Get Mystery Box with random crypto!

አዲስ ነገር መረጃ

የቴሌግራም ቻናል አርማ addis_news — አዲስ ነገር መረጃ
የቴሌግራም ቻናል አርማ addis_news — አዲስ ነገር መረጃ
የሰርጥ አድራሻ: @addis_news
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 76.12K
የሰርጥ መግለጫ

አዲስ ነገር መረጃዎች
መረጃዎች በትኩሱ ና ሳይዉሉ እንዲሁም ሳያድሩ በቻናሉ በኩል ይደርሳሉ
ለአስተያየት እና ለማስታወቂያ ስራዎች 👇👇
@Addisnegermereja_bot

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 13

2023-05-13 11:45:36
ምርጫ ቦርድ የሕወሓትን ሕጋዊ ሰውነት ሥረዛ ይነሣልኝ ጥያቄ ውድቅ አደረገ!

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ቀደም ሲል በሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ሕ.ወ.ሓ.ት) ላይ ያስተላለፈውን የፓርቲውን ሕጋዊ ሰውነት ሥረዛ ፓርቲው ይነሣልኝ ሲል ያቀረበውን ጥያቄ ቦርዱ ውድቅ ያደረገበት ደብዳቤ ከላይ ተያይዟል።

@Addis_News
@Addis_News
4.5K views08:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-13 11:45:33
4.2K views08:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-13 09:08:07
ኤሎን መስክ ለትዊተር አዲስ ዋና ሥራ አሥፈጻሚ ሾሙ!

ኤሎን መስክ ሊንዳ ያካሪኖን አዲሷ የትዊተር ዋና ሥራ አሥፈጻሚ አድርገው ሾመዋቸዋል፡፡

የጣሊያን የዘር ሐረግ ያላቸው የ63 ዓመቷ ሊንዳ ያካሪኖ ÷ በትዊተር ኩባንያ ውስጥ በዋናነት በንግድ ሥራዎች ላይ ትኩረት አድርገው እንደሚሠሩ ኤሎን መስክ አስታውቀዋል።

እርሳቸው ደግሞ በምርት ዲዛይን እና አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ማዳበር ላይ እንደሚያተኩሩ አመላክተዋል። የቀድሞው ዋና ሥራ አስፈጻሚ አያይዘውም በኩባንያው ውስጥ የሚኖራቸው ሚና ዋና የቴክኖሎጂ ኃላፊነት መሆኑን ጠቁመዋል።

 @Addis_News
@Addis_News
6.7K views06:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-13 09:05:18 ኢትዮጵያ የብርን የመግዛት አቅም ማዳከሟ አይቀሬ መሆኑን ኢኮኖሚስቶች ተናገሩ!!

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እንደ ሀገር የገጠመውን የውጭ ምንዛሬ እጥረትን ለመፍታት በሚል በየጊዜው የተለያዩ እርምጃዎችን ሲወስድ ቆይቷል።

የወጪ ንግድን ለማበረታታት እና የውጭ ምንዛሬ እጥረትን ለመፍታት እንደ መፍትሔ ሲወሰድ የቆየው የብርን የመግዛት አቅም ማዳከም አንዱ ነው። ለአብነትም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ወደ ስልጣን በመጡበት ወቅት አንድ የአሜሪካ ዶላር 27 ብር ገደማ የነበረ ሲሆን አሁን ላይ በባንኮች 54 ነጥብ 2 ብር በመመንዘር ላይ ሲሆን በጥቁር ገበያ ደግሞ እስከ110 ብር ድረስ እየተመነዘረ ይገኛል።

መንግስት በጦርነት እና ኮሮና ቫይረስ የተጎዳውን ኢኮኖሚ እንዲያገግም ከዓለም አቀፍ የገንዘብ አበዳሪ ተቋማት ብድር እና እርዳታ ለማግኘት ጥረት ላይ እንደሆኑ ይገለጻል። በቅርቡም የአይኤምኤፍ ባለሙያዎች በአዲስ አበባ ከመንግስት ከፍተኛ ባለሙያዎች እና አመራሮች ጋር በአዲስ አበባ እና በዋሸንግተን ውይይት ማድረጋቸው ና ጥሩ መግባባቶች ላይ ተደርሷል ማለታቸው ይታወሳል። ይህን ውይይት ተከትሎም ዓለም ባንክ እና አይኤምኤፍ የኢትዮጵያ መንግስት የውጭ ምንዛሬ ተመንን በጥቁር ገበያ ካለው ምንዛሬ ተመን ጋር እኩል እንዲያደርጉ ምክረ ሀሳብ እንዳቀረቡ ሮይተርስ ዘግቧል።


አል ዐይን አማርኛ በጉዳዩ ዙሪያ የኢትዮጵያ መንግስት ከውጭ ምንዛሬ ተመን እና እጠረቱ ጋር በተያያዘ የምጣኔ ሀብት ባለሙያዎችን አነጋግሯል።

ዶክተር ሽመልስ አርአያ በማክሮ ኢኮኖሚክስ ጉዳዮች ዙሪያ አማካሪ እና የጥናት ባለሙያ ናቸው፤ እሳቸው እንደሚሉት ከሆነ የኢትዮጵያ መንግስት ከመቼውም ጊዜ በላይ የውጭ ምንዛሬ እጥረት ገጥሞታል።

እጥረቱን ተከትሎም መንግስት የብርን የመግዛት አቅም ማዳከሙ አይቀሬ ነው፣ እነ ዓለም ባንክም ብዙ ቅድመ ሁኔታዎችን ያስቀመጡት ኢትዮጵያ ያለባትን እጥረት መጠን ስለሚያውቁ ጭምር መሆኑንም ዶክተር ሽመልስ አክለዋል።

ዓለም ባንክ አሁን ያለው የዓለም ኢኮኖሚ ስርዓት እንዲቀጥል ይፈልጋል ያሉት ዶክተር ሽመልስ ስርዓቱ እንዲቀጥል ደግሞ ሀብታም ሀገራት ሀብታም ሆነው እንዲቀጥሉ የግድ ድሃ ሀገራት ከድህነታቸው እንዲወጡ አይፈለግም ብለዋል።በብዙ ጉዳዮች እየተፈተነ ያለው የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የገጠመውን የውጭ ምንዛሬ ተመን ለመፍታት ሲል መንግስት ብድር እና ሌሎች የገንዘብ ድጋፎችን ለማግኘት የብርን የመግዛት አቅም ያዳክማል፣ ለዚህ ደግሞ የውጪ ንግድን ለማበረታታት የሚል ስም ይሰጣልም ብለዋል።

ከዚህ በፊት የተደረጉ የብርን የመግዛት አቅም ማዳከም ውሳኔዎች የኑሮ ውድነትን ከማባባስ፣ የሐብት ሽሽትን ከመፍጠር እና የንግድ ሚዛንን ከማዛባት ውጪ ጥቅም አለማስገኘታቸውንም አክለዋል ዶከተር ሽመልስ። እንደ ዶክተር ሽመልስ ገለጻ የሀገር ውስጥ መገበያያ ገንዘብን ማዳከም የሚሰራው እንደ ጃፓን እና ቻይና ያሉ ሰፊ ወደ ውጪ ሊላኩ የሚችሉ ምርቶች ላሏቸው ሀገራት ብቻ እንጂ እንደ ኢትዮጵያ የግብርና ምርቶችን ወደ ውጪ ለሚልኩ ሀገራት አይደለም።

መንግስት የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ከሚያመነጨው ገቢ በላይ ብር ማተሙን ካላቆመ የኢኮኖሚ ቀውሱ ይጨምራል ያሉት ደግሞ ሌላኛው ኢኮኖሚስት አቶ መቆያ ከበደ ናቸው። አቶ መቆያ እንዳሉት “የመንግስት ገቢ እና ወጪ አለመመጣጠን፣ ቅንጡ ፕሮጀክቶች ላይ ከፍተኛ ገንዘብ ማፍሰስ እና መንግስት ራሱ የውጭ ምንዛሬ ከጥቁር ገበያ እየገዛ መሆኑ በኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሬ እጥረቱን እያባባሱ ናቸው” ብለዋል።

“በኢትዮጵያ ማንኛውም ሰው የየትኛውንም ሀገራት መገበያያ ብር እስካለው ድረስ ከጥቁር ገበያ እየገዛ ነው” የሚሉት አቶ መቆያ ይህ የሚያሳየው የውጭ ምንዛሬ ከገበያው ላይ መኖሩን ነው፣ ኢኮኖሚው የውጭ ምንዛሬ እያመነጨ ነው፣ ችግሩ የአያያዝ እንጂ የአቅርቦት አይደለም ሲሉም አክለዋል። መንግስት የገጠመውን የውጭ ምንዛሬ እጥረት ለመፍታት ኢኮኖሚውን በውድድር ለይ የተመሰረተ ማድረግ እና የውጭ ምንዛሬ ተመኑን በባንኮች እና በጥቁር ገበያ ያለውን እኩል ማድረግ ይኖርበታልም ብለዋል። በኢኮኖሚው አስገዳጅነትም ሆነ በእነ ዓለም ባንክ ቅድመ ሁኔታ የኢትዮጵያ መንግስት የብርን የመግዛት አቅም ማዳከሙ እንደማይቀርም አቶ መቆያ ግምታቸውን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዋና ገዢ ከሰሞኑ የብርን የመግዛት አቅም ሊዳከም ነው በሚል እየተሰራጨ ያለው መረጃ ሀሰት ነው ሲል ማስተባበሉ ይታወሳል።

  @Addis_News
@Addis_News
6.5K views06:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-13 07:50:48 የማለዳ ዐበይት ዜናዎች

1፤ የትግራይ ክልል የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ዓለማቀፍ ረድዔት ድርጅቶች ያቋረጡት የምግብ ዕርዳታ እንዲቀጥል ጥሪ ማድረጉን ቪኦኤ ዘግቧል። በክልሉ የምግብ ዕርዳታ ሥርጭቱ ባለፈው ወር ከተቋረጠ ወዲህ፣ ወደ ክልሉ እየገቡ ያሉት መጠነኛ የሕጻናት አልሚ ምግቦችና የግብርና ግብዓቶች ብቻ መኾናቸውን ኮሚሽኑ መግለጡን ዘገባው ጠቅሷል። የዓለም ምግብ ፕሮግራም ከሽሬ ከተማ የዕርዳታ መጋዘኔ ከፍተኛ መጠን ያለው የዕርዳታ እህል ተዘርፏል በማለት፣ የዕርዳታ ሥርጭት ማቋረጡ ይታወሳል። የአሜሪካው ዓለማቀፍ የልማትና ዕርዳታ ድርጅትም በተመሳሳይ ምክንያት የዕርዳታ ሥርጭት ለጊዜው አቋርጫለኹ ብሏል።

2፤ ዓለማቀፉ የፍልሰት ድርጅት የጅቡቲ መንግሥት በሕገወጥ መንገድ ገብታችኋል ብሎ ያስወጣቸው 6 ሺህ  ኢትዮጵያዊያን ፍልሰተኞች አፋር ክልል ደዋሌ መግባታቸውን አስታውቋል። ድርጅቱ፣ በምሥራቃዊው መስመር ማለትም በፑንትላንድ፣ ሱማሌላንድና ጅቡቲ በኩል ወደ ባሕረ ሰላጤው አገራት ለሚሰደዱ 1 ሚሊዮን ያህል ፍልሰተኞች የ58 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ከለጋሾች ጠይቋል። በምሥራቁ መስመር ባሕር አቋርጠው የሚጓዙት ፍልሰተኞች አብዛኞቹ ኢትዮጵያዊያን መኾናቸውን የጠቀሰው ድርጅቱ፣ ለጋሾች ይህንኑ መስመር ዘንግተውታል በማለት ወቅሷል። ድርጅቱ የገንዘብ ድጋፉን የጠየቀው፣ በስደት ወቅት እንግልት ለሚገጥማቸው ፍልሰተኞችና ለተመላሾች የተለያዩ ድጋፎችን ለመስጠት ነው።

3፤ ኢትዮጵያ፣ ሱማሊያና ኬንያ በጋራ ድንበር ጸጥታ ዙሪያ ለመተባበር የሚያስችላቸውን የጋራ ፕሮጀክት መርቀዋል። ከብሪታኒያ መንግሥት የገንዘብ ድጋፍ የሚያገኘው የጋራ ፕሮጀክቱ መሠረቱ የተጣለው፣ በሰሜን ምሥራቅ ኬንያ ማንዴራ አውራጃ እንደኾነ የኬንያ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። የፕሮጀክቱ ዓላማ፣ በአገራቱ የጋራ የድንበር አካባቢ ሰላም፣ ጸጥታ፣ ልማትና ድንበር-ዘለል ትብብሮችን ማረጋገጥ ነው። ሦስቱ አገራት የጋራ ፕሮጀክቱን የጀመሩት፣ በነውጠኛው አልሸባብ ላይ የጋራ ወታደራዊ ዘመቻ ለማድረግ ከተስማሙ ከጥቂት ስምንታት በኋላ ነው።

4፤ የኤርትራ ማስታወቂያ ሚንስቴር የኢትዮጵያው "ቦርከና" ጋዜጣ "በኤርትራና ኢትዮጵያ መካከል ውጥረት እየተፈጠረ ይኾን?" በማለት ያተመውን ሃተታ "በሐሰትና ግምታዊ ድምዳሜ የተሞላ" በማለት ተችቷል። ሚንስቴሩ በመግለጫው፣ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ በቅርቡ ስለ ሱዳኑ ግጭት በሰጡት ቃለ ምልልስ ኢትዮጵያን ጎሸም ያደረጉ አስመስሎ አቅርቧል በማለት ወቅሷል። ጋዜጣው "ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሥመራ መሄድ ፈልገው፣ የኤርትራ መንግሥት ሁለት ጊዜ ፍቃድ ነፍጓቸዋል" እንዲኹም "ኤርትራ ለአማራ ፋኖዎች ወታደራዊ ሥልጠና በመስጠቷ የዐቢይ ካድሬዎች ኢሳያስን እየተቹ ነው" በማለት የጻፋቸው ነገሮች "ሐሰት" መኾናቸውንም ሚንስቴሩ ገልጧል። ሚንስቴሩ፣ ኤርትራ አዲስ ወታደራዊ ዝግጅት እያደረገች እንደኾነ ጋዜጣው ያሰራጨውን ወሬም "የተሳሳተ" በማለት አስተባብሏል።

5፤ ደቡብ ሱዳን የግብጹ ፕሬዝዳንት አል ሲሲ በሱዳን ግጭት ዙሪያ ለመምከር የመሪዎች ስብሰባ እንዲካሄድ ለፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ሃሳብ ማቅረባቸውን በውጭ ጉዳይ ሚንስቴሯ በኩል አረጋግጣለች። ፕሬዝዳንት ሲሲ ይህንኑ ሃሳብ ያቀረቡት፣ ውጭ ጉዳይ ሚንስትራቸውን ሳሜ ሽኩሪን ከአራት ቀናት በፊት ወደ ጁባ በላኩበት ወቅት እንደኾነ ሚንስቴሩ ገልጧል። ፕሬዝዳንት ኪር በበኩላቸው፣ የመሪዎች ጉባዔ ከተካሄደ የሁሉንም የሱዳን ጎረቤቶች መሪዎች ያካተተ ይሁን የሚል መልስ መስጠታቸውንና የፕሬዝዳንት ሲሲን ምላሽ እየተጠባበቁ መኾኑን ሚንስቴሩ ጨምሮ አመልክቷል።

Via ፦ [ዋዜማ]

@Addis_News
@Addis_News
7.5K views04:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-13 07:50:02
የትዳር እና የወንድ ልጅ ችግር የሆነውን የስንፈተ ወሲብ እንዲሁም የብልት ቁመት ማነስን በዘላቂነት ችግሩን የሚፈታ ORGINAL EUROPE STANDARD መዳኒቶች እኛ ጋር አሉ
   MAXMAN TITAN_GEL VIMAX
የብልት መጠንን በዘላቂ ሁኔታ ለመጨመር
በግንኙነት ወቅት ቶሎ ላለመርጨት
የተሻለ የወሲብ ፍላጎት አና ችሎታ የሚጨምር
ብልት ውጥር እና ቀጥ ብሎ እንዲቆይ
  % ኦሪጂናል (noside effect )
  % ተፈጥሮዊ (herbal)
                         0907270050
                         0907270050
እንዲሁም ኅርባል ክብደት መጨመሪያ አለ ይደውሉ
አ.አ ላላችሁትም በእራሳችን transport  ያሉበት ድረስ በ 30 ደቂቃ እናደርሳለን
ወደ ክልል ከተሞች በፖስታ ቤት እንልካለን
ለተጨማሪ መረጃ https://t.me/TWAKELpharmacy
https://t.me/TWAKELpharmacy
6.9K views04:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-13 07:49:29
ከ ሀገር ዉጭ ዉስጥም ያላቹ የተወደዳችሁ ቤተሰቦቼ 
መርጌታ  የባህል መድህኒት
0945638808
0945638808

1.ለሀብት
2.ለገበያ ብዙ ደንበኛ እንዲኖረን
3.ለመስተፋቅር
4.መኖሪያ ፈቃድ በ12 ቀን ለመቀበል

የምንሰራው ጥበብ
============
5.ሰውን ለማፍዘዝ ለማደንገዝ
6. ለሰላቢ በሌላ አማርኛ ነገሮችን ለመሰወር
7.ለግርማ ሞገስ
8.ለትምህርት ዘኢያገድፍ
9.ለዐቃቤ ርዕስ ለመከላከያ
10.ሰው እንዲወደን ማድረግያ
11.ብልት ማሳደጊያ ዕፀ አብይ
12.ለስንፈተ ወሲብ
13.ለዐደበተ ርቱዕ ጥሩ ተናጋሪ እንድንሆን
14.ለቁመት መጨመርያ ዕፀ (ኤግኤል)
15.በግለ ወሲብ ለምትሰቃዩ ወይም በሴጋ
16.ለመልክ ውበት እንዲኖረን ማድረጊያ
17. ስራ እንድንቀጠር ማድረግያ
18.ፈተና አሪፍ ውጤት እንድናመጣ ማድረግያ
19.ለሴቶች ትልቅ ዳሌ እንዲኖረን ማድረግያ በዕፀዋት ብቻ
20.ፀጉር እንዲረዝም ማድረጊያ ..... ወዘተ
21.ለውፍረት
22.ለቅጥነት
23.ለስልጣን መጨመርያ
24.ለጥላ ወጊ
25.ለህዝብ ፍቅር
26.ብር እንዳይባክን ማድረግያ
27.የሴት ድንግልና መመለሻ
28.ለቁማር
29.ደፋር ለመሆን
30. ህልም እንፈታለን
31. ትዳር ላይ ማትስማሙ እድትስማሙ ሚያደርግ
32.ለመካን

ስ.ቁ 0945638808
7.2K views04:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-12 22:22:17
የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን) አባልና ስራ አስፈፃሚ ዘሪሁን ገሰሰ አሁን ከመሸ ከእስር ተለቋል።

@Addis_News
@Addis_News
11.1K views19:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-12 20:34:14
#የችሎት ውሎ

ፍ/ቤቱ ፖሊስ በጋዜጠኞቹ ላይ የጠቀቀውን ተጨማሪ 14 ቀናት የምርመራ ጊዜ ፈቀደ!


ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው እና ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ አስፋው ዛሬ ግንቦት 4 ቀን 2015 ዓ.ም ከረፋዱ 4:00 ላይ በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አንደኛ ወንጀል ችሎት ቀርበው ነበር::
ጋዜጠኞቹ በሁከትና ብጥብጥ ተጠርጥረዋል በሚል ቀደም ሲል አራዳ ፍርድ ቤት ቀርበው በዋስ እንዲወጡ ተወስኖላቸው የነበረ ሲሆን የፌደራል ፖሊስ ውሳኔውን በመተው በሌላ "በሽብር" ጠርጥሬያቸዋለሁ በሚል ነው ወደልደታ ፍርድ ቤት ያዛወራቸው::
ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርበው በጠበቆቻቸው በኩል ጥፋተኛ አለመሆናቸውንና ህጉ ከሚፈቅደው ውጭ ጋዜጠኞቹ በቅድመ እስር እየተጉላሉ መሆኑን ተከራክረዋል::
በዋስ ወተው ጉዳያቸውን በውጭ እንዲከራከሩም ጠይቀው ነበር::
ይሁንና ፍርድ ቤቱ መርማሪ ፖሊስ የጠየቀውን የ14 ቀን ቀጠሮ ፈቅዷል ሲል ጋዜጠኛ አራጋው ሲሳይ አጋርቷል።



@Addis_News
@Addis_News
12.8K views17:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-12 20:27:16
በአማራ ክልል በባህርዳር እና በሌሎችም ትልልቅ ከተሞች ታግዶ የነበረው የዳታ ኢንተርኔት አገልግሎት ተለቋል።

በአማራ ክልል ከልዩ ኃይል እንደገና መደራጀት ጋር ተያይዞ በተከሰተው አለመግባባት በትልልቅ ከተሞች የኢንተርኔት አገልግሎት ተቋርጦ እንደቆየ ሲገለጽ ነበር።

ካሳለፍነው ረቡዕ ግንቦት 2/2015 ምሽት ጀምሮ ግን አገልግሎቱ መለቀቁን ኢትዮ ኤፍ ኤም ከነዋሪዎቹ አረጋግጧል።የዳታ ኢንተርኔት አገልግሎት ተቋርጦባቸው የነበሩት ጎንደር፣ ባህርዳር እና ወልዲያ ከዕረቡ ምሽት ጀምሮ መስራት እንደጀመረ ታውቋል፡፡

የሞባይል ዳታ አገልግሎት በአማራ ክልል በጎንደር፣ በባህርዳር እና በወልዲያ ከተማ ከተዘጋ ከኹለት ሳምንታት በላይ ያስቆጠረ ሲሆን፣ የተዘጋበት ዋና ምክንያት በክልሉ ከሚንቀሳቀሰው ታጣቂ ኃይልና ከክልሉ ልዩ ኃይል ጋር በተገናኘ በተፈጠረው ውጥረት እንደነበር ተነግሯል፡፡

[ኢትዮ ኤፍ ኤም]

@Addis_News
@Addis_News
12.1K views17:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ