Get Mystery Box with random crypto!

Tiriyachen | ጥሪያችን

የቴሌግራም ቻናል አርማ tiriyachen — Tiriyachen | ጥሪያችን T
የቴሌግራም ቻናል አርማ tiriyachen — Tiriyachen | ጥሪያችን
የሰርጥ አድራሻ: @tiriyachen
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.91K

Ratings & Reviews

1.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2023-05-05 22:28:18 የነቢያት ስም በቁርኣን

አሰላሙ ዐለይኩም ወራሕመቱላሂ ወበረካቱሁ

ወንድም እህቶቼ እንደምን አላችሁ? ዐፊያ ስራ ቤተሰብ ዲን እንዴት ነው? እስኪ ጉዴን እዩልኝ። በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ውስጥ ያሉ ክለቦችን ብዛት ፣ ወይንም በስፔኑ ላሊጋ ካለሆነም በጣሊያኑ ሴሪአ ያሉትን ክለቦች ሲጠይቁኝ አብዛኛውን በቃሌ አውቃቸዋለሁ 25ቱን የነቢያትን ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ የተጠቀሱትን ግን ተናገር ስባል ክ 10 መዝለል አልችልም። ግን ለምን? ነቢያቱን ማወቄ ለሕይወቴ ሲጠቅመኝ የኳስ ክለቦቹን ግን ማወቄ አይጠቅመኝ አለማወቄ አልጎዳን። እኮ ለምን ነቢያቱን በቃል ማወቅ ተሳነኝ? የ 25 ሰው ስልክ ቁጥሮችን በቃሌ አውቃለሁ። እንዴት የ25ቱን ነቢያት ስም ማወቅ ተሳነኝ። ከዛሬ ጀምሮ ስማቸውን በቃል ለመያዝ ልወስን ቃልም ልግባ አላህም ያግዘኛል። ኢንሻአላህ

የነቢያት ስም ከነ-አመጣጡ

1. አደም(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ9 ሱራዎች በ25 አንቀጾች ውስጥ 25 ጊዜ ተጠቅሷል።

2. ኢድሪስ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ2 ሱራዎች በ2 አንቀጾች ውስጥ 2 ጊዜ ተጠቅሷል።

3. ኑሕ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ30 ሱራዎች በ50 አንቀጾች ውስጥ 50 ጊዜ ተጠቅሷል።

4. ኢብራሒም(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ25 ሱራዎች በ63 አንቀጾች ውስጥ 69 ጊዜ ተጠቅሷል።

5. ሉጥ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ14 ሱራዎች በ27 አንቀጾች ውስጥ 27 ጊዜ ተጠቅሷል።

6. ኢስማዒል(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ8 ሱራዎች በ12 አንቀጾች ውስጥ 12 ጊዜ ተጠቅሷል።

7. ኢስሐቅ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ12 ሱራዎች በ16 አንቀጾች ውስጥ 17 ጊዜ ተጠቅሷል።

8. የዕቁብ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ10 ሱራዎች በ10 አንቀጾች ውስጥ 16 ጊዜ ተጠቅሷል።

9. ሁድ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ3 ሱራዎች በ7 አንቀጾች ውስጥ 7 ጊዜ ተጠቅሷል።

10. ሷሊሕ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ9 ሱራዎች በ25 አንቀጾች ውስጥ ለ 25 ጊዜ ተጠቅሷል።

11. ሹዐይብ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ4 ሱራዎች በ10 አንቀጾች ውስጥ 11 ጊዜ ተጠቅሷል።

12. ሙሳ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ34 ሱራዎች በ131 አንቀጾች ውስጥ 136 ጊዜ ተጠቅሷል።

13. ሀሩን(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ13 ሱራዎች በ20 አንቀጾች ውስጥ ለ 20 ጊዜ ተጠቅሷል።

14. ዳዉድ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ9 ሱራዎች በ16 አንቀጾች ውስጥ ለ 16 ጊዜ ተጠቅሷል።

15. ሱለይማን(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ7 ሱራዎች በ16 አንቀጾች ውስጥ ለ 17 ጊዜ ተጠቅሷል።

16. ኢልያስ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ1 ሱራ በ2 አንቀጾች ውስጥ ለ 2 ጊዜ ተጠቅሷል።

17. አዩብ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ4 ሱራዎች በ4 አንቀጾች ውስጥ ለ 4 ጊዜ ተጠቅሷል።

18. ዩኑስ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ4 ሱራዎች በ4 አንቀጾች ውስጥ ለ 4 ጊዜ ተጠቅሷል።

19. ዩሱፍ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ3 ሱራዎች በ26 አንቀጾች ውስጥ ለ 27 ጊዜ ተጠቅሷል።

20. አል-የሰዕ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ2 ሱራዎች በ2 አንቀጾች ውስጥ ለ 2 ጊዜ ተጠቅሷል።

21. ዙል-ኪፍል(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ2 ሱራዎች በ2 አንቀጾች ውስጥ ለ 2 ጊዜ ተጠቅሷል።

22. ዘከሪያ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ4 ሱራዎች በ6 አንቀጾች ውስጥ ለ 7 ጊዜ ተጠቅሷል።

23. የሕያ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ4 ሱራዎች በ5 አንቀጾች ውስጥ ለ 5 ጊዜ ተጠቅሷል።

24. ዒሳ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ11 ሱራዎች በ25 አንቀጾች ውስጥ ለ 25 ጊዜ ተጠቅሷል።

25. ሙሐመድ(ዐለይሂ ሶላቱ ወስ-ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ4 ሱራዎች በ4 አንቀጾች ውስጥ ለ 4 ጊዜ ተጠቅሷል።

በኡስታዝ አቡ ሃይደር የተዘጋጀ

ጥሪያችን በሁሉም ቦታ
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
463 views19:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-05 22:28:13
386 views19:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-03 19:08:44 አንዳችንም ነገር ከራሱ ማድረግ የማይችል አካል እንዴት ብዬ ነው አምላክ አድርጌ የምይዘው? ደግሞስ የላከኝን ፈቃድ እንጂ ፈቃዴን አልሻም እያለ እንዴት ብዬ ነው መልዕክተኛ ነህ የማልለው? አዎ! እሱ መልዕክተኛ ብቻ ነው። ወገኖች ሆይ! ለነገው ዓለም የሚያዋጣችሁ አንዱንና እውነተኛውን አምላክ አላህን በማምለክ፤ ለእናንተም ጭምር ነቢይና መልዕክተኛ አድርጎ በላካቸው ነቢዩ ሙሐመድ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ስታምኑ ብቻ ነው። መልካም ይሆንላችሁ ዘንድ ካሰባችሁ። እሱም እንዲህ ይላል፡-

…የመጽሐፉም ሰዎች ባመኑ ኖሮ ለእነርሱ የተሻለ በሆነ ነበር። ከእነርሱ አማኞች አሉ። አብዛኞቻቸዉ ግን አመጸኞች ናቸው።

ሱረቱ አሊ-ዒምራን 3፡110

በአላህ አምላክነት፤ በቅዱስ ቁርኣን የአምላክ ቃልነት፤ በነቢዩ ሙሐመድ ነቢይነት የካደና በዛው ክህደቱ የሞተ ሰው ጀነት ለእሱ እርም ናት።

እነዚያ አንቀጾቻችንን ያስተባበሉ ከእርሷም የኮሩ ለእነርሱ የሰማይ ደጃፎች አይከፈቱላቸውም፤ ግመል በመርፌ ቀዳዳ እስከሚገባ ድረስ ገነትን አይገቡም። እንደዚሁም አጋሪዎችን እንቀጣለን።

ሱረቱል አዕራፍ 7፡40

በኡስታዝ አቡ ሀይደር የተዘጋጀ

ጥሪያችን በሁሉም ቦታ
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
495 views16:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-03 19:08:43 ማነው ወፍን የፈጠረው?

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው። ክብርና ምስጋና ለዓለማቱ ጌታ ለአላህ የተገባ ይሁን። የአላህ ሰላምና ውዳሴ የሰው ዘር ታላቅ መሪ ለሆኑት ለነቢዩ ሙሐመድ፤ ለመላው የአላህ መልዕክተኞች፤ የሐቅንም መንገድ በተከተለ ሁሉ ላይ ይሁን።

ሀሰት ሲደጋገም እውነት ይመስላል እንዲሉ ሆነና ከሰብአዊ ፍጡርነት እና ከነቢይነት ውጪ ምንም ድርሻ የሌለውን የመርየምን ልጅ ዒሳን (የአላህ ሰላም በሁለቱም ላይ ይሁን) አምላክ እና ፈጣሪ ለማድረግ የቅጥፈት ዘመቻዎች በየአቅጣጫው እየተደጋገሙ ነው። ከእነዚህም ውስጥ አንዱ “ዒሳ (ዐለይሂ-ሰላም) ወፍን ፈጥሯል” የሚለው ተረት ተረት ነው። እንኳን ወፍን ሊፈጥር ይቅርና ፍጥረተ ዓለሙ እራሱ ቢተባበረውና ቢያግዘው ዝንብ መፍጠር እንኳ አይችልም። ይህ የጌታችን ቃል ነው እንዲህ ይላል።

እናንተ ሰዎች ሆይ! አስደናቂ ምሳሌ ተገለጸላችሁ። ለእርሱም አድምጡት። እነዚያ ከአላህ ሌላ የምትግገዟቸው (ጣዖታት) ዝምብን ፈጽሞ አይፈጥሩም። እርሱን (ለመፍጠር) ቢሰበስቡም እንኳ (አይችሉም)። አንዳችንም ነገር ዝንቡ ቢነጥቃቸው ከእርሱ አያስጥሉትም። ፈላጊውም ተፈላጊውም ደከሙ (ደካሞች ናቸው)።

ሱረቱል ሐጅ 22፡73

ታዲያ ከምን ተነስተው ነው ዒሳን ወፍ እንደፈጠረ ለማሳመን የሚኳትኑት ከተባለም ቀጣዩን ማስረጃ ይሆነናል ያሉትን ጥቅስ እናቅርበውና ምላሹን አብረን እንከታተል፡-

ወደ እሥራኤልም ልጆች መልዕክተኛ ያደርገዋል። (ይላልም) ፡-እኔ ከጌታዬ ዘንድ በተዓምር ወደ እናንተ መጣሁ። እኔ ለእናንተ ከጭቃ አንደ ወፍ ቅርጽ እፈጥራለሁ። በእርሱም እተነፍስበታለሁ። በአላህም ፈቃድ ወፍ ይሆናል። በአላህም ፈቃድ ዕውር ሆኖ የተወለደን፤ ለምጸኛንም አድናለሁ። ሙታንንም አስነሳለሁ። የምትበሉትንና በቤታችሁ የምታደልቡትንም ሁሉ እነግራችኋለሁ። የምታምኑ እንደሆናችሁ ለእናንተ በዚህ ውስጥ በእርግጥ ተዓምር አለበት።

ሱረቱ አሊ-ዒምራን 3፡49

እስኪ መጠነኛ ማብራሪውን አብረን እንከታተል።

ሀ. “ወደ እሥራኤልም ልጆች መልዕክተኛ ያደርገዋል።”

ይህ የሚያስረዳን ዒሳ (ዐለይሂ-ሰላም) መልዕክተኛ መሆኑንና የተላከውም ወደ ቤተ እስራኤል ብቻ እንደሆነ ነው። ከዚህ መልዕክተኝነት ውጪ ሌላ ሚና የለውም። በሌላም አንቀጽ ላይ እንደተነገረው የእሱ መልዕክተኝነት እንዳለፉት መልዕክተኞች የሆነ እንጂ ሌላ እንዳልሆነ ሲናገር እንዲህ ይላል፡-

የመርየም ልጅ አልመሲሕ ከበፊቱ መልዕክተኞች በእርግጥ ያለፉ የሆነ መልዕክተኛ እንጅ ሌላ አይደለም። እናቱም በጣም እውነተኛ ናት። (ሁለቱም) ምግብን የሚበሉ ነበሩ። አንቀጾችን ለእነርሱ (ለከሐዲዎች) እንዴት እንደምናብራራ ተመልከት። ከዚያም (ከእውነት) እንዴት እንደሚመለሱ ተመልከት።

ሱረቱል ማኢዳህ 5፡75

ለ. “እኔ ከጌታዬ ዘንድ በተዓምር ወደ እናንተ መጣሁ።”

በማለት አላህ የዒሳ ጌታው እና አምላኩ የላከው እንደሆነ መስክሯል። ተዓምርንም ያመጣው ከእሱ ዘንድ እንጂ ከራሱ እንዳልሆነም አብሮ ገልጿል። በአምስት የቁርኣን አንቀጾች ላይ አላህ የእሱም የህዝቦቹም ጌታ እንደሆነና እሱ ብቻ መመለክ እንዳለበት አስተምሯል፡-

እነዚያ “አላህ እርሱ የመርየም ልጅ አልመሲሕ ነው” ያሉ በእርግጥ ካዱ። አልመሲሕም አለ “የእስራኤል ልጆች ሆይ! ጌታዬንና ጌታችሁን አላህን ተገዙ።” እነሆ! በአላህ የሚያጋራ ሰው አላህ በእርሱ ላይ ገነትን በእርግጥ እርም አደረገ። መኖሪያውም እሳት ናት። ለበዳዮችም ምንም ረዳቶች የሏቸውም።

ሱረቱል ማኢዳህ 5፡72

ሐ. “እኔ ለእናንተ ከጭቃ አንደ ወፍ ቅርጽ እፈጥራለሁ።”

ቁም ነገሩ እዚህ ጋር ነው ያለው። አማርኛ ማንበብን ለቻለ ሰው አንቀጹ የሚናገረው ስለ ወፍ ቅርጽ እንጂ ሌላ እንዳልሆነ ለመረዳት አያዳግተውም። ዒሳ ከጭቃ “እንደ ወፍ ቅርጽ” እፈጥራለሁ አለ እንጂ፤ መች ወፍ እፈጥራለሁ አለ? ጭቃ አምጥቶ የወፍ ቅርጽ መፍጠር ማንም ሰው ሊያደርገው የሚችል ቀላል ተግባር ነው። ቁም ነገሩ በወፍ ቅርጽ በተሰራው ጭቃ ላይ ህይወትን ዘርቶ የእውነት ወፍ እንዲሆን በማድረግ እንዲበር ማስቻሉ ነው። ታዲያ ዒሳ ይህን አላደረገም ወይ? ከተባለም አንቀጹ ይቀጥልና፡-

መ. “በእርሱም እተነፍስበታለሁ፤ በአላህም ፈቃድ ወፍ ይሆናል።”

በማለት ወፍ አድራጊው የጌታ አላህ ፈቃድና ኃይል እንጂ የዒሳ ችሎታ እንዳልነበር ያሳያል። የታለ ታዲያ ዒሳ ወፍ ፈጠረ የሚለው? የአላህ ፈቃድ ባይኖር ኖሮ ጭቃው ጭቃ እንደሆነ ይቀር ነበር እንጂ መች ወፍ ሆኖ ይበር ነበር? ዒሳ (ዐለይሂ-ሰላም) ጭቃውን አምጥቶ የወፍ ቅርጽ የሰራው እንኳ በራሱ ፍላጎት ሳይሆን በጌታው አላህ ፈቃድ እንደሆነ ቅዱስ ቁርኣን በሱረቱል ማኢዳህ ቁጥር 110 ላይ ይናገራል።

ሠ. “በአላህም ፈቃድ ዕዉር ሆኖ የተወለደን፤ ለምጸኛንም፤ አድናለሁ። ሙታንንም አስነሳለሁ።”

እነዚህም ተአምራት የተከናወኑት አሁንም በአላህ ፈቃድ እንጂ በዒሳ (ዐለይሂ-ሰላም) ችሎታ አይደለም።

ረ. “የምትበሉትንና በቤታችሁ የምታደልቡትንም ሁሉ እነግራችኋለሁ።”

አንዳንድ ወገኖች ይህን ሀሳብ ይዘው ‘ዒሳ ሁሉን እንደሚያውቅ ቁርኣን መሰከረ’ ይሉናል። ሰዎቹ የሚበሉትንና በቤታቸው ያከማቹትን መናገር ሁሉን ማወቅ ሆነ በቃ? ይህ ዕውቀት በጊዜም፣ በቦታም፣ በአይነትም የተገደበ ዕውቀት እንጂ ሁሉን የማወቅ ስልጣን አይደለም። እንዴት የሚሉ ከሆነም፡-
ከጊዜ አንጻር፡- ዒሳ (ዐለይሂ-ሰላም) እየተናገረ ያለው በእርሱ ዘመን ስለነበሩት ህዝቦቹ እንጂ ከእሱ በፊት ስላለፉት ወይም ወደፊት ስለሚመጡት ትውልዶች አይደለም። በወቅቱ የነበረውን ብቻ የሚመለከት ነው።
ከቦታ አንጻር፡- ዒሳ (ዐለይሂ-ሰላም) እየተናገረ ያለው ነቢይ ሆኖ በተላከበት አካባቢ ለነበሩት እስራኤላውያን እንጂ በሌላ አካባቢ ስላሉት ህዝቦች አይደለም። አሁንም ዕውቀቱ ከቦታ አንጻር ግድብ ነው።
ከአይነት አንጻር፡- ዒሳ (ዐለይሂ-ሰላም) እነግራችኋለሁ በማለት እየተናገረ ያለው ስለ መብላቸው ብቻ ነው። ከዛ ውጪ ስለሌላ ነገር አልተናገረም። ታዲያ በምን መልኩ ነው ዒሳ (ዐለይሂ-ሰላም) ሁሉን ያውቃል ብለን ድምዳሜ የምንሰጠው?

ሰ. “የምታምኑ እንደሆናችሁ ለእናንተ በዚህ ዉስጥ በእርግጥ ታምር አለበት።”

በማለት አንቀጹ ይጠናቀቃል። እኛም ምላሻችን፡- አዎ አምነናል! የመርየም ልጅ ዒሳ ሆይ! አንተ ከአላህ ዘንድ በተአምራት የተላክህ የእሱ መልዕክተኛ እንደሆንክ አምነን ተቀብለናል፤ ደግሞም መስክረናል። አምላክ ግን አልነበርክም፣ አይደለህምም፤ ወደፊትም አትሆንም።

ሸ. ወገኖች ሆይ! ኢየሱስ ተአምራትን በራሱ ኃይል ማድረግ እንደማይችል የሚናገሩትን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች የት አድርጋችሁት ነው በእኛ ቅዱስ ቁርኣን ላይ የምትከራከሩን?

ኢየሱስም ቀረበና እንዲህ ብሎ ተናገራቸው። ሥልጣን ሁሉ በሰማይና በምድር ተሰጠኝ።

የማቴዎስ ወንጌል 28፡18

ኢየሱስ ሁሉን ቻይ አምላክ ከሆነ በሰማይና በምድር ያሉ ስልጣኖችን ከማን ነው የተቀበለው? አምላክ ይሰጣል ወይንስ ይቀበላል?

እኔ ከራሴ አንዳች ላደርግ አይቻለኝም፤ እንደ ሰማሁ እፈርዳለሁ ፍርዴም ቅን ነው፥ የላከኝን ፈቃድ እንጂ ፈቃዴን አልሻምና።

ዮሀንስ ወንጌል 5፡30
436 views16:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-03 19:08:30
335 views16:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-02 17:18:10 ስቅለት የመቅደስ መስዋዕትን አላስቀረም

እንደ ክርስቲያኖች እሳቤ መሠረት ሁሉም የእንስሳት መስዋዕትነት በኢየሱስ የመስቀል ላይ መስዋዕትነት አማካኝነት ፍፃሜውን አግኝቷል። ክርስቲያኖች ይህንን መስዋዕትነትም የመስዋዕትነት ሁሉ ቁንጮ እንደሆነ ይገልፁታል። የኢየሱስ መስዋዕትነት ሀጥያትን የሚያሰርይ ከመሆኑ በተጨማሪ ሁሉንም ሀጥያተኛ ሰው ንፁህ የሚያደርግ በመሆኑ ሌላ ተጨማሪ መስዋዕትነት አያስፈልግም። ከዚህ ውጭ መስዋዕት ማድረግ ግን በተለይም እንደ ፕሮቴስቴንት አማኞች መሠረት የኢየሱስን ስቅለት ማጓደል ወይንም ለስቅለቱ “ምስጋና ቢስነት” ነው። በአጭሩ ሲቀመጥም፦

 “ለክርስቲያኑ ማህበረሰብ የእንስሳት መስዋዕትነት በኢየሱስ ሞትና ትንሳኤ አማካኝነት ቁሟል።” [1]

እንዳለመታደል ሁኖ ይህ አመለካከት ግን በጠንካራ ማስረጃ የተደገፈ አይደለም። ይህም ማለት ከኢየሱስ ስቅለት በኃላም ቢሆን በአዲስ ኪዳን የሚታወቁ ቀደምት ተከታዮቹ በቤተ መቅደሱ መስዋዕት ማቅረባቸው ተጠቅሷል። የህጉ ተቃዋሚ ተደርጎ የተሳለው ጳውሎስ ሳይቀር ከኢየሱስ ስቅለትና ትንሳኤ ብዙ አመት በኃላ በኢየሩሳሌም ቤተ መቅደስ የእንስሳት መስዋዕት አቅርቧል። 

በሀዋርያት ስራ 21፥26 እንደተነገረን ጳውሎስና የሱ ሰዎች “የመንፃት ስርአትን” በቤተ መቅደሱ ፈጽመዋል። የመንፃት ስርአት ደግሞ ያለምንም ጥርጥር በውስጡ የእንስሳት መስዋዕትን ያካተተ ነው።  

“ጳውሎስም በማግስቱ ሰዎቹን ይዞ ሄደ፤ አብሮአቸውም የመንጻቱን ሥርዐት ፈጸመ። ከዚያም የመንጻቱ ሥርዐት መቼ እንደሚያ በቃና የእያንዳንዳቸውም መሥዋዕት መቼ እንደሚቀርብ ለማስታወቅ ወደ ቤተ መቅደስ ገባ።”

  — ሐዋርያት 21፥26 (አዲሱ መ.ት)

የመንፃት ስርአት ምንድን ነው? አንቀፁን አስመልክቶ ማብራሪያ የሰጠው ዶ/ር ስኮት ሀን እንዲህ ይላል፦

“ጊዜያዊ የመንፃት ስርአት ከወይን መቆጠብን፣ ፀጉርን መላጨትን እንዲሁም ከአስክሬን ጋር አካላዊ መነካካትን ያቅባል (ዘኁልቁ 6፥1-12) የመንፃት ስርአቱን የሳምንት ንፃትን፣ መደበኛ ፀጉር መላጨትን፣ በመቅደስ ለምግብነት የሚያገልግል የእንስሳት መስዋዕትን ያካተተ ነው (ዘኁልቁ 6:13-21)። ጳውሎስም በ18፥18 ላይ እንዲሁ ተመሳሳይ የመንፃት ስርአትን ፈጽሟል  [2]

የእንስሳት መስዋዕትነት ከስቅለትም በኃላ ቢሆን ቀጥሏል። ይህ የሚጠቁመውም ክርስቲያኖች የኢየሱስን ስቅለት አበይት መስዋዕት አድርገው እንደማይቆጥሩት ነው። 

ጳውሎስ ይህንን አይነት ስርአት አንድ ጊዜ ብቻ አይደለም የፈጸመው እንደ ሀንና ሚች ገለፃ መሠረት ሁለት ጊዜ ፈጽሟል። የሐዋርያት ስራ ምዕራፍ 21 እንዴውም በግልፅ ቋንቋ የመንፃት ስርአቱን ሲፈጽም የእንስሳት መስዋዕት ፈጽሞ እንደነበር ይነግረናል። የዚህ ማስረጃ በዋናነት በኢየሱስ መስዋዕትነት ሳቢያ የመቅደሱ መስዋዕትነት ቀርቷል ለሚለው ጭብጥ ትልቅ ሳንካ ነው። ያ ቢሆን ኑሮ ክርስትናን የተቀበሉ አይሁዶች ስርአቱን ባላስቀጠሉትና ባቆሙት ነበር።. ነገር ግን ያደረጉት በተቃራኒው ነበር። የጥንት ክርስቲያኖች በስርአት ደረጃ ከጳውሎሳዊው ዕሳቤ በተለየ ለሙሴ ህግ የቀረቡ ነበሩ። በፕሪንስተን ቲዮሎጂካል ሴሚናር የሲስተማቲክ ቲዮሎጂ ፕሮፌሰር የሆነው ሀዝል ቶምፕሰን እንዲሁም ዶ/ር ጆርጅ ሃንሲንገር እንደሚያስቀምጡት የጥንት ክርስቲዬኖች በህግ ደረጃ የአይሁድ ህግን የሚከተሉ ነበሩ፦ 

“በመጀመሪያዎቹ የክርስትና ጊዜያት ወቅት ክርስቲያን ለመሆን የአይሁድነት መለያዎች ማቆም አይጠበቅም ነበር።.ጥንታዊ ክርስቲያኖችም በዋናነት የአይሁድን ህግ የሚተገብሩ አይሁዶች ነበሩ። ጳውሎስም እራሱ ይህንን አይነት ክርስትና ሲያወግዝ አናየውም። የሱ ተልዕኮ የነበረውም ከዚህ ክርስትና ጋር መሳ ለመሳ የሚሄድና ህግ ሳያስፈልጋቸውም ክርስቲያን መሆን እንደሚችሉ የሚያሳይ ሌላ አይነት ክርስትናን ማስተዋወቅ ነበር” [3]

ከላይኛው ንግግር የምንወስደው ቁምነገርም ጳውሎሳዊው ክርስትና ከመጀመሪያዎቹ የክርስትና እሳቤዎች ያፈነገጠና አዲስ ቅርጽ የያዘ እንደነበር ነው። የመጀመሪያዎቹ ክርስቲያኖችም በዝንባሌ ደረጃ አይሁድ የነበሩ ሲሆን ያ ማለትም ህግጋትን አጥብቀው የሚይዙና የሚተገብሩ እንደነበሩ ነው። ስለዚህም የጥንት ክርስቲያኖች ለህግጋት ተገዥ ከነበሩ የሚሰጠን ትርጉምም የእንስሳት መስዋዕትነትን ያለምንም ማንገራገር ይፈጽሙ እንደነበር ነው፤ ምክንያቱም የህጉ አንዱ ክፍል ነውና። የሀዋርያት ስራ ምዕራፍ 21 የሚሰጠን መልዕክት እጅግ አስፈላጊ መልዕክት ነው። ከዚህም በተጨማሪ እንደ ሃንሲንገር ገለፃ መሠረት ጳውሎስ ይህንን የአይሁድ ህግ የሚተገብሩ ክርስቲያኖችን ሲቃወም ካልነበረ የእንስሳ መስዋዕትነቱንም የሚቃወምበት ገጠመኝ አይኖርም ማለት ነው። 

ነገር ግን ዋነኛው ጥያቄ የጥንት ክርስቲያኖች ኢየሱስ ለሀጥያታቸው ሲል መስዋዕት መሆኑን ካመኑና የእርሱ መስዋዕትነት የመስዋዕት ሁሉ ቁንጮ መሆኑን የሚቀበሉ ከሆነ ለምን የእንስሳት መስዋዕትን ይፈጽማሉ? የሚለው ነው። የዚህ መልሱ ቀላልና ግልፅ ነው፤ ይኸውም “የኢየሱስ መስዋዕትነት አለምን ማዳኛ የወንጀል ማሰረያ መስዋዕት ነው ብለው አያምኑም ነበር” የሚለው ነው። 

ከዚህም በተጨማሪ ጳውሎስ እራሱ ተግባሩን በመቅደሱ የፈጸመና ከባልደረቦቹ ጋር በመሆን ያስቀጠለ መሆኑ ነው። ይህ ደግሞ ዘመነኛ ክርስቲያኖች በሒደት ካመጡት አመለካከት የተለየ እንደሆነ እንረዳለን። ይህም ማለት በአጭሩ፦

በኢየሱስ የምድር ቆይታ የመጀመሪያ ጊዜያት ላይ የነበሩ ተከታዮቹ ከሚያምኑትና ከተገበሩት የተለየ እንግዳ አመለካከት በዘመናት ሒደት ውስጥ ቅርፅ በመያዝ በአሁኑ የወንጌላውያን እሳቤ ውስጥ እንደሰረፀ እንረዳለን።

(የወንድም ኢብን አንዋርን https://unveiling-christianity.net ድረ ገጽ መሰረት ተደርጎ በትርጉም የቀረበ)

Notes:

[1] n.d. (2001, January 1). When did the animal sacrifices stop and why?. Retrieved from https://bible.org/question/when-did-animal-sacrifices-stop-and-why

[2] Hahn, S. & Mitch, C. (2010). Ignatius Catholic Study Bible: New Testament. San Francisco: Ignatius Press. p. 243

[3] Hunsinger, G. (2015). Conversational Theology: Essays of Ecumenical, Postliberal, and Political Themes, with Special Reference to Karl Barth. London: Bloomsbury T&T Clark. 100

ጥሪያችን በሁሉም ቦታ
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
493 views14:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-02 17:17:50
383 views14:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-30 19:09:46 ጌታ የተባለው እየሱስ ብቻ ነውን ?

በዩሃንስ ወንጌል ምእራፍ 20፡28 ላይ ተጠራጣሪው ቶማስ እየሱስን ጌታዬ አምላኬ ብሎታል። ይህ እየሱስ ፈጣሪ አምላክ መሆኑን ያሳያልን? ከዚህ ቀደም እንዳየነው እየሱስ አንድም ጊዜ አምላክ ነኝ ብሎ አያውቅም፡፡ ነገር ግን መልእክተኛ እና ነብይ መሆኑን በተደጋጋሚ ጊዜ ተናግሯል። እንዲሁም የዘላለም ህይወት አምላክን በብቸኝነት በማመን እና በሱም መልእክተኝነት በማመን መሆኑን ተናግሯል።በዩሃንስ ወንጌል 17፡3 እውነተኛ አምላክ ብቻ የሆንህ አንተን የላክኸውንም እየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘልአለም ሕይወት ናት] ይላል።

ብዙ ክርስትያኖች ዩሃንስ ወንጌል 10፡30ን ጠቅሰው አብ እና እየሱስ አንድ አምላክ ናቸው ይሉናል። ነገር ግን ከ 23 ጀምረን ካነበብነው የአላማ እንጂ የመለኮት አንድነትን እንደማያካትት እንረዳለን።በተጨማሪም እዛው ከዩሃንስ 17፡3 ቀጥለን ካነበብን አንድነታቸው አምላክ ለሱ የሰጠው በጎች የአብም ስለሆነ ፤ አብ ስለሰጠውና ከሱ ሚነጥቅ ስለሌለ ከእየሱስም ከአብም ሚነጥቅ ስለማይኖር በዚህ ረገድ ብቻ አንድ እንደሆኑ ግልጽ ይሆንልናል። ቁጥር ዘ ላይ (... እንደ እኛ አንድ ይሆኑ ዘንድ በስምህ ጠብቃቸው።) የሚለውን ክርስትያኖች እንደሚሉት ዩሃንስ 10፡30 ላይ የመለኮትን አንድነት ካሳየና እየሱስ እና አብ አንድ እንደሆኑት ሃዋርያቱም ከነሱጋ አንድ ከሆኑ ከ 4 በላይ አምላክ ሊኖረን ነው ማለት ነው።

ወደ ዩሃንስ ወንጌል ስንመለስ 10፡30-36 እንዲህ ይነበባል፦ [ እኔና አብ አንድ ነን።አይሁድም ሊወግሩት ደግመው ድንጋይ አነሱ ፡፡ እየሱስ። ከአባቴ ብዙ መልካም ስራ አሳየኋቹ፤ከእነርሱ ስለማናቸው ስራ ትወግሩኛላችሁ?ብሎ መለሰላቸው፡፡አይሁድም፡፡ ስለ መልካም ስራ አንወግርህም፤ስለ ስድብ፤አንተም ሰው ስትሆን ራስህን አምላክ ስለማድረግህ ነው እንጂ ብለው መለሱለት፡፡እየሱስም እንዲህ ብሎ መለሰላቸው። እኔ :: አማልክት ናችሁ አልሁ ተብሎ በህጋችሁ የተጻፈ አይደለምን? መጽሃፉ ሊሻር አይቻልምና እነዚያን የእግዚአብሄር ቃል የመጣላቸውን አማልክት ካላቸው፥የእግዚአብሄር ልጅ ነኝ ስላልሁ እናንተ አብ የቀደሰውን ወደአለምም የላከውን።ትሳደባለህ ትሉታላችሁን?]

ከነዚህ አንቀጾች ብዙ ነገር ማወቅ እንችላለን፡፡ ለምሳሌ ፦

1) የአምላክ ልጅ እንጂ አምላክ ነኝ አለማለቱን። ራሱን የአምላክ ቃል ከሚመጣላቸው ነብያት ጋር ማወዳደሩ እና እነሱ እራሱ እኔ የአምላክ ልጅ ነኝ ከማለቱ በላይ አማልክት መባላቸውን ማንሳቱ እሱም እንደሌሎች ምልእክተኞች መሆኑን ያሳያል።

2) መልእክተኛ መሆኑን፦ በግልጽ ቋንቋ አብ የቀደሰውን ወደአለምም የላከው ፤ በማለት የእግዚአብሄር አብ መልእተኛ መሆኑን መስክሯል።

3) እየሱስ ባቻ ሳይሆን ሁሉም ነብያት አማልክት እንደሚባሉ፦ይህ ግን ከአምላክ ፈጣሪጋ አንድ ናቸው ወይም እኩል ናቸው ማለት አይደለም። 10፡29 አብ ከሁሉም ሰው ይበልጣል።ከእየሱስም አብ ይበልጣል። ዩሀ.14፡28 (መዝ.ዳዊት 82፡6)

አምላክ ሙሴን አምላክ ማለቱንም እንደተጨማሪ ማስረጃ መውሰድ እንችላለን። [ዘጸ.7፡1] እግዚአብሄርም ሙሴን አለው፡፡ እይ፥ እኔ ለፈርዖን አምላክ አድርጌሃለው፤ ወንድምህም አሮን ነቢይ ይሆንልሃል።] ታድያ ሙሴን አምላክ አርጎ እየሱስን ጌታና ክርስቶስ ቢያደርገው ምን ይገርማል?(የሀዋ.ሥራ 2፡36)

ባጠቃላይ በመጽሃፍ ቅዱስ ጌታ እና አምላክ የተባሉት ብዙ ከመሆናቸውም በላይ እየሱስን አምላክ ነው የሚያስብል የተለየ ተአምር የለውም። ከሱ በፊት ያሉት ነብያት ያረጉትን ነገር እሱም እንደነብይ አርጓል።አምላክ ተአምራትን ሰቶ የላከው ሰው ነው።(የሀዋርያት ስራ 2፡22)

{ የመርየም ልጅ ዒሳም፦ “የእስራኤል ልጆች ሆይ! እኔ ከተውራት በፊቴ ያለውን የማረጋግጥ እና ከእኔ ቡሃላ በሚመጣው መልእክተኛ ስሙ አህመድ በሆነው የማበስር ስሆን ወደ እናንተ(የተላክሁ) የአላህ መልእክተኛ ነኝ”…. ቁርዐን 61፡ 6

አምላክ ሰው ሆኗል
ከቼዋን እስታርስ መጽሐፍ የተቀነጨበ

ጥሪያችን በሁሉም ቦታ
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
603 views16:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-30 19:09:16
452 views16:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-29 17:22:59
ጥሪያችን በሁሉም ቦታ
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
543 views14:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ