Get Mystery Box with random crypto!

የርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ትምህርቶች

የቴሌግራም ቻናል አርማ abagebrekidan — የርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ትምህርቶች
የሰርጥ አድራሻ: @abagebrekidan
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 43.76K
የሰርጥ መግለጫ

በዚህ ቻናል ተሰምተው የማይጠገቡ የአባታችንን ትምህርቶች በትንሽ ሜጋ ባይት ታገኛላችሁ
ለማንኛውም አስተያየት @Anteyee ማድረስ ትችላላችሁ

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2024-04-21 18:54:10 ኒቆዲሞስ|| ሰማያዊ ልደት
                      
Size 21.7MB
Length 1:02:18

  በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
http://t.me/abagebrekidan
http://t.me/abagebrekidan
13.7K viewsÃńŧęŋəĥ, 15:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-20 18:50:35

15.3K viewsSamuel, 15:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-15 19:05:14

13.2K viewsSamuel, 16:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-13 14:39:35 እሴተ ሃይማኖት  
       ክፍል 4                          
Size:- 18.9MB
Length:-54:07
       
     በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
http://t.me/abagebrekidan
http://t.me/abagebrekidan
14.0K viewsÃńŧęŋəĥ, 11:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-12 08:53:18ስለእውነት ምን ይሻላል?✞✞

እውነትን ለማወቅ የሚፈልግ የለም እንጅ እውነትን ለማወቅ ሁሉም ደፋ ቀና እያለ ነው። ስለ እውነት የሚጠይቁ የማይቆጠሩ ናቸው። ሰለ እውነት የሚመራመሩትስ ቢሆን! ስለ እውነት የሚዋኙ አሉ። ስለ እውነት የሚከንፉም እልፍ! ስለ እውነት የሚቆፍሩም ትእለፊት ናቸው። እውነት ግን በዚህ ሁሉ የለችም። ምክንያቱም እውነት አይፈልጓትም እንጅ አጠገባቸው አለችና። እውነት ልሳኗ እስኪዘጋ በረጅም ጩኸት አየጮኸች አቤት የሚላት የለም። ለእውነት ጆሮውን የደፈነው ሁሉ ግን ስለ እውነት ተመራማሪ ነው። አንድ ቀን አይቷት ቀርተቶ ሲያልፍ ድምጿ ጭር ያላለችበት ሁሉ የእውነት የልብ ወደጅ ነኝ ብሎ ስለ ራሱ ድርሰት ያስነብባል። እውነት ታማ አጠገባቸው እየረገጡ ወደ ውሸት ሠርግ እየሄዱ የእውነት ጠበቃ ይሆናሉ። ነብርን የፍየል፥ ጅብን የአህያ፥ ፍየልን የቅጠል፥ ቀበሮን የበግ ፥ዶሮን የጥሬ ፤ውሻን የቅቤ ጠበቃ የሚያቆማቸው ማን ነው? አንድ ሚ'ገርመኝ ነገር አለ። ድመትን ነምር ቢያባርራት። ድመትን አስጥሎ ራሱ ለመብላት ነው እንጅ እውነት ሳንባን ከድመት ለመጠበቅ ይሆናልን?

እውነት ቤት ውስጥ አለች ነገር ግን ሰዎች ከቤት ያስወጧት ዘንድ ሌሊት ከቀን እየጎሰሟት ስለ እውነት ግን ደግሞ በአደባባይ ይሰብካሉ። በውሸት ሻማ እውነትን ይፈልጋሉና የእድሜ ነፋስ ሻማውን ያጠፋውና እውነትን ሳያዩ ያሸልባሉ። አንገቱን ያቀረቀረ ሰማይን አያይም፤ ሥግብግብነት ያጎበጠው ሰውም በእውነት ሰማይ ላይ የሚያበራውን ጸሐይ አያይም። መድኀኒቱን በመርዝ ዕቃ ቢጠጡት ይገድላል እንጅ አያደንም። እውነትንም በውሸት መመርመር አይቻልም እውነትን እየሰቀሉ እውነትን ይመረምራሉ። በውሸት በሚኖሩም የውሸት መሞት ግን አይቻልም።

በእውነት ላይ ፍርድ እየፈረዱ እውነት ምንድን ነው ቢሉት ምን ዋጋ አለሁ? ይህቺ ዓለም
ስለ እውነት እየጠየቅን መልሱን ሳንሰማ እንድንወጣ በሁከቷ እድል ትነሳናለች።"ጌታ ኢየሱስም መልሶ እኔ ንጉሥ እንደሆንሁ አንተ ትላለህ። እኔ ስለ እውነት ልመሰክር ስለዚህ ተወልጃለሁ ስለዚህም ወደ ዓለም መጥቻለሁ፤ ከእውነት የሆነ ሁሉ ድምፄን ይሰማል አለው። ጲላጦስም እውነት ምንድን ነው አለው ይህንንም ብሎ ዳግመኛ ወደ አይሁድ ወጥቶ እኔስ አንዲት በደል ስንኳ አላገኘሁበትም።"ዮሐ፲፯፰፥፴፯
ጰላጦስ ስለ እውነት ጠይቆ ሳይመለስለት ለእውነት ጥብቅና ሊቆም ወጣ። ሳይጸናበትም ቀረና እውነትን ሰቀለ። እርሱ በጌታ ላይ በደል አለማግኘቱ ብቻ መስሎታል እውነት! ጌታ ግን የሌለበት ብቻ ሳይሆን ኃጢአትትን የሚደመስስ እውነተኛ አምላክም ነበር። ይህ ግን እሰከ ጊዜው ድረስ አልገባውም ነበር። እውነትን እሽ በጎ ላለማለት እድል የሚነሱት ገንዘብና ሥልጣን መጣበት ናቸው። ዓለም ለእውነት መኖር በሚፈልጉ ሰዎች ላይ ፈጥና ጉሮሯቸው ላይ ትቆማለች ወዲያውም የህልውና ጉዳይ አይደል ምን ይደረግ ታስብላቸዋለች። ማራጭ በማያቀርቡለት ኑሯቸው ለይ ትመጣለች። እነርሱም እውነትን ሳይውጧት ይቀራሉ። ጲላጦስ በከፊሉም ቢሆን ስለ እውነት ሲከራከር አይሁድ"እንግዲያውስ የቄሳር ወዳጅ አይደለህም" ነበር ያሉት። ያን ጊዜ ተብረከረከ። በሹመቱ መጡበታ!

ችግሩ ምንድን ነው። እውነት በጥልቀት ሳትገባው ስለ እውነት መቆሙ። ሳይገባው የወደደ ሳይገባው ይጠላል። ሳይገባው ያመነ፡ሳይገባው ይክዳል። እውነት ክርስቶስ ነው። ቄሳር የጲላጦስ ንጉሥ ቢሆንም ክርስቶስ ግን የቄሳር ፈጣሪ ነው። ስለዚህ ይህ ቢገባው አይሸበርም ነበር።
ሁለተኛ ስለ እውነት ሲኖር ይህ እንደማይቀርለት ማወቅ ነበረበት። ነገር ግን ይህ ሁሉ ባይቀርም በእውነት ነጻ መውጣቱ ደግሞ አይቀርም! ወተአምርዋ ለጽድቅ ወጽድቅኒ ታግዕዘክሙ=እውነትን ታውቃላችሁ እውነትም አርነት ያወጣችኋል" ዮሐ፰፥፴፪
ስለ እውነት እንድናውቅ እውነት እንዲገባን
ስለ እውነት ለመኖር እውነት እንዲመራን
እውነተኛው አምላክ በእውነት ይጠብቀን!
አባ ገብረ ኪዳን
http://t.me/abagebrekidan
http://t.me/abagebrekidan
13.7K viewsÃńŧęŋəĥ, 05:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-06 21:12:32 መጋቢት 29
††† በዓለ ጽንሰት †††

††† ይሕች ቀን ለቤተ ክርስቲያን በእጅጉ ልዩ ናት:: በዓመቱ ከሚከበሩ በዓላትም አንደኛውን ሥፍራ ትይዛለች::

በዚሕ ዕለት አምላካችን እግዚአብሔር:-

1.ሰማይና ምድርን ፈጠረ:: (ዘፍ. 1:1)

2.በቅዱስ ገብርኤል ብሥራት በድንግል ማርያም ማኅፀን አደረ (ተጸነሰ):: በዓሉም "በዓለ ትስብእት" ይባላል:: "አምላክ ሰው : ሰው አምላክ የሆነበት" ማለት ነው:: (ሉቃ. 1:26)

3.የክብር ባለቤት መድኃኔ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን ድል አድርጎ ተነሳ:: (ማቴ. 28:1፣ ማር. 16:1፣ ሉቃ. 24:1፣ ዮሐ. 20:1)

4.ጌታችን ዳግመኛ ለፍርድ በዚሕች ቀን ይመጣል:: (ማቴ. 24:1)

††† በእነዚህ ታላላቅና ድርብርብ በዓላት ምክንያት ቀኑ "ርዕሰ በዓላት" (የበዓላት ራስ) : "በኩረ በዓላት" እየተባለም ይጠራል::

††† "እነሆ ከደመና ጋር ይመጣል:: ዓይንም ሁሉ: የወጉትም ያዩታል:: የምድርም ወገኖች ሁሉ ስለ እርሱ ዋይ ዋይ ይላሉ:: አዎን አሜን::
ያለውና የነበረው: የሚመጣውም: ሁሉንም የሚገዛ ጌታ አምላክ: አልፋና ኦሜጋ እኔ ነኝ ይላል::" †††
(ራእይ ፩፥፯)
እንኳን አደረሳችሁ
http://t.me/abagebrekidan
http://t.me/abagebrekidan
13.9K viewsÃńŧęŋəĥ, edited  18:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-28 20:46:49 ❖❖❖ አንድ " ግዩር " እንዲህ ይመክራል ❖❖❖❖

ሥለ እግዚአብሔር ብለን ሰውን እንውደድ እንጅ ስለ ሰው ብለን እግዚአብሔርን መውደድ አይገባንም ። በእግዚአብሔር ፊት ሰውን መውደድህን ይገለጥልህ እንጅ በሰው ፊት የእግዚአብሔር ወዳጅ ለመምሰል ብለህ የምትኖ ር አትሁን ። ለሰዎች ብለህ እንደወደድከው ለሰዎች ብለህ ልትጠላው ትችላለህ እና ።
❖❖❖❖❖❖❖
የእግዚአብሔር ሰው መሆን ማለት እግዚአብሔርን መመገብ እንጅ እግዚአብሔርን ማወቅ አይደለም ። ለመዳን ብለህ እወቅ እንጅ በእውቀትህ የምትድን አይምሰልህ ። የማታውቀውን የምታውቀው ልትኖረው እንጅ እውቀቱ በክርስቶስ ቀኝ ሊያቆምህ አይምሰልህ ። በጎ ነገርን ያወቅሃት ዕለት ብቻ ደስ አይበልህ ፥ የሠራሃት ዕለት እንጅ ፥ በመሥራትህም አትመካ አልፈጸምካትምና ። ከእግዚአብሔር ያወቅሃትን መልካም ነገር ወዲያው ሥራት ፥ እየሠራሃት ያለችህን መልካም ነገር አትልቀቃት ። እየኖርክ ተማር እንጅ እየተማርክ ብቻ ዘመንህን እንዳትፈጽም ተጠንንቀቅ ። ያለ ዕውቀት ብትኖር ከፍርድ የምታመልጥ አይደለምና መቼም ቢሆን ከቤተክርስቲያን ጉባዔያት አትታጣ ፥ በማወቅህ ፍርድ አይቀርልህምና ያወቅኸውን ፈጥነህ ሥራ ።
❖❖❖❖❖❖❖
ቤተክርስቲያንን በሁለት መንገድ ማወቅህን አረጋግጥ ። እንደ አሕዛብ ጠላቷ እንዳትሆን በትምህርት ዕወቃት ፤ እንደ ፈሪሳውያን እንዳትሆን በኑሮ ዕወቃት ። ለሥርዓቷ ታማኝ ሁን ፥ አንተ ወደ ሥርዓቷ እደግ እንጅ ሥርዓቷ ወደ አንተ ፈቃድ እንዲወርድልህ አትውደድ ፤ ሰማያውይቷን ቤተክርሰቲያን ምድራዊት እንድትሆንልህ አትፍቀድ ። በቤተክርስቲያን መንፈሳዊ አንድነቶች ካልተሳተፍክ ከቤተክርስቲያን አንድነት እየተለየህ እንደሆነ እወቅ ። እሊህም ፦ ኪዳን ማስደረስ ፥ ማስቀደስ ና ንስሐ ገብቶ መቁረብ ፥ በምህላ ጸሎቶቿ በአዋጅ አጽዋማቷ መተባበር ናቸው ። ከቤት ከሚጸለይ አሥር ጸሎት ይልቅ በቤተክርስታያን የሚደረግ አንድ ጸሎት እንደሚበልጥ አውቀህ በየቀኑ ወደ እርስዋ ገሥግሥ ። በሕይወትህ ሁሉ ቤተክርስቲያናዊ ሁን !

ብቻየን ለፋሁበት ብለህ ገንዘብህን ብቻህን አትጨርሰው ። ከምታገኘው ሁሉ ለመድኀኔዓለም ድርሻ አስቀምጥ ። የለመነህን ሰው አትመርምረው ቢቻልህ ስጠው ባይቻልህ እዘንለት እንጅ ። ለስንፍናህ ሁሉ ምክንያት አታብጅለት ። መልካሙን ነገርም ዛሬ ሥራው ፥ ክፉውን ነገርም ዛሬ ተናዘዘው ። እያንዳንዱ የጊዜ ሽርፍራፊ የገነትና የሲዖል ሰው ለመሆንህ ዋጋ እንዳለው እወቅ ።
ይቆየን
መልካም የሆነ እግዚአብሔር ለመልካም የሚሳብ መልካምን የሚያደርግ በመልካሞ የሚጸና በጎ ሕሊና ይስጠን !

ርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረኪዳን
ሰኔ ፲፯ - ፳፻፲፪ ዓም
http://t.me/abagebrekidan
http://t.me/abagebrekidan
13.4K viewsÃńŧęŋəĥ, edited  17:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-27 10:09:54 ተፈስሒ ፍስሕት
ውዳሴ ማርያም የመድገም ጥቅም
t.me/abagebrekidan
14.3K viewsÃńŧęŋəĥ, 07:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-26 20:04:00 እኔ ካንተ ጋር ነኝና አትፍራ
                         
Size 23.8MB
Length 1:08:15

  በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
http://t.me/abagebrekidan
http://t.me/abagebrekidan
12.9K viewsÃńŧęŋəĥ, 17:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-22 20:43:03

13.1K viewsSamuel, 17:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ