2024-03-19 08:53:19
መስቀል ነደ እሳትን የተሸከመ የኪሩቤልም ባልንጀራ የሆነ እንደ ድንግል ማርያም ስም አራት ፊደል ያለው ነበልባላዊ የእሳት መንበር።
✣✣✣ አዳምን ከሞት ያወጣው የሕይወት ዛፍ።
✥✥✥ የኃጢአትን ቀላይ የገታ መርከብ።
❖❖❖ ባሕረ እሳትን ያሻገረ የድኅነት ትርክዛ።
✞✟✟ነፍሳት የሕይወት እንጀራን የጠገቡበት ማዕድ!
✟✟✟ክርስቶስና ቤተክረስተያን የተሞሸሩበት የሠርግ ቦታ።
ምእመናን የተጸነሱበት መካነ ክርስትና።
ቤተክርስቲያን የጸናችበት መሠረተ ሃይማኖት።
የፍስሐ ኩሉዓለም ክርስቶስ ደም የፈለቀበት ሙሐዘ ትፍሥሕት!
ከሕይወት ውኃ ከክርስቶስ የተተከለ ሁል ጊዜ የሚያፈራ የሕይወት ዛፍ።
የንጉሥ ልጅ በአባቱ ኅልቀተ ወርቅ ማኅተም እንዲመካ፥ የንጉሠ ነገሥት ክርስቶስ ልጆች የምንለይበት የምንመካበት ትእምርተ ድኂን።
የጨለማውን አበጋዞችን ድቅድቅ የምንገፍበት
ጸዳለ ኩሉ ዓለም።
የሚወረወረውን ፍላጻ የምንሰብርበት ልብሰ ሃይማኖት ጥሩር።
✟✟✟ ጦር ከነቀነቀ ጋሻ ከታጠቀ ከቀን ወራሪ ከሌሊት ሰባሪ የምንመክትበት ንዋየ ሐቅል።
ቢዋጉ ማሸነፊያ ቢሸሹ መጠጊያ ጸወነ ሥጋ ወነፍስ ወልታ ጽድቅ።
መስቀል መልዕልተ ለኩሉ ነገር
ርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማhttp://t.me/abagebrekidan
http://t.me/abagebrekidan
13.3K viewsÃńŧęŋəĥ, 05:53