Get Mystery Box with random crypto!

Tiriyachen | ጥሪያችን

የቴሌግራም ቻናል አርማ tiriyachen — Tiriyachen | ጥሪያችን T
የቴሌግራም ቻናል አርማ tiriyachen — Tiriyachen | ጥሪያችን
የሰርጥ አድራሻ: @tiriyachen
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.91K

Ratings & Reviews

1.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2023-03-15 18:01:11 ባለ ሦስት ፊት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

112፥1 በል «እርሱ አላህ አንድ ነው»፡፡ قُلْ هُوَ اللَّهُ أَحَدٌ

አምላካችን አሏህ በምንነት ሆነ በማንነት አንድ አምላክ ነው፥ ከእርሱ ጋር ምንነቱን የሚጋሩ የሆኑ ማንነቶች የሉም። ከእርሱ በቀር አምላክ የለም፦
112፥1 በል «እርሱ አላህ አንድ ነው»፡፡ قُلْ هُوَ اللَّهُ أَحَدٌ
20፥14 እኔ አላህ እኔ ነኝ ያለ እኔ አምላክ የለምና አምልከኝ፡፡ ሶላትን እኔን ለማውሳት ስገድ፡፡ إِنَّنِي أَنَا اللَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا أَنَا فَاعْبُدْنِي وَأَقِمِ الصَّلَاةَ لِذِكْرِي

"ሸኽስ" شَخْص ማለት "እኔነት"person" ማለት ሲሆን "ማን" ተብሎ የሚጠየቅ "ማንነት" ነው፥ ከነሕው ሕግ አንጻር በሙተከለም "አና" أَنَا እና በጋዒብ "ሁወ" هُوَ ብለን የምንጠቀመው ለሙፍረድ ሸኽስ ነው። "እኔ" ብሎ ሦስት አካል የለምና፥ ባይሆን "እኔ" ማለቱ በራሱ አንድ "እኔነት" እንደሆነ ቁልጭ እና ፍንትው አርጎ ያሳያል።
እንደ ጎርጎሮሳውያን አቆጣጠር በ 220 ድህረ-ልደት ጠርጡሊያኖስ፦ "አምላክ በምንነት አንድ በማንነት ሦስት ነው" ብሎ የሥላሴን ቀመር ቀምሯል። "ኡሲያ" οὐσία ማለት "ኑባሬ" "ሃልዎት" "ህላዌ" ማለት ሲሆን ግሪካውያን "ምንነትን" ለማሳየት የሚጠቀሙበት ስያሜ ነው፥ "ፕሮሶፓን" πρόσωπον የሚለው ቃል "ፕሮስ" πρός ማለትም "ዘንድ" እና "ኦፕስ" ὤψ ማለትም "ዓይን" ለሚለው ሁለት ቃላት ውቅር ሲሆን "ፊት" ወይም ለድራማ እና ለቲያትር ብለው ፊት ላይ የሚያጠልቁት "ጭንብል"mask" ማለት ነው፦
ማቴዎስ 6፥17 "ፊትህን" ታጠብ። τὸ πρόσωπόν σου νίψαι,

እዚህ አንቀጽ ላይ "ፊት" ለሚለው የገባው ቃል "ፕሮሶፓን" πρόσωπον እንደሆነ አንባቢ ልብ ይለዋል። አንዱ አምላክ አብ አንድ ፊት እንዳለው በግልጽ ተቀምጧል፦
ራእይ 22፥3 "ፊቱንም" ያያሉ። καὶ ὄψονται τὸ πρόσωπον αὐτοῦ,
ማቴዎስ 18፥10 መላእክቶቻቸው በሰማያት ዘወትር በሰማያት ያለውን የአባቴን "ፊት" ያያሉ እላችኋለሁና። λέγω γὰρ ὑμῖν ὅτι οἱ ἄγγελοι αὐτῶν ἐν οὐρανοῖς διὰ παντὸς βλέπουσι τὸ πρόσωπον τοῦ Πατρός μου τοῦ ἐν οὐρανοῖς.

እነዚህ አናቅጽ ላይ "ፊት" ለሚለው የገባው ቃል "ፕሮሶፓን" πρόσωπον እንደሆነ ልብ አድርግ! በብሉይ ኪዳን ግሪክ ሰፕቱአጀንት ፈጣሪ አንድ ፊት እንዳለው ለማመልከት እና ለማመላከት በነጠላ "ፕሮሶፓን" πρόσωπον ተብሎ ተገልጿል፦
ዘጸአት 33፥20 ደግሞም፦ ሰው አይቶኝ አይድንምና "ፊቴን" ማየት አይቻልህም" አለ። καὶ εἶπεν· οὐ δυνήσῃ ἰδεῖν τὸ πρόσωπόν μου· οὐ γὰρ μὴ ἴδῃ ἄνθρωπος τὸ πρόσωπόν μου καὶ ζήσεται.

ባይብል ላይ ባለ ሦስት ፊት አምላክ ቢኖር ኖሮ "ፕሮሶፓ" πρόσωπᾰ ማለትም "ፊቶች" የሚል ቃል እናገኝ ነበር። ኢየሱስ ከአንዱ አምላክ በተለየ መልኩ የራሱ "ፊት" እንዳለው ተቀምጧል፦
ማቴዎስ 26፥39 ጥቂትም ወደ ፊት እልፍ ብሎ በ-"ፊቱ" ወደቀ። καὶ προελθὼν μικρὸν ἔπεσεν ἐπὶ πρόσωπον αὐτοῦ,
ማርቆስ 1፥2 መንገድህን የሚጠርግ መልክተኛዬን በ-"ፊትህ" እልካለሁ። ἀποστέλλω τὸν ἄγγελόν μου πρὸ προσώπου σου,

አሁን እነዚህ አናቅጽ ላይ "ፊት" ለሚለው የገባው ቃል "ፕሮሶፓን" πρόσωπον ነው። "አንዱ አምላክ "ሦስት ፊት" አለው" የሚል ከዘፍጥረት እስከ ራእይ በባትሪ ብትፈልጉ አታገኙም፥ አንድ ምንነትን የሚጋሩ ባለ ሦስት ፊት አምላክ በህንድ ብራህማ፣ ቪሽኑ እና ሲቫ ሲሆኑ በግብጽ ደግሞ ኦስሪስ፣ አይሲስ እና ሆረስ ናቸው። ዋቢ መጽሐፍ ይህንን ተመልከቱ፦
[Bible Myths and Their parallels in other Religious By T.w Doane 1882 page 369]

የሥላሴ አማንያን በድፍረት "የእኛ አምላክ "ሥሉስ አምላክ" ነው" ብለዋል፥ "ሥሉስ አምላክ" ማለት "ሦስት አምላክ" ማለት ነው፦
፨ሃይማኖተ አበው ዘዲዮናስዮስ ምዕራፍ 99
“አምላካችን ያለ መለየት ሦስት ነው”።

፨የሐሙስ ሰይፈ ሥላሴ 22-23
“ሦስት ልዑላን ገዢዎች፥ ሦስት ጌቶች ናቸው”

፨አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ መድብለ እንዚራ ስብሐት
“በአንቺ "ሦስቱ ጌቶች" የተጠለሉብሽ በድንኳን አጠገብ የቆምሽ ዕንጨት አንቺ ነሽ”

የሥላሴ አማንያን ሆይ! "ፈጣሪን ሦስት ፊት፣ ሦስት ጌቶች፣ ሥሉስ አምላክ(ሦስት አምላክ)፣ ሥሉስ ቅዱስ(ሦስት ቅዱስ)፣ ሦስት ልዑላን ገዢዎች ነው" አትበሉ! ተከልከሉ! ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና፡፡ አላህ አንድ አምላክ ብቻ ነው፦
4፥171 «ሦስት ነው» አትበሉ! ተከልከሉ! ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና፡፡ አላህ አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ وَلَا تَقُولُوا ثَلَاثَةٌ ۚ انتَهُوا خَيْرًا لَّكُمْ ۚ إِنَّمَا اللَّهُ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ

አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen

ወሠላሙ ዐለይኩም
306 views15:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-12 19:57:23 ኢየሱስ ክርስቶስ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

5፥17 *እነዚያ አላህ እርሱ የመርየም ልጅ አልመሲሕ ነው ያሉ በእርግጥ ካዱ*፡፡ لَّقَدْ كَفَرَ الَّذِينَ قَالُوا إِنَّ اللَّهَ هُوَ الْمَسِيحُ ابْنُ مَرْيَمَ

ዐበይት ክርስትናን ማለትም ኦርቶዶክንስ፣ ካቶሊክን፣ አንግሊካንን እና ፕሮቴስታንትን፦ "ፍጡር እና ሰው ታመልካላችሁን? ብለን ስንጠይቃቸው "እረ በፍጹም" የሚል መልስ ይሰጣሉ፥ "ኢየሱስን ታመልኩ የለ? ኢየሱስ አምላክ እና ሰው ወይም በአምላክነቱ ፈጣሪ በሰውነቱ ፍጡር ነው" ትሉ የለ? ለሚለው ጥያቄ ኦርቶዶክን፣ ካቶሊክ እና አንግሊካን፦ "አዎ! ሰውነቱ መለኮት ስላለበት ሰውነቱ ይመለካል" በማለት ፍጡርነቱ እንደሚመለክ ይናገራሉ፥ ስለዚህ ፍጡርና ሰው ያመልካሉ።
ፕሮቴስታንት እንደ ዐቅሚቲ፦"የምናመልከው ሰውነቱን ሳይሆን በሰውነቱ ውስጥ ያለው አምላክነቱን ነው" የሚል ምላሽ ይሰጣሉ። ይህም ችግር የሚመለክ እና የማይመለክ ሁለት ኢየሱስ ወደሚለው ወደ ንስጥሮሳውያን ትምህርት ይጠጋል።
ቅሉ ግን ኢየሱስ እና ክርስቶስ የሚለው ስም በራሱ የፍጡር ስም ስለሆነ ኢየሱስ ክርስቶስ ፍጡር ነው፥ መመለክ በፍጹም የለበትም። ይህንን ነጥብ በነጥብ እንመልከት፦

ነጥብ አንድ
"ኢየሱስ"
"ኢየሱስ" የሚለው ስም "የህ-ሹአ" יְהוֹשׁוּעַ በቀዳማይ ዕብራይስጥ፣ "የሽ-ሹአ" יֵשׁוּעַ‎ በደኃራይ ዕብራይስጥ፣ "ዒሣ" عِيسَى በቀዳማይ ዐረቢኛ፣ "የሡዕ" يَسُوع በደኃራይ ዐረቢኛ፣ "ዔሣዩ" ܝܫܘܥ በዐረማይክ፣ "ኤሱስ" Ἰησοῦς በግሪክ ሰፕቱአጀንት ሲሆን ትርጉሙ "የሕ መድኃኒት" ማለት ነው፥ "የሕ" ወይም "ያሕ" יָהּ‎ የቴትራግራማተን ምጻረ-ቃል ሲሆን ለፍጡራን ስም በመነሻ ቅጥያ አሊያም በመድረሻ ቅጥያ ሆኖ ይመጣል። ይህ "ኢየሱስ" የሚለው የፍጡር ስም የናዝሬቱ ኢየሱስ ከመፀነሱ በፊት ብሉይ ኪዳን ላይ ለብዙ ሰዎች ስም ሆኖ ያገለግል ነበር፥ ከዚያ መካከል የነዌ ልጅ ኢየሱስ ነው፦
1. የግዕዝ እትም፦
ዘኍልቍ 11፥28 ወይቤሎ ኢየሱስ ዘነዌ ዘይቀውም ቅድሜሁ ለሙሴ ዘውእቱ ኅሩዩ ይቤሎ እግዚእየ ሙሴ ክልኦሙ።
2. ትርጉም፦
“ከልጅነቱ ጀምሮ የሙሴ አገልጋይ የነበረው የነዌ ልጅ ኢየሱስ፦ ጌታዬ ሙሴ ሆይ፥ ከልክላቸው አለው።”
3. ዕብራይስጥ፦
וַיַּעַן יְהוֹשֻׁעַ בִּן-נוּן, מְשָׁרֵת מֹשֶׁה מִבְּחֻרָיו–וַיֹּאמַר: אֲדֹנִי מֹשֶׁה, כְּלָאֵם.
4. ግሪክ ሰፕቱጀንት፦
καὶ ἀποκριθεὶς ᾿Ιησοῦς ὁ τοῦ Ναυὴ ὁ παρεστηκὼς Μωυσῇ, ὁ ἐκλεκτός, εἶπε· κύριε Μωυσῆ, κώλυσον αὐτούς.

ግዕዙ "ኢየሱስ" እንዳለው፣ ዕብራይስጡ "የህ-ሹአ" יְהוֹשֻׁ֣עַ እንዳለው፣ የግሪኩ ሰፕቱጀንት "ኤሱስ" Ἰησοῦς እንዳለው አንባቢ ልብ ይለዋል። በተመሳሳይም የአዲሱ ኪዳን ግሪክ ኮይኔ ሐዋ 7፥45 ላይ የነዌ ልጅን "ኤሱስ" Ἰησοῦς ብሎ አስቀምጦታል፦
ἣν καὶ εἰσήγαγον διαδεξάμενοι οἱ πατέρες ἡμῶν μετὰ Ἰησοῦ ἐν τῇ κατασχέσει τῶν ἐθνῶν ὧν ἐξῶσεν ὁ θεὸς ἀπὸ προσώπου τῶν πατέρων ἡμῶν ἕως τῶν ἡμερῶν Δαυείδ·
Act 7፥45 Which also our fathers that came after brought in with Jesus into the possession of the Gentiles, whom God drave out before the face of our fathers, unto the days of David

ዐማርኛው ላይ "ኢያሱ" እያሉ ሊያስቀይሱ ቢሞክሩም እንግሊዝኛው ላይ ሳያቅማሙ እንቅጩን ፍርጥ አርገው "Jesus" ብለው አስቀምጠውታል፥ ይህ ስም አዲስ ኪዳን ላይም ለብዙ ሰዎች ስም ሆኖ ያገለግል ነበር።
፨ ሲጀመር "ኢየሱስ" የሚለው የፍጡር ስም ባይሆን ኖሮ ፈጣሪ፣ ነቢያት እና ሐዋርያት ለፍጡራን ስም አርገው አይጠቀሙም ነበር።
፨ ሲቀጥል እራሱ ፈጣሪ አብሮት ያልነበረው ከጊዜ በኃላ የፍጡር ስም ይጠቀማል ብሎ ማሰብ ዘበት ነው።
፨ ሢሰልስ ናዝሬት ላይ ከማርያም የተወለደው ልክ እንደ እስማኤል በመልአክ ከጊዜ በኃላ የወጣለት ስም ነው፦
ዘፍጥረት 16፥11 የእግዚአብሔር መልአክም አላት፦ እነሆ አንቺ ፀንሰሻል፥ ወንድ ልጅንም ትወልጃለሽ፤ ስሙንም እስማኤል ብለሽ ትጠሪዋለሽ፥ እግዚአብሔር መቸገርሽን ሰምቶአልና።

ስለዚህ የናዝሬቱ ኢየሱስ ከመወለዱ በፊት "ኢየሱስ" የሚለው የፍጡር ስም ከሆነ ኢየሱስን ማምለክ እራሱ ሺርክ ነው።

ነጥብ ሁለት
"ክርስቶስ"
በብሉይ ግሪክ ሰፕቱጀንት ላይ "ክርስቶስ" χριστός የሚለው እና በብሉይ ዕብራይስጥ ማሶሬቲክ ላይ "መሢሕ מָשִׁיחַ‎ የሚለው የማዕረግ ስም ትርጉሙ "የተቀባ" ወይም "ቅቡዕ" ማለት ሲሆን ይህ ስም ለነቢያት፣ ለካህናት እና ለነገሥታት የሚያገለግል የፍጡር ስም ነው፦
1ኛ ሳሙ 12፥3 እነሆኝ በእግዚአብሔር እና “በመሲሑ” מְשִׁיח֗וֹ ፊት መስክሩብኝ የማንን በሬ ወሰድሁ?
1. ዕብራይስጡ፦
הנני ענו בי נגד יהוה ונגד משיחו את שור מי לקחתי וחמור מי לקחתי ואת מי עשקתי את מי רצותי ומיד מי לקחתי כפר ואעלים עיני בו ואשיב לכם׃
2. ግሪክ ሰፕቱጀንት፦
ἰδοὺ ἐγώ, ἀποκρίθητε κατ᾿ ἐμοῦ ἐνώπιον Κυρίου καὶ ἐνώπιον χριστοῦ αὐτοῦ· μόσχον τίνος εἴληφα ἢ ὄνον τίνος εἴληφα ἢ τίνα κατεδυνάστευσα ὑμῶν ἢ τίνα ἐξεπίεσα ἢ ἐκ χειρὸς τίνος εἴληφα ἐξίλασμα καὶ ὑπόδημα; ἀποκρίθητε κατ᾿ ἐμοῦ, καὶ ἀποδώσω ὑμῖν.

እዚህ አንቀጽ ላይ በግሪኩ ሰፕቱጀንት "ክርስቶስ" χριστός እና በዕብራይስጡ ማሶሬቲክ "መሢሕ מָשִׁיחַ‎ ነቢዩ ሳሙኤል ንጉሥ ሳኦልን የጠራበት ስም መሆኑ አንባቢ ልብ ይለዋል። ፈጣሪ ቀቢ ከሆነ ተቀቢ ፍጡር ነው፥ እግዚአብሔር ኢየሱስን በመንፈስ ቅዱስ ስለቀባው እግዚአብሔር አምላኩ ቀቢ ኢየሱስ ተቀቢ ነው፦
ሐዋ 10፥38 እግዚአብሔር የናዝሬቱን ኢየሱስን በመንፈስ ቅዱስ በኃይልም “ቀባው”፥
ዕብራውያን 1፥9 ጽድቅን ወደድህ ዓመፅንም ጠላህ፤ ስለዚህ "እግዚአብሔር አምላክህ ከጓደኞችህ ይልቅ በደስታ ዘይት ቀባህ"፥ ይላል።

ስለዚህ ኢየሱስ ሆነ ክርስቶስ የፍጡራን የተፀውዖ ወይም የማዕረግ ስም ከሆነ ኢየሱስ ክርስቶስ ፍጡር ነው። ፍጡር ደግሞ በምንም መልኩ አይመለክም፥ ፍጡርን ማምለክ በራሱ ሺርክ ነው። ይህ ዓይን ያስፈጠጠ እና ጥርስ ያስገጠጠ ክህደት ነው፥ እነዚያ የፈጠራቸውን አምላክ አሏህን እርሱ የመርየም ልጅ አልመሲሕ ነው ያሉ በእርግጥ ካዱ፦
5፥17 *እነዚያ አላህ እርሱ የመርየም ልጅ አልመሲሕ ነው ያሉ በእርግጥ ካዱ*፡፡

አሏህ ሂዳያህ ይስጣቸው! ለእኛም ጽናቱን! አሚን።

ከከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ

መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen

ወሠላሙ ዐለይኩም

ወሠላሙ ዐለይኩም
448 views16:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-12 19:57:07
365 views16:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-11 19:39:33
አላህ ቁርአን ለምን "እኛ" ይላል? ክፍል 3

ክፍል 4 ለማግኘት:-

https://vm.tiktok.com/ZMYfQJEt8/

መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
‐‐‐
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
180 views16:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-10 20:27:58 የአጎት እና የአክስት ልጅ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

16፥116 በአላህም ላይ ውሸትን ልትቀጣጥፉ ምላሶቻችሁ በሚመጥኑት ውሸት «ይህ የተፈቀደ ነው፥ ይህም እርም ነው» አትበሉ፡፡ وَلَا تَقُولُوا لِمَا تَصِفُ أَلْسِنَتُكُمُ الْكَذِبَ هَـٰذَا حَلَالٌ وَهَـٰذَا حَرَامٌ لِّتَفْتَرُوا عَلَى اللَّهِ الْكَذِبَ

የአባት ወንድም የሆነ አጎት "ዐም" عَمّ ሲባል የአባት እኅት የሆነች አክስት "ዐማህ" عَمَّة ትባላለች፥ የእናት ወንድም የሆነ አጎት(ሹማ) ደግሞ "ኻል" خَال ሲባል የእናት እኅት የሆነች አክስት(ሹሜ) "ኻላህ" خَالَة ትባላለች። በኢሥላም የአጎት ልጅ ሆነ የአክስት ልጅ ማግባት ሐላል ነው፦
33፥50 እነዚያንም ከአንተ ጋር የተሰደዱትን የአጎትህን ሴቶች ልጆች፣ የአክስቶችህንም ሴቶች ልጆች፣ የየሹማህንም ሴቶች ልጆች፣ የየሹሜዎችህንም ሴቶች ልጆች ማግባትን ለአንተ ፈቅደንልሃል፡፡ يَا أَيُّهَا النَّبِيُّ إِنَّا أَحْلَلْنَا لَكَ أَزْوَاجَكَ اللَّاتِي آتَيْتَ أُجُورَهُنَّ وَمَا مَلَكَتْ يَمِينُكَ مِمَّا أَفَاءَ اللَّهُ عَلَيْكَ وَبَنَاتِ عَمِّكَ وَبَنَاتِ عَمَّاتِكَ وَبَنَاتِ خَالِكَ وَبَنَاتِ خَالَاتِكَ

እዚህ አንቀጽ ላይ "ፈቅደናል" ለሚለው የገባው የግሥ መደብ "አሕለይና" أَحْلَلْنَا ነው፥ የስም መደቡ "ሐላል" حَلَال ሲሆን "የተፈቀደ" ማለት ነው። ሚሽነሪዎች፦ "የአጎት ልጅ ወይም የአክስት ልጅ ማግባት ለምን ተፈቀደ? ብለው እርርና ምርር በማለት ሲንጨረጨሩ እና ሲንተከተኩ ይታያል፥ ለመሆኑ የአጎት ልጅ ወይም የአክስት ልጅ ማግባት ከመነሻው መቼ ክልክል ሆኖ ያውቃል? ባይብል ላይ "ዘመድ" በሚለው ፈርጅ ውስጥ የአጎት ልጅ ወይም የአክስት ልጅ ማግባት አልተካተተም፦
ዘሌዋውያን 18፥6 ከእናንተም ማንም ሰው ኃፍረተ ሥጋውን ይገልጥ ዘንድ ወደ "ዘመዱ" ሁሉ አይቅረብ! እኔ ያህዌህ ነኝ።

ዘሌዋውያን 18፥7-18 ላይ እናት፣ የእንጀራ አባት እናት፣ እኅት፣ ልጅና የልጅ ልጅ፣ አክስት፣ የአጎት ሚስት፣ ምራት(የልጅ ሚስት)፣ የወንድም ሚስት፣ የሚስት እኅት ማግባት ተከልክሏል፥ ቅሉ ግን የአጎት ልጅ ወይም የአክስት ልጅ ማግባት የተከለከለበት ጥቅስ ከዘፍጥረት እስከ ራእይ በባትሪ ብትፈልጉ አታገኙም። ከዚያ ይልቅ የአጎት ልጅ ማግባት የተፈቀደ ነው፥ እንበረም የአጎቱን ልጅ ዮካብድን አግብቶ አሮን እና ሙሴን ወልደዋል፦
ዘጸአት 6፥20 እንበረምም የአጎቱን ልጅ ዮካብድን አገባ፥ አሮን እና ሙሴንም ወለደችለት።

ለሙሴ ኦሪት ከተሰጠ በኃላም ቢሆን በኦሪት ውስጥ የአጎት ልጅ ወይም የአክስት ልጅ ማግባት ከመፈቀዱም አልፎ የተወደደ ሆኗል፥ የሰለጰዓድ ልጆች ማህለህ፣ ቲርጻ፣ ዔግላ፣ ሚልካ፣ ኑዓ ፈጣሪ አዟቸው ከአጎቶቻቸው ልጆች ጋር ተጋብተዋል፦
ዘኍልቍ 36፥10-11 ያህዌህም ሙሴን እንዳዘዘው እንዲሁ የሰለጰዓድ ሴቶች ልጆች አደረጉ። የሰለጰዓድ ልጆች ማህለህ፣ ቲርጻ፣ ዔግላ፣ ሚልካ፣ ኑዓ "ከአባታቸው ወንድሞች ልጆች ጋር ተጋቡ"።

"ከአባታቸው ወንድሞች ልጆች ጋር ተጋቡ" የሚለው ኃይለ-ቃል ይሰመርበት! ይህንን ጥቅስ አፍጦና አፋጦ፤ አግጦና አንጋጦ ስታነቡ ቆሌ ተገፎ እና ቆሽት አሮ፦ "ሰማይ ተንዶ ሊናጫነኝ ነው፥ ምድር ተከፍቶ ሊውጠኝ ነው" እንደምትሉ እሙን ነው። አሏህ ያላለውን በምትመጥኑት ውሸት «ይህ የተፈቀደ ነው፥ ይህም እርም ነው» አትበሉ፦
16፥116 በአላህም ላይ ውሸትን ልትቀጣጥፉ ምላሶቻችሁ በሚመጥኑት ውሸት «ይህ የተፈቀደ ነው፥ ይህም እርም ነው» አትበሉ፡፡ وَلَا تَقُولُوا لِمَا تَصِفُ أَلْسِنَتُكُمُ الْكَذِبَ هَـٰذَا حَلَالٌ وَهَـٰذَا حَرَامٌ لِّتَفْتَرُوا عَلَى اللَّهِ الْكَذِبَ

ስለዚህ "ሰባት ቤት ድረስ ማግባት ክልክል ነው" የሚለው መርሕ ሰው ሠራሽ ሕግ ነው። አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ

መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen

ወሠላሙ ዐለይኩም
316 views17:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-10 20:27:12
293 views17:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-09 21:22:31
አላህ ቁርአን ለምን "እኛ" ይላል? ክፍል 2

ክፍል 3 ለማግኘት:-

https://vm.tiktok.com/ZMYfQJEt8/

መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
‐‐‐
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
154 views18:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-03 20:42:58 4፥172 መሢሑ ለአላህ ባሪያ ከመኾን ፈጽሞ አይጠየፍም፡፡ ቀራቢዎች የኾኑት መላእክትም አይጠየፉም፡፡ እርሱን ከመገዛት የሚጠየፍ እና የሚኮራም ሰው አላህ ሁሉንም ወደ እርሱ በእርግጥ ይሰበስባቸዋል፡፡ لَّن يَسْتَنكِفَ الْمَسِيحُ أَن يَكُونَ عَبْدًا لِّلَّهِ وَلَا الْمَلَائِكَةُ الْمُقَرَّبُونَ ۚ وَمَن يَسْتَنكِفْ عَنْ عِبَادَتِهِ وَيَسْتَكْبِرْ فَسَيَحْشُرُهُمْ إِلَيْهِ جَمِيعًا

ኢየሱስ ከመገዛት የማያቅማማለትን አንዱን አምላክ አሏህን ትገዙ ዘንድ ጥሪያችን ነው። አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ

መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
‐‐‐
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen

ወሠላሙ ዐለይኩም
237 views17:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-03 20:42:58 ገዥ እና ተገዥ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

19፥65 እርሱ የሰማያት እና የምድር በሁለቱም መካከል ላለው ሁሉ ጌታ ነውና ተገዛው፡፡ እርሱን በመገዛትም ላይ ታገስ፡፡ ለእርሱ ሞክሼን ታውቃለህን? رَّبُّ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ وَمَا بَيْنَهُمَا فَاعْبُدْهُ وَاصْطَبِرْ لِعِبَادَتِهِ ۚ هَلْ تَعْلَمُ لَهُ سَمِيًّا

በገዢ እና በተገዢ መካከል ያለው መገዛዛት የአገልግሎት መገዛዛት" functional subordination" እና የባሕርይ መገዛዛት" ontological subordination" ተብሎ ለሁለት ይከፈላል፥ ይህንን ነጥብ በነጥብ እስቲ እንይ፦

ነጥብ አንድ
"የአገልግሎት መገዛዛት"
ለምሳሌ ባል የሚስት ራስ በመሆን ገዥ ሲሆን ሚስት ደግሞ ተገዥ ናት፦
1 ቆሮንቶስ 14፥34 ሴቶች በማኅበር ዝም ይበሉ፤ ሕግ ደግሞ እንደሚል "እንዲገዙ" እንጂ እንዲናገሩ አልተፈቀደላቸውምና።

የትኛው ሕግ? ስንል "ኦሪት" ማለት "ሕግ" ማለት ሲሆን ኦሪት ዘፍጥረት ላይ ባል የሚስት ገዥ እንደሆነ ይናገራል፦
ዘፍጥረት 3፥16 እርሱም "ገዥሽ" ይሆናል።

ባል እና ሚስት በምንነት ሰው ሲሆኑ አንድ ናቸው፥ በማንነት ግን ሁለት ስለሆኑ ሁለት ሰው ናቸው። በመካከላቸው ያለው መገዛዛት የምንነት ሳይሆን የደረጃ መገዛዛት ነው፦
ኤፌሶን 5፥22 ሚስቶች ሆይ! ለጌታ እንደምትገዙ ለባሎቻችሁ ተገዙ!

ሚስት ለባሏ የምትገዛው ለክርስቶስ እንደምትገዛው ነው፥ ክርስቶስ ሰው ሲሆን ሚስት ክርስቶስ በመከተል የምትገዛው በደረጃ መገዛዛት ነው። ምክንያቱም ሚስት እና ባል ሰው ሆነው የኤክሌሲያ ክፍል ናቸው፥ ኤክሌሲያ ለክርስቶስ የምትገዛው የደረጃ መገዛት ነው፦
ኤፌሶን 5፥24 ዳሩ ግን ቤተ ክርስቲያን ለክርስቶስ እንደምትገዛ እንዲሁ ሚስቶች ደግሞ በሁሉ ለባሎቻቸው ይገዙ።

ባል ሚስቱን ክርስቶስ ኤክሌሲያን የሚገዛው በደረጃ መገዛት ነው፥ ካልሆነ ኤክሌሲያ በሚስት ክርስቶስ በባል መመሰሉ ትርጉም የለውም። “ኤክሌሲያ” ἐκκλησία የሚለው የግሪኩ ቃል ከሁለት ቃላት የተዋቀረ ቃል ነው፥ እርሱም “ኤክ” ἐκ ማለትም “ከ” ከሚል መስተዋድድ እና “ካሌኦ” καλέω ማለትም “የተጠራ” ከሚል ግስ ነው። በጥቅሉ “ተጠርተው የወጡ” ማለት ነው፥ ይህ ቋንቋዊ ፍቺው ሲሆን ሙያዊ ፍቺው ደግሞ “ጉባኤ” “ማኅበር” “ስብሰባ” ማለት ነው።
አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ መጽሐፈ ምሥጢር በሚለው መጽሐፉ ላይ ከሚያበሻቅታቸው መ*ና*ፍ*ቃ*ን አንዱ የእስክንድርያውን አርጌንስ ሲሆን አንድ ምዕራፍ ሰጥቶ በምዕራፍ 7 ላይ ይወርፈዋል፥ ሲደመድምም፦ "ልቡ ደካማ እና ኅሊናው የእንስሳ" በማለት ያብጠለጥለዋል፦
መጽሐፈ ምሥጢር 7፥17 "ልቡ ደካማ እና ኅሊናው የእንስሳ የሆነ የአርጌንስ ተግሳጽ ተፈጸመ"

አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ የእስክንድርያው አርጌንስን የሚያነውርበት ምክንያት "አብ የወልድ ገዥ ነው፥ ወልድ የአብ ተገዥ ነው" በማለት ዛሬ የፕሮቴስታንት ሥነ-መለኮት የሚቀበለውም የአገልግሎት መገዛዛት" functional subordination" ስላራመደ ነው።
ነጥብ ሁለት
"የባሕርይ መገዛዛት"
ለምሳሌ ሰው በእንስሳት ላይ ሁሉ ገዥ ነው፦
ዘፍጥረት 1፥28፤ እግዚአብሔርም ባረካቸው፥ እንዲህም አላቸው፦ ብዙ፥ ተባዙ፥ ምድርንም ሙሉአት፥ "ግዙአትም" የባሕርን ዓሦችና የሰማይን ወፎች በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ "ግዙአቸው"።

የሰው ኑባሬ እና የእንስሳ ኑባሬ አንድ አይደለም፥ ሰው በምንነት ሰው እንጂ ድመት፣ ውሻ፣ በግ፣ በሬ አይደለም። እንስሳን ሲገዛ የሚገዛው በባሕርይ ነው፦
መዝሙር 8፥6 በእጆችህም ሥራ ሁሉ ላይ ሾምኸው፤ ሁሉን ከእግሮቹ በታች አስገዛህለት፥
መዝሙር 8፥7-8 በጎችንም ላሞችንም ሁሉ ደግሞም የምድረ በዳውን እንስሶች፥ የሰማይንም ወፎች የባሕርንም ዓሦች፥ በባሕር መንገድ የሚሄደውንም ሁሉ።

"ሁሉን" በሚለው ቃል በጎች፣ ላሞች፣ የምድረ በዳውን እንስሶች፣ የሰማይንም ወፎች፣ የባሕርንም ዓሦች፣ በባሕር መንገድ የሚሄደው ያጠቃልላል፥ ይህ ጥቅስ ስለ ሰው የሚናገር ቢሆንም የዕብራውያን ጸሐፊ ከዚህ ጠቅሶ ለኢየሱስ ይጠቀምበታል፦
ዕብራውያን 2፥8 "ሁሉን ከእግሮቹ በታች አስገዛህለት" ብሎ መሰከረ። ሁሉን ከእርሱ በታች ባስገዛ ጊዜ ያልተገዛለት ምንም አልተወምና። አሁን ግን ሁሉ እንደ ተገዛለት ገና አናይም።

አሁን ግን ሁሉ ማለትም በጎች፣ ላሞች፣ የምድረ በዳውን እንስሶች፣ የሰማይንም ወፎች፣ የባሕርንም ዓሦች፣ በባሕር መንገድ የሚሄደው እንደ ተገዛለት ገና አናይም፥ ግን ዳግም ሲመጣ ሁሉም ከእግሩ በታች ይገዛለታል፦
ኤፌሶን 1፥22 ሁሉንም ከእግሩ በታች አስገዛለት።
1 ቆሮንቶስ 15፥27 ሁሉን ከእግሩ በታች አስገዝቶአልና። ነገር ግን፦ "ሁሉ ተገዝቶአል" ሲል፥ ሁሉን ካስገዛለት በቀር መሆኑ ግልጥ ነው።

አንዱ አምላክ ለክርስቶስ ሁሉን ከእግሩ በታች አስገዝቷል ሲባለው "ሁሉ" በሚለው ቃል ውስጥ ሁሉን ያስገዛለት አንዱን አምላክ አይጨምርም፥ ሁሉ ከተገዛለት በኋላ ኢየሱስ ሁሉን ላስገዛለት ለአንዱ አምላክ ይገዛል፦
1 ቆሮንቶስ 15፥28 ሁሉ ከተገዛለት በኋላ ግን እግዚአብሔር ሁሉ በሁሉ ይሆን ዘንድ በዚያን ጊዜ ልጁ ራሱ ደግሞ ሁሉን ላስገዛለት ይገዛል።

በጎች፣ ላሞች፣ የምድረ በዳውን እንስሶች፣ የሰማይንም ወፎች፣ የባሕርንም ዓሦች፣ በባሕር መንገድ የሚሄደው ለኢየሱስ የሚገዛው የባሕርይ መገዛት ሲሆን ኢየሱስ ፍጡር ስለሆነ ለፈጣሪው የሚገዛው የባሕርይ ነው፦
1 ቆሮንቶስ 11፥3 ነገር ግን የወንድ ሁሉ ራስ ክርስቶስ፥ የሴትም ራስ ወንድ፥ የክርስቶስም ራስ እግዚአብሔር እንደ ሆነ ልታውቁ እወዳለሁ።

"ክርስቶስ" ማለት "የተቀባ" ማለት ነው፥ ይህንን የተቀባ ሰው የቀባው አንዱ አምላክ ሲሆን ይህ አንዱ አምላክ ለዚህ ሰው "ራስ" ከሆነ ይህ መግዛት የባሕርይ ነው። "ራስ" ማለት "ገዥ" ማለት ነው፦
1 ዜና 29፥11 አንተም በሁሉ ላይ ከፍ ከፍ ያልህ ራስ ነህ።

ፈጣሪ በፍጡራኑ ሁሉ ላይ ራስ ከሆነ የእርሱ ገዥነት የባሕርይ እስከሆነ ድረስ በኢየሱስ ላይ የባሕርይ ገዥ ነው፥ እንደ ጳውሎስ እሳቤ መሢሑ በስጦታ እና በጸጋ ያገኘውን የመግዛት ሥልጣን ለሰጠው ማንነት ያስረክባል፦
1 ቆሮንቶስ 15፥24 በኋላም "መንግሥቱን" ለእግዚአብሔር ለአባቱ አሳልፎ "በሰጠ ጊዜ" አለቅነትንም ሁሉና ሥልጣንን ሁሉ ኃይልንም በሻረ ጊዜ፥ ፍጻሜ ይሆናል።

እዚህ ጥቅስ ላይ "በሰጠ ጊዜ" ጊዜ የሚለው ይሰመርበት!! መንግሥትን(መግዛትን) ሲያስረክብ ያኔ እርሱ ራሱ ገዥ ሳይሆን ተገዥ ይሆናል። ኢየሱስ እራሱ የሚገዛው ጌታ ካለው ይህ ጌታ የሰማያት እና የምድር በሁለቱም መካከል ላለው ሁሉ ጌታ ነውና ተገዛው። መሢሑ እራሱ የዓለማቱን ጌታ አሏህን ከመገዛት አይጠየፍም፦
19፥65 እርሱ የሰማያት እና የምድር በሁለቱም መካከል ላለው ሁሉ ጌታ ነውና ተገዛው፡፡ እርሱን በመገዛትም ላይ ታገስ፡፡ ለእርሱ ሞክሼን ታውቃለህን? رَّبُّ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ وَمَا بَيْنَهُمَا فَاعْبُدْهُ وَاصْطَبِرْ لِعِبَادَتِهِ ۚ هَلْ تَعْلَمُ لَهُ سَمِيًّا
240 views17:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-03 20:42:29
228 views17:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ