው ማግለሉን በይፋዊ የትዊተር የማህበረሰብ ትስስር ገጹ ያስታወቀው።

#ArifNeger

ለፈጣን መረጃዎች
ዩትዩብ: https://youtube.com/c/Addisnegertop10

ቲክቶክ: https://www.tiktok.com/@arifneger24

ኢንስታግራም: https://www.instagram.com/Arifneger

ቴሌግራም: https://t.me/arifnegermedia

ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/Arifnegermedia/
2.5K views22:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 16:23:18
በፖኪስታን በደረሰ የጎርፍ አደጋ የሟቾች ቁጥር ከአንድ ሺ አለፈ
እንዲሁም ከፓኪስታን ሰሜናዊ አካባቢዎች በሺዎች የሚቆጠሩ በትዕዛዝ መፈናቀላቸውን መንግስት ገልጿል

በፓኪስታን ከሰኔ ወር ጀምሮ በጎርፍ አደጋ የሞቱት ሰዎች ቁጥር 1ሺ33 መድረሱን የሀገሪቱ ብሔራዊ የአደጋ መከላከል ባለስልጣን ባወጣው አሃዛዊ መረጃ ያሳያል።

ከሰኔ ወር ጀምሮ የጣለው ከባድ ዝናብ ከ33 ሚሊዮን በላይ ዜጎች በማጥቃቱ በሀገሪቱ ባለፉት 24 ሰዓታት 119 ሰዎች መሞታቸውን ሲጂቲኤን ዘግቧል።

ከፓኪስታን ሰሜናዊ አካባቢዎች በሺዎች የሚቆጠሩ በትዕዛዝ መፈናቀላቸውን መንግስት ገልጿል።

በሀገሪቱ ደቡብ ምስራቅ ክልል ውስጥ የምትገኝ የሲንዲ ግዛት አንድ ባለስልጣን የጎርፍ መጥለቅለቁ ከፈረንጆቹ በ2010 ከነበረው የከፋ መሆኑን ጠቁመዋል።
ይህም በፓኪስታን ታሪክ ውስጥ እጅግ የከፋ የጎርፍ መጥለቅለቅ ተደርጎ ይቆጠር ነበር።

በፈረንጆቹ በ2010 በተከሰተው የጎርፍ አደጋ ቢያንስ 1,700 በፓኪስታን ገድለዋል ፣ አብዛኛዎቹ የሲንዲ ግዛት ነዋሪዎች ናቸው።
ባለፈው ረብኡ ቻይና 25,000 ድንኳኖችን እና የእርዳታ ቁሳቁሶችን ጨምሮ የአስቸኳይ ጊዜ ሰብአዊ ዕርዳታ ወዲያውኑ ልካለቸ

#ArifNeger

#Ethiopia #Ethiopiannews #ዜና #News

ለፈጣን መረጃዎች
ዩትዩብ: https://youtube.com/c/Addisnegertop10

ቲክቶክ: https://www.tiktok.com/@arifneger24

ኢንስታግራም: https://www.instagram.com/Arifneger

ቴሌግራም: https://t.me/arifnegermedia

ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/Arifnegermedia/

አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን!
2.2K views13:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ