Get Mystery Box with random crypto!

Alif media

የቴሌግራም ቻናል አርማ alif_media_1 — Alif media A
የቴሌግራም ቻናል አርማ alif_media_1 — Alif media
የሰርጥ አድራሻ: @alif_media_1
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.95K
የሰርጥ መግለጫ

አንብብ { አንብቢ }
ስታነብ ታሪክህን ታውቃለህ!
ስታነብ የስኬት ማማ ላይ ትወጣለህ!
ስታነብ ጉድለትህን ታውቃለህ!

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-28 21:38:54
ክብር ለ ሀገር መከላከያ ሰራዊት
328 views18:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 21:34:56 ሰበር መረጃ

ሠላምን ምረጥ ሲባል ውጊያን የመረጠው ህውሃት እየጨለመበት፣የትግራይ ህዝብ እየነጋለት ነው።ሽራሮ በሀገር መከላከያ ሰራዊት ቁጥጥር ስር ገብታለች
329 views18:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 21:33:38
ይህ ቃሪእ ማን ነው ስሙ የምታውቁ እስኪ ጠቆም አድርጉኝ
374 views18:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 20:58:44 አዲስ የሚከፍል telegram bot ተገናኝተዋል.
Invite በማረግ እና task በመስራት በነፃ ይከፍላል. ተጠቀሙበት.
Steps
1. Start bot
2.join chats
3.share phone number

Step ከላይ የፃፍኩት ነው በጣም ቀላል ነዉ ከ 15ብር ጀምሮ withdraw ማድረግ ይቻላል.



https://t.me/Ethiofree_birrbot?start=1486022879
216 views17:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 20:50:55 አዲስ የሚከፍል telegram bot ተገናኝተዋል.
Invite በማረግ እና task በመስራት በነፃ ይከፍላል. ተጠቀሙበት.
Steps
1. Start bot
2.join chats
3.share phone number

Step ከላይ የፃፍኩት ነው በጣም ቀላል ነዉ ከ 15ብር ጀምሮ withdraw ማድረግ ይቻላል.



https://t.me/Ethiofree_birrbot?start=1486022879
418 views17:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 14:37:06
ሰብአዊነት የሚባል ነገር የለም እንዴ እናንተየ

ሁለቱም ኢትዩጵያዊ
ሀለቱም በጎ የሰሩ

ነገር ግን የአንድ እምነት ብቻ ተለይቶ እውቅና መሰጠት ተገቢ አይደለም ።
327 views11:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 06:49:19 የታላቁ አዛኝ የአለም ነብይ ጣፋጭ ታሪክ

#ፀሀፊ_አብድልቃድር_እና---- #አንዋር

[ክፍል 5]

በካዕባ ግንባታ መሳተፋቸው

ካዕባ በአላህ ስም፣አላህን በብቸኝነት ለማምለክ የተገነባ የመጀመሪያው ቤት ነው።አባታችን ነብዩላህ ኢብራሂም(ዐ.ሰ) ከጣኦት አምልኮ ጋር ከፍተኛ ፍልሚያ ካደረጉ በኋላ ከአላህ በሆነ ትዕዛዝ ካእባን አነፁ።

وإذ يرفع إبراھيم القواعد من البيت وإسماعيل ربنا تقبل منا إنك أنت السميع العليم

" #ኢብራሒምና እስማኤልም 'ጌታችን ሆይ!ከእኛ ተቀበል።አንተ ሰሚውና አዋቂው ነህና' የሚሉ ሲሆኑ ከቤቱ መሰረቶቹን ከፍ ባደረጉ ጊዜ (አስታውስ)።"

( አል- በቀራህ 2፤127)

ካእባ ከዚህ በኋላ ለብዙ አደጋዎች ተጋልጠዋል።ነብያችን ﷺ በነብይነት ከመላካቸው ከጥቂት አመታት በፊት መካን ያጥለቀለቀው ሐይለኛ።ጎርፍ ይጠቀሳል።የአላህ መልዕክተኛ ﷺ በነብይነት ከመላካቸው በፊት ካዕባን ለማደስ በተደረገው ጥረት ላይ በንቃት ተሳትፈዋል፤በትከሻቸው ድንጋይ እየተቀበሉ ያቀብሉ እንደነበር ተዘግቧል።ያኔ እድሜያቸው 35 አመት እንደነበር ዘገባዎች ያመለክታሉ።

ቡኻሪ እንደዘገቡት ጃቢር ኢብን አብደላህ(ረ.ዐ) የሚከተለውን ሀዲስ አስተላልፈዋል፡-

لما بنيت الكعبت,ذھب النبي صلي الله عليه وسلم والعباس ينقلان الحجارت,فقال العباس للنبي صلي الله عليه وسلم:اجعل إزارك علي رقبتك,فخر علي الأرض وطمحت عيناه الي السماء فقال: أرني إزاري فشده عليه

"ካእባን በሚገነባ ጊዜ ነብዩ ﷺ እና አጎታቸው ዐብባስ (ረ.ዐ) ድንጋይ ያቀብሉ ነበር ዐብባስም ለነብዩ ﷺ "ሽርጥህን ከአንገትህ ላይ ደልድለህ ተሸከም" አሏቸው።ነብዩም ﷺ እንደተባሉት ሲያደርጉ ራሳቸውን #ስተው ወደቁ።ዐይናቸው ወደላይ ተንጋጠጠ።'ሽርጡን አቀብሉኝ'አሉና ከወገባቸው ላይ ታጠቁት።'

አላህ ይህን ያደረገው ሐፍረተ ገላቸውን ሌላ ሰው እንዳያየው ለመከላከል ነው።ይህ ክስተት እኚህ ሰው ለታላቅ ጉዳይ #የታጩ መሆናቸውን አመላካች ነው።

ጥቁሩን ድንጋይ ወደ ቦታው የመመለስን ክብር ለማግኘት በጎሳዎች መካከል የተነሳውን ውዝግብ በማፍታታቱ ሒደትም ነብያችን ﷺ ትልቅ ሚና ተጫውተዋል።ውዝግቡ ወደ ጦርነት ሊያመራ ተቃርቦ ነበር። የበኒ ዐብዱዳርና የበኒ ዐድይ ጎሳዎች በደም የተሞላ ገበታ አቅርበው ለክብራቸው በጋራ ለመፋለም እጃቸውን ከገበታው ውስጥ በማስገባት ቃል ተገባቡ።ቁረይሾች ውዝግቡን ለመፍታት ለአራት ወይም ለአምስት ቀናት ቢቀመጡም አልተሳካላቸውም። በመጨረሻም አቡ ኡመያህ አል-መኽዙሚ የተባለ ሰው፡- "ወገኖቼ ሆይ! አትወዛገቡ።ሁላችሁም የተስማሙበትን ሰው ዳኛ አድርጉ" ሲል ሀሳብ አቀረበ። "በተቀደሰው ካእባ በር መጀመሪያ ለሚገባው ሰው ዳኝነት እናድራለን" ሲሉም ተስማሙ።ያ ሰው ታማኙ ሙሐመድ ﷺ ሆኑ።" ይህ ታማኝ የሚሰጠንን ብይንስ በደስታ እንቀበላለን"አሉ።ጉዳዩን አጫወቷቸው። እርሳቸውም ኩታቸውን ዘረጉ።ሁሉም ጎሳዎች የኩታውን ጫፍ እንዲይዙ አዘዙ።ድንጋዩን አነሱና ከኩታቸው ላይ አስቀመጡት።እንዲያነሱም አዘዟቸው።ከሚቀመጥበት ቦታ ላይ ሲደርስ እርሳቸው ድንጋዩን ያዙና አስቀመጡት።ይህ ክስተት የነብዩን አዎንታዊ ስብእና፣ጥበባቸውንና የላቀ ደረጃቸውን ያሳያል።ታዲያ ወገኖቻቸው መልዕክታቸውን ላለመቀበል ለምን ያን ያህል አንገራገሩ።

የአላህ መልክተኛ ﷺ ተቀጣጥሎ የነበረውን የጦርነት እሳት ማጥፋታቸው አራት እውነታዎችን ይከስትልናል፡-

አዎንታዊነት የነብዩ ሙሐመድ ﷺ ስብዕና መሰረታዊ አካል ነው።በካዕባ ግንባታም ሆነ በሌሎች የማሕበረሰባቸው ጉዳዮች ላይ ያሳዩት የነበረው የላቀ ተሳትፎ ከዚህ ባህሪያቸው የመነጨ ነው።

ጉዳዮችን የሚያስኬዱበትን፣ችግሮችን የሚፈቱበትን እጅግ አስደናቂ ጥበብ ያሳያል።በተለይም ይህን ጥበብ የከበረ የሽምግልና ሒደት ያከናወኑት በመካከላቸው ውዝግብ በተነሱባቸው አጋጣሚዎች ሁሉ ብዙ ደም ከመፍሰሱ በፊት እርቅ በሚያወርዱ ጎሳዎች መሀል መሆኑ ደግሞ ለድርጊታቸው የበለጠ ድምቀት ይሰጠዋል።

ከቁረይሾች ዘንድ የነበራቸውን የላቀ የክብር ደረጃ ያመላክታል።"ታማኙ"(አል-አሚን) በሚል ማዕረግ ይጠሯቸው ነበር።

ከአላህ ዘንድ መልዕክት ወርዶላቸው እርሱን ማድረስ በጀመሩ ጊዜ የነዚህ ወገኖቻቸው ልቦች በክህደት መሞላታቸው፣በማስተባበልና በማወክ ጥሪያቸውን ማስተናገዳቸው በጣም ያስገርማል።በየትኛውም ቦታና ዘመን የሚገኙ የእውነት ተጣሪዎችን የሚቀናቀኑ ወንጀሎችን እኩይ ባህሪም በጉልህ ያሳያልልልልልልል።


ይህን የነብያችንን ﷺ ትልቅ ታሪክ አንብበን ስንጨርስ እኛ ጋር ብቻ እንዲቀመጥ ሳንፈቅድ ላላወቁትና ላልሰሙት ይህን ውድ ታሪክ እንድናሰማ ትልቅ አማና ጥለንባችሗል።

@Alif_media_1

ይ ላ ሉን
383 views03:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 20:25:06 ይህን ቻናል የሚቆጣጠር ጀግና ማነው @Muh_ali_bot
430 views17:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 09:03:00 የታላቁ አዛኝ የአለም ነብይ ጣፋጭ ታሪክ
•════••• •••════•

[ክፍል 4]



እመት ኸዲጃን ማግባታቸው
••┈┈┈┈••✦✿✦••┈┈┈┈••

ኢብን ሂሻም እንደዘገቡት ኸዲጃ (ረ.ዐ) ማሕበራዊ ክብር እና ሃብት የነበራት ነጋዴ እንስት ናት። ወንዶችን በሽርክና ታስነግዳለች። የአላህን መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ሐቀኝነትና ታማኝነት እንዲሁም መልካም ስብእና ስትሰማ ወደርሳቸው መልእክት በመላክ ገንዘቧን ይዘው ለንግደ ወደ ሻም እንዲሄዱ ጠየቀቻቸው። ለሌሎች ከምትሰጠው በላይ ገንዘብም ልትሰጣቸውና መይሰራህ የተባለ አገልጋይዋን ከርሳቸው ጋር ልትልክ ቃል ገባች።

ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) ጥያቄዋን ተቀበሉ። ገንዘቧንም ይዘው ከአገልጋይዋ ከመይሰራህ ጋር ወደ ሻም ተጓዙ። ጉዟቸው የተሳካ ነበር። እጥፍ ድርብ ትርፍ ይዘው ወደ ኸዲጃ ተመለሱ። ገንዘቡንም በታማኝነት አስረከቡ። መይሰራህ የነቢዩን (ሰ.ዐ.ወ) መልካም ስብእናና ውብ ባህሪ ሲያይ ልቦናው በአድናቆትና በክብር ተሞላ። ያየውንም ለኸዲጃ አወጋት። እርሷም በነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) ታማኝነት ተደነቀኝ። በርሳቸው ሰበብ ያገኘችው በረከትም ሳያስገርማት አልቀረም፡፡ ይህ ሁኔታ ለጋብቻ እንድትጠይቃቸው አነሳሳት። ሐሳቧን አቀረበችላቸው። እርሳቸውም ተቀበሏት። አጎቷን ዐምር ኢቢን አሰድን በአጎታቸው በአቡ ጧሊብ በኩል አስጠየቁ። አቡ ጧሊብ የጋብቻ ጥያቄውን ያቀረቡት በሚከተለው ንግግር ነበር፡-

الحمد لله الذي جعلنا من ذرية إبراهيم، وجعلنا حضنة بيته، وجعلنا خدام الناس ثم إن ابن أخي هذا محمد بن عبد الله لا يوزن به رجل (إلا رجح به) شرفًا ونبلاً وفضلاً (وعقلاً) وإن كان في المال قلاًّ (أي فقيرًا) فإن المال ظل زائل وأمر حائل وعارية مسترجعة، وهو والله بعد هذا له نبأ عظيم وخطر جليل وقد خطب إليكم رغبة في كريمتكم خديجة وقد بذل لها من الصداق (كذا)….،

“የኢብራሂም ዝርያ፣ የቤቱ ጠባቂ፣ የሐጃጆች አገልጋይ ላደረገን አምላክ ምስጋና ይድረሰው። ይህ የወንድሜ ልጅ ሙሐመድ በገንዘብ በኩል ድሃ ቢሆንም በመልካም ስብእናና በአስተዋይነት ከየትኛውም ወንድ ሚዛን ይደፋል። ገንዘብ ደግሞ አላፊና ጠፊ ነገር ነው። ከዚህ በተጨማሪም ሙሐመድ ታላቅ እድል ያለው ሰው ነው። ልቅናችሁን በመሻትም ኸዲጃን ለጋብቻ ጠይቋታል። ይህን ያህል ጥሎሽም ይጥላል።”

የኸዲጃ ቤተሰቦች ተስማሙ። ጋበቻውም ተፈጸመ። ያኔ የርሳቸው እድሜ 25 ዓመት ሲሆን፣ የርሷ ደግሞ 40 ዓመት ነበር። ኸዲጃ እርሳቸውን ከማግባቷ በፊት ሁለት ባሎችን አግብታ ፈትታለች።

መሠረት-አልባ ሂስ
• ┈•✿ ✿•┈ •

ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) ከኸዲጃ (ረ.ዐ) ጋር ያደረጉት ጋብቻ ለስጋዊ ሐሴት ብዙም ትኩረት የማይሰጡ እንደነበሩ ያመለክታል። እንደሌሎች የእድሜ እኩዮቻቸው ወጣቶች ስጋዊ ደስታን የሚሹ ቢሆን ኖሮ በእድሜ ከርሳቸው የምታንስ፣ ቢያንስ ቢያንስ የእድሜ እኩያቻውን ያገቡ ነበር። እርሷን ለማግባት የወሰኑት ክብሯንና መልካም ስብእናዋን ተመልክተው ነበር። በዘመነ መሐይምነት ንጹህና ከአጓጉል ድርጊት የተጠበቀች እንደነበረች ተመስክሮላታል። (የአንተም የትዳር ጓደኛ ምርጫ የነብይህን አርአያነት የተከተለ ይሁን።)

ይህ ጋብቻ እመት ኸዲጃ (ረ.ዐ) በ56 ዓመት እድሜያቸው እስከሞቱበት እለት ድረስ ቀጥሏል። ነቢዩም (ሰ.ዐ.ወ) ሌላ ሴት የማግባት ሐሳብ ሳይኖራቸው እድሚያቸው 50ዎቹን ተሻገረ። ወንድ ልጅ ብርቱ የወሲብ ፍላጎቱን ለማርካት ሲል ብዙ ሚስቶችን ለማግባት የሚከጅለው ከ25-50 ባለው የእድሜ ክልል ውስጥ መሆኑ ይታወቃል።

ነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) በኸዲጃ (ረ.ዐ) ላይ ሌላ ሴት የመደረብ ሐሳብ ሳያድርባቸው ይህን የእድሜ ክልል አለፉ። ቢፈልጉ ኖሮ በርካታ እንስቶችን ያገኙ ነበር። የሕብረተሰቡ ባህልም ይደግፋቸውዋል። ኸዲጃ (ረ.ዐ) አግብታ የፈታች እና በእድሜም የርሳቸው እጥፍ ልትባል የምትችል ሆና እያለ ቢያገቧትም ከርሷ ጋር ሌላ እንስት ሳያገቡ አብረዋት ኖረዋል። ይህ እውነታ ለእስልምና የበረታ ጥላቻ ያላቸው ሚሽነሪዎችና ኦሪየነታሊስቶች፣ እንዲሁም የነርሱ አገልጋይ፣ የአስተሳሰባቸው አቀንቃኝ የሆኑ አምላክ የለሾችና ዓለማዊያን የሚሰነዝሩትን ክስ ባዶ የሚያስቀር ነው። እነዚህ ወገኖች የአላህን መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ጾታዊ ስሜት ያጠቃቸው አድርገው ለመሳል ጥረዋል። ዓላማቸው እውነትን መፈለግ ሳይሆን እምነትን ማናጋት፣ የርሳቸውን አርአያነት ጥላሸት መቀባትና የወሲብ ስሜትን እሳት ማቀጣጠል በመሆኑ ሂሳቸው አያስገርምም።

ለስጋዊ ስሜቱ ተገዥ የሆነ ሰው እንደ ዐረቢያ ባለ በብክለት የተከበበ ክልል ውስጥ እየኖረ፣ በዙሪያው በሚተራመሰው የብክለት ማእበል ሳይሳብ እስከ 25 ዓመት እድሜው ንጹህና ጥብቅ ሆኖ ሊኖር አይችልም። ከዚያ በኋላም በእጥፍ እድሜ የምትበልጠውን ፈት ሴት ለማግባት፣ ብሎም በዙሪያው ወዳሉ በርካታ እንስቶች አይኑን ሳይጥል፣ የፈለጋትን ሴት ለማግኘት ያለውን ሰፊ እድል ሳይጠቀም እድሜውን ሙሉ ከአዛውንት ሚስቱ ጋር ለመኖር አይፈቅድም።

ከኸዲጃ (ረ.ዐ) ሕልፈት በኋላ ዓኢሻን (ረ.ዐ) እና ሌሎች እንስቶችን ማግባታቸው በነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ልቅናና በምሉእ ባህሪያቸው ላይ ያለንን እምነት የሚያጠናክሩ ሰበቦችንና ጥበቦችን ያዘሉ ናቸው። የጋብቻዎች ምክንያቶች ምንም ይሁኑ ምን የእስልምና ጠላቶች እንደሚያናፍሱት ስጋዊ ስሜቱን ለማስተናገድ ሊሆን ፈጽሞ አይችሉም። ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) ይህ ፍላጎት ቢኖራቸው ኖሮ ሊያስተናግዱበት በሚችሉበት ተፈጥሯዊ ጊዜ ባስተናገዱት ነበር። በዚያ ላይ ያኔ ከየትኛውም ሐሳብና ሐላፊነት ነጻ ስለነበሩ ይህን ጥሪ ለማስተናገድ እንቅፋት የሚሆናቸው ነገር አልነበረም።



ይቀጥላል ያ ጀመአ
517 views06:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-21 21:01:41 የታላቁ አዛኝ የአለም ነብይ ጣፋጭ ታሪክ



የፉጅጃር ጦርነትና የፈዱል ስምምነት

[ክፍል3]

ነብዩ ﷺ እድሜያቸው 14 ሲሞላ "ሐርበል ፉጅጃር" በተባለው ጦርነት ላይ ተሳተፉ።

የኪናናህና የቁረይሽ ጎሳ በአንድ ወገን፣የቀይስ ጎሳ በሌላ ወገን ተሰልፈው ያደረጉት ጦርነት ነው።ለአረቦችም እጅግ አስፈሪ ጦርነት ነበር።

የተቀደሰችውን የመካን ከተማ ክብር የገረሰሰ ስለነበር እለቱ"የውመል ፉጅጃር"(የአመፅ ቀን) ተባለ።

የአላህ መልዕክተኛ ﷺ እንዲህ ሲሉ ተናግረዋል፡-በዚህ ጦርነት ላይ ለአጎቶቼ ቀስት እየሰበሰብኩ አቀብል ነበር።"ያኔ የ 14 ወይም የ15 አመት ልጅ እንደነበሩ ከፊል ዘገባዎች ያመላክታሉ።

ሌሎች ደግሞ የ20 አመት ልጅ መሆናቸውን ዘግበዋል።የመጀመሪያው ሀሳብ ሚዛን ይደፋል። ምክንያቱም በጦርነቱ ወቅት የነበራቸው ሚና ቀስት እየሰበሰቡ ማቀበል መሆኑ ልጅ እግር እንደነበሩ ያመለክታል። ይህ ተሳትፎ ከልጅነታቸው ጀምሮ ጀግንነትን እንዲማሩና የውጊያ ልምድ እንዲቀስሙ አደረጋቸው። ይህ ጦርነት እንደሌሎች የአረብ ጦርነቶች ሁሉ በኢምንት ምክንያት የተነሳ ነው።ከዚያም የዘረኝነት እሳት አቀጣጠለው።የኢስላም ብርሀን ልቦናዎቻቸውን አስማምቶ ይህን ጥመት እስኪያስወግድላቸው ድረስ እንደዚሁ ነበሩ።

ቁረይሾች ከፉጅጃር ጦርነት እንደተመለሱ "ፈዱል" የተባለውን ስምምነት ለማድረግ ተጠራሩ። ስምምነቱ ከቁረይሽ ባለቤቶች መካከል አንዱ በነበረው በጀድአን ቢን ተይሚ ቤት ውስጥ ተፈፀመ።የስምምነቱ ይዘት መካ ውስጥ ተበድሎ ያገኙትን ማንኛውም ሰው የከተማዋ ነዋሪ ይሁንም አይሁን ከጎኑ ቆመው በደሉን ለማካካስ የተስማሙበት ነበር።የአላህ መልዕክተኛ ﷺ ከአጎቶቻቸው ጋር በመሆን በስምምነቱ ላይ ተስማምተዋል።

አላህ በመልዕክተኝነት ከላካቸው በኋላ እንዲህ ሲሉ ተደምጠዋል፡-

لقد شهدت مع عمومتي حلفا في دار عبدالله بن جدعان ما أحب ان لي به حمر النعم ولو دعيت به في الإسلام لأجبت

《"በአብደላህ ኢብን ጀድአን ቤት ውስጥ
በተደረገው ስምምነት ላይ ተገኝቻለው።ከዚያ ሳልገኝ ቀርቼ በልዋጩ ቀይ ግመል ቢሰጠኝ የምመርጥ አይደለሁ።በእስልምና ውስጥ ሆኜም ወደዚያ ስምምነት ብጋበዝ ግብዣውን እቀበላለሁ።"》

ምክንያቱም እርሳቸው የተላኩት መልካም ስነ-ምግባራትን ለማሟላት ነው።የስምምነቱ ይዘቱም የመልካም ስነ-ምግባር አካል ነው።ኢስላም የስምምነቱን አብይ ይዘት ያፀድቃል።ይህ ስምምነት በርካታ ሰዎችን ከበደል ታድጓል።

ከ"ሒልፈል ፉዱል" ስምምነት ከምናገኛቸው ትምህርቶች መካከል ዋነኛው፡- "ከተበዳይ ጎን መቆምና በደሉን ማካካስ ነው"።

ውድ አንባቢያን!!!! በዚህ ረገድ የሚወሳ የግል ተሞክሮ አለህን???????

የምን አንብቦ ዝም ነው ፤

🅢🅗🅐🅡🅔 🅛🅘🅚🅔 🅙🅞🅘🅝

በማድረግ ላላወቁት እናሳውቅ።

@𝙋𝘼𝙍𝙏
---------------ይ --------------------ቀ -------------------------ጥ -------------------------------ላ -------------------------------------ል

ክፍል 3 #ይቀጥላል.........


@Alif_media_1 @Alif_media_1
@Alif_media_1

ይ ላ ሉን

@Alif_media_1
599 views18:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ