Get Mystery Box with random crypto!

Tiriyachen | ጥሪያችን

የቴሌግራም ቻናል አርማ tiriyachen — Tiriyachen | ጥሪያችን T
የቴሌግራም ቻናል አርማ tiriyachen — Tiriyachen | ጥሪያችን
የሰርጥ አድራሻ: @tiriyachen
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.91K

Ratings & Reviews

1.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2023-02-20 19:20:02 የማይመገብ አምላክ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

6፥14 *«ሰማያትንና ምድርን ፈጣሪ ከኾነው አላህ እርሱ የሚመግብ የማይመገብም ሲኾን ሌላን አምላክ እይዛለሁን?»* በላቸው፡፡ قُلْ أَغَيْرَ اللَّهِ أَتَّخِذُ وَلِيًّا فَاطِرِ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ وَهُوَ يُطْعِمُ وَلَا يُطْعَم

አምላካችን አላህ የሚመገቡ አካላትን በመፍጠር እርሱ የሁሉም መጋቢ ነው፤ ነገር ግን በተቃራኒው እርሱ ሲሳይን ሰጪ ስለሆነ የማይመገብ አምላክ ነው፦
6፥14 *«ሰማያትንና ምድርን ፈጣሪ ከኾነው አላህ እርሱ የሚመግብ የማይመገብም ሲኾን ሌላን አምላክ እይዛለሁን?»* በላቸው፡፡ قُلْ أَغَيْرَ اللَّهِ أَتَّخِذُ وَلِيًّا فَاطِرِ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ وَهُوَ يُطْعِمُ وَلَا يُطْعَم
51፥57 *ከእነርሱም ምንም ሲሳይ አልፈልግም፡፡ ሊመግቡኝም አልሻም*፡፡ مَا أُرِيدُ مِنْهُم مِّن رِّزْقٍ وَمَا أُرِيدُ أَن يُطْعِمُونِ

በባይብልም አንዱ አምላክ እንደማይመገብ ተገልጿል፦
መዝሙር 50፥12 *ብራብም ለአንተ አልነግርህም፥ ዓለምና ሞላው የእኔ ነውና። የፍሪዳውን ሥጋ እበላለሁን? የፍየሉንስ ደም እጠጣለሁን?*

ፈጣሪ፦ እበላለሁን? እጠጣለሁን? ሲል በምጸታዊ አነጋገር አልበላም አልጠጣም እያለ ነው፤ ከዚያ ይልቅ ሁሉን የሚመግብ ነው፦
መዝሙር 136፥25 *ለሥጋ ሁሉ ምግብን የሚሰጥ*፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።

አምላካችን አላህ መርየምን እና ልጇን ለዓለማት ታምር አድርጓል፤ ነገር ግን እርሱ መልእክተኛ እናቱ ደግሞ እውነተኛ ናቸው እንጂ ከዚያ ያለፈ ደረጃ የላቸውም፤ ሁለቱም እንደማንኛውን ፍጡር ምግብን የሚበሉ ነበሩ፤ መመለክ የሚገባው የሚመግብ የማይመገብ ከማንም ምንም ሲሳይ የማይፈልግ አንድ አምላክ አላህ ብቻ ነው፦
5፥75 *የመርየም ልጅ አልመሲሕ ከበፊቱ መልክተኞች በእርግጥ ያለፉ የኾነ መልክተኛ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡ እናቱም በጣም እውነተኛ ናት፡፡ ሁለቱም ምግብን የሚበሉ ነበሩ*፤ مَّا الْمَسِيحُ ابْنُ مَرْيَمَ إِلَّا رَسُولٌ قَدْ خَلَتْ مِن قَبْلِهِ الرُّسُلُ وَأُمُّهُ صِدِّيقَةٌ ۖ كَانَا يَأْكُلَانِ الطَّعَامَ ۗ انظُرْ كَيْفَ نُبَيِّنُ لَهُمُ الْآيَاتِ ثُمَّ انظُرْ أَنَّىٰ يُؤْفَكُونَ

ኢየሱስ ለሥድስቱ የተፈጥሮ ሕግጋት ይገዛል፤ እነዚህም ሕግጋት፦ መራብ፣ መጠማት፣ መብላት፣ መጠጣት፣ መጸዳዳት እና መሽናት ናቸው። ኢየሱስ እየበላ እና እየጠጣ መጣ፦
ማቴዎስ 11፥19 *የሰው ልጅ እየበላና እየጠጣ መጣ*፥
ሉቃስ 24፥42 እነርሱም *ከተጠበሰ ዓሣ አንድ ቁራጭ፥ ከማር ወለላም ሰጡት፤ ተቀብሎም በፊታቸው በላ*።

ኢየሱስ ይራብ፣ ይጠማ፣ ይበላ እና ይጠጣ ከነበረ፤ ወደ አፍ የሚገባ ሁሉ ወደ ሆድ አልፎ ወደ እዳሪ መጸዳዳት ግድ ይለዋል፦
ማቴዎስ 15፥17 *ወደ አፍ የሚገባ ሁሉ ወደ ሆድ አልፎ ወደ እዳሪ እንዲጣል አትመለከቱምን?*

ፈጣሪ ሰው ሆኖ ይራባል፣ ይጠማል፤ ይበላል፣ ይጠጣል፣ ይጸዳዳል፣ ይሸናል ማለት ለእርሱ የነውርና የጎደሎ ባህርይ ነው፤ የሰማያትና ምድር ጌታ፣ የዙፋኑ ጌታ፣ የማሸነፍ ጌታ ከሚሉት ነገር ሁሉ ጠራ፤ “ከሚሉት” ተብሎ የተቀመጠው ቃል “የሲፉነ” يَصِفُونَ ማለት “ባህርይ ካደረጉለት”they attribute” ነገር ሁሉ የጠራ ነው፦
43፥82 *የሰማያትና ምድር ጌታ የዙፋኑ ጌታ ከሚሉት ነገር ሁሉ ጠራ*። سُبْحَانَ رَبِّ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ رَبِّ الْعَرْشِ عَمَّا يَصِفُونَ
21፥22 *የዐርሹ ጌታ አላህም ከሚሉት ሁሉ ጠራ*። فَسُبْحَانَ اللَّهِ رَبِّ الْعَرْشِ عَمَّا يَصِفُونَ
6:100 *ጥራት የተገባው ከሚሉት ነገር የላቀ ነው*። سُبْحَانَهُ وَتَعَالَىٰ عَمَّا يَصِفُونَ
23:91 *አላህ ከሚመጥኑት ሁሉ ጠራ*። سُبْحَانَ اللَّهِ عَمَّا يَصِفُونَ
37፥180 *የማሸነፍ ጌታ የሆነው ጌታህ ከሚሉት ሁሉ ጠራ*። سُبْحَانَ رَبِّكَ رَبِّ الْعِزَّةِ عَمَّا يَصِفُونَ

ወሒድ ዐቃቤ እሥልምና

መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
‐‐‐
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen

ወሰላሙ አለይኩም
313 views16:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-20 19:19:47
280 views16:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-19 18:04:55 ሑሉል

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኛ በሆነው፡፡

88፥1 ከሁሉ በላይ የኾነውን ጌታህን ስም አሞግሥ፡፡ سَبِّحِ اسْمَ رَبِّكَ الْأَعْلَى

"ሑሉል" حُلُول ማለት "አምላክ ሁሉ ነገር ነው፥ በሁሉ ነገር ውስጥ ነው" የሚል እሳቤ ነው፥ ይህ እሳቤ በኢሥላም ሺርክ ውስጥ ይመደባል። "ፓንቴይዝም"pantheism" የሚለው ቃል የሁለት ቃላት ውቅር ነው፥ "ፓን" እና "ቴዎስ" ከሚሉ ሁለት ቃላት የተዋቀረ ሲሆን "አምላክ ሁሉ ነገር ነው"God is all thing" ማለት ነው።
"ፓን" πᾶν ወይም "ፓስ" πᾶς ማለት "ሁሉ ነገር" ማለት ነው፥ "ፓን" πᾶν ተሳቢ ቅጽል ገላጭ ሲሆን "ፓስ" πᾶς ደግሞ ባለቤት ቅጽል ገላጭ ነው።
"ቴዎን" θεὸν ወይም "ቴዎስ" θεός ማለት "አምላክ" ማለት ነው፥ "ቴዎን" θεὸν ተሳቢ ስም ሲሆን ቴዎስ" θεός ደግሞ ባለቤት ስም ነው።

"አምላክ ሁሉ ነገር ነው፥ በሁሉ ነገር ውስጥ ነው" የሚለው እሳቤ በጥንት ጊዜ በሕንድ፣ በግብፅ፣ በባቢሎን፣ በግሪክ እና በሮም የነበረ አሳብ ነው፥ የሚያሳዝነው ጳውሎስ ከእነዚህ ዐረማዊ እሳቤ ወስዶ አምላክ ሁሉ ነገር እንደሚሆን እና በሁሉ ነገር እንደሚሆን ተናግሯል፦
1 ቆሮንቶስ 15፥28 ሁሉ ከተገዛለት በኋላ ግን አምላክ "ሁሉ" "በሁሉ" ይሆን ዘንድ" በዚያን ጊዜ ልጁ ራሱ ደግሞ ሁሉን ላስገዛለት ይገዛል። ὅταν δὲ ὑποταγῇ αὐτῷ τὰ πάντα, τότε καὶ αὐτὸς ὁ Υἱὸς ὑποταγήσεται τῷ ὑποτάξαντι αὐτῷ τὰ πάντα, ἵνα ᾖ ὁ Θεὸς πάντα ἐν πᾶσιν.

እዚህ አንቀጽ ላይ "ሁሉ" ለሚለው የገባው ቃል "ፓንታ" πάντα ሲሆን "ሁሉ ነገር"all thing" ማለት ነው፥ "አምላክ ሁሉ ነገር ይሆን ዘንድ" "አምላክ በሁሉ ነገር ይሆን ዘንድ" የሚለው አሳብ ከጥንቱ ፓጋን የተቀዳ ነው። "ፈጣሪ በሁሉ ነገር ውስጥ ይገኛል" የሚለው እሳቤ "ምሉዕ በኲለሄ" ይሉታል፥ እንደ ክርስትናው "ፈጣሪ መንፈስ ነው፥ በመንፈሱ ሁሉን የሞላ ነው" ይላሉ። በመንፈሱ ሁሉም ነገር ውስጥ ካለ "የጌታ መንፈስ ባለበት በዚያ አርነት አለ" ስለሚል ጠንቋይ ቤት፣ ድግምት ቤት፣ ሰይጣን ውስጥ እና የሰይጧን ቤት ካለ በእነዚያ ቦታ አርነት አለን?
2 ቆሮንቶስ 3፥17 ጌታ ግን መንፈስ ነው፥ የጌታም መንፈስ ባለበት በዚያ አርነት አለ።

አምላክ ብርሃን ነው ጨለማም በእርሱ ዘንድ ከቶ የለም፥ አምላክ ሁሉም ቦታ ውስጥ ካለ የመንፈሳዊ ጨለማ ሆነ የሌሊት ጨለማ እና ሰይጣን እንዴት ሊኖሩ ቻሉ?
1 ዮሐንስ 1፥5 አምላክ ብርሃን ነው ጨለማም በእርሱ ዘንድ ከቶ የለም።
መዝሙር 139፥12 ጨለማ በአንተ ዘንድ አይጨልምምና፥ ሌሊትም እንደ ቀን ታበራለችና፥ እንደ ጨለማዋ እንዲሁ ብርሃንዋ ነው።

"አምላክ ሁሉ ነገር ውስጥ አለ" ሲባል የሴት ብልት ውስጥ፣ የሴት ማኅፀን ውስጥ፣ የሰው ሆድ ውስጥ፣ ሽንት ቤት እና ሰይጣን ውስጥ አለን? "አምላክ ሁሉ ነገር ውስጥ አለ" ከተባለ ሰው በጥፊ ሲመታ መለኮት በሥጋ ተመታ እንላለልን? አምላክ ሥጋ ሆነ እና በሥጋ ተደበደበ፣ ተራበ፣ ተጠማ፣ ሞተ የሚባለው ትምህርት "ኢቲሓድ" اِتِّحَاد ሲባል በክርስትናው ተሠግዎት"incarnation" ይባላል፥ ይህ ትምህርት ከሑሉል የተቀዳ ሲሆን ሺርክ ነው።

አምላካችን አሏህ ፈጣሪ ነው፥ ከፍጥረቱ ጋር በባሕርያቱ ግኑኝነት ቢኖረውም ከፍጥረቱ ውጪ የሚኖር ነው። በፍጥረቱ ውስጥ የለም፥ ፍጥረቱን ያካበበ እንጂ በፍጥረቱ ውስጥ የተካበበ አይደለም። እርሱ ከፍጥረቱ መካከል ማንንም አይመስልም፥ እርሱ ሁሉ ነገር ወይም በሁሉ ነገር ውስጥ ሳይሆን ከሁሉ ነገር በላይ ያለ አምላክ ነው፦
88፥1 ከሁሉ በላይ የኾነውን ጌታህን ስም አሞግሥ፡፡ سَبِّحِ اسْمَ رَبِّكَ الْأَعْلَى

"አምላክ ሁሉ ነገር ነው፥ በሁሉ ነገር ውስጥ ነው" የሚሉትን አሏህ ሂዳያህ ይስጣቸው! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ

መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
‐‐‐
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen

ወሠላሙ ዐለይኩም
184 views15:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-19 18:04:32
180 views15:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-18 20:22:43 አስገራሚ የመፅሀፍ "ቅዱስ" አንቀፆች

አስፀያፊ አንቀፆች

እነኝህ ቃላት አይደለም አምላክ ሊናገራቸውና የሰው ልጅ እንኳን ሊጠራቸው የሚያሳቅቁ ናቸው፡፡

❖ የሴት ልጅ ጡት

ወሲባዊ በሆነ መልኩ የሴት ልጅ ጡት ባይብል ውስጥ በተደጋጋሚ ተጠቅሶ እናገኘዋለን፡፡ ለአብነት ጥቂቶችን እንግለፅ

➊ (መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን ምዕ. 1)
----------
13፤ ውዴ ለእኔ #በጡቶቼ መካከል እንደሚያርፍ እንደ ተቋጠረ ከርቤ ነው።

14፤ ውዴ ለእኔ በዓይንጋዲ ወይን ቦታ እንዳለ እንደ አበባ እቅፍ ነው።

15፤ ወዳጄ ሆይ፥ እነሆ፥ ውብ ነሽ፤ እነሆ፥ አንቺ ውብ ነሽ፤ ዓይኖችሽም እንደ ርግቦች ናቸው።

16፤ ውዴ ሆይ፥ እነሆ፥ አንተ ውብ ነህ፥ መልከ መልካምም ነህ፤ አልጋችንም ለምለም ነው።


(መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን ምዕ. 4)
----------
5፤ ሁለቱ #ጡቶችሽ መንታ እንደ ተወለዱ፥በሱፍ አበባ መካከል እንደሚሰማሩእንደ ሚዳቋ ግልገሎች ናቸው።

6፤ ቀኑ እስኪነፍስ ጥላውም እስኪያልፍ ድረስ፥ወደ ከርቤው ተራራ ወደ ዕጣኑም ኮረብታ እሄዳለሁ።

7፤ ወዳጄ ሆይ፥ ሁለንተናሽ ውብ ነው፥ነውርም የለብሽም።

8፤ ሙሽራዬ ሆይ፥ ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነዪ፤ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነዪ፤ከአማና ራስ ከሳኔርና ከኤርሞን ራስ፥ከአንበሶች መኖሪያ ከነብሮችም ተራራ ተመልከች።

9፤ እኅቴ ሙሽራ ሆይ፥ ልቤን በደስታ አሳበድሽው፤አንድ ጊዜ በዓይኖችሽ፥ ከአንገትሽ ድሪ በአንዱልቤን በደስታ #አሳበድሽው።

➌ " በእርሻ ላይ እንዳለ ቡቃያ አበዛሁሽ፥ አንቺም አደግሽ ታላቅም ሆንሽ፥ በእጅጉም አጌጥሽ፤ ጡቶችሽም አጐጠጐጡ ጠጕርሽም አደገ፥ ነገር ግን ዕርቃንሽን ሆንሽ፥ ተራቍተሽም ነበርሽ። "
(ትንቢተ ሕዝቅኤል 16:7)

ስለዚህ የሚያወሩ አንቀፆች ብዙ ስለሆኑ ሁሉንም መዘርዘሩ ይከብዳል አንቀፁን ብቻ ሰጥቸ ልለፍ፡፡

መኃልየ መኃልየ ዘሰለሞን 7:4 ; 7:8; 8:10

❖ የእግዚአብሄር "ሚስቶች"

በህዝቅኤል ትንቢት እንደተገለፀው እግዚአብሄር ሁለት ሚስቶች ነበሩት፤ እስኪ ሙሉ ታሪኩን ህዝቅኤል እራሱ ይንገረን፡፡

(ትንቢተ ሕዝቅኤል ምዕ. 23)
----------
1፤ የእግዚአብሔር ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ።

2፤ የሰው ልጅ ሆይ፥ የአንዲት እናት ልጆች የሆኑ ሁለት ሴቶች ነበሩ።

3፤ በግብጽም አመነዘሩ፥ በኰረዳነታቸው አመነዘሩ፤ በዚያ #ጡቶቻቸው ምዋሸሹ በዚያም የድንግልናቸውን ጡቶች ዳበሱ።

4፤ ስማቸውም የታላቂቱ ኦሖላ የእኅትዋም ኦሖሊባ ነበረ፥ ለእኔም ሆኑ ወንዶችና ሴቶች ልጆችንም ወለዱ። ስማቸውም ኦሖላ ሰማርያ ናት፤ ኦሖሊባ ደግሞ ኢየሩሳሌም ናት።

5፤ ኦሖላም ገለሞተችብኝ፥ ውሽሞችዋንም ጎረቤቶችዋን አሦራውያንን በፍቅር ተከተለቻቸው።

6፤ እነርሱም ሰማያዊ ሐር የለበሱ አለቆችና ሹማምቶች፥ መልከ መልካሞች ጐበዛዝት፥ በፈረስ ላይ የሚቀመጡ ፈረሰኞች ነበሩ።

7፤ ግልሙትናዋንም ከተመረጡ ከአሦር ሰዎች ሁሉ ጋር አደረገች፥ በፍቅር በተከተለቻቸውም ጣዖቶቻቸው ሁሉ ረከሰች።

8፤ በግብጽም የነበረውን ግልሙትናዋን አልተወችም፤ በዚያ በኰረዳነትዋ ጊዜ ከእርስዋ ጋር ተኝተው ነበር፥ የድንግልናዋንም #ጡቶች ዳብሰው ነበር፥ ግልሙትናቸውንም አፍስሰውባት ነበር።

❖ የወንድ ልጅ ብልት

ይሄኛው ደግሞ እጅግ አሳፋሪ ከመሆኑ የተነሳ ለመንፈሳዊ ሰው ይፅፈው ዘንድ እራሱ ይከብዳል፤ እንዲህ ይነበባል

" #ቍላው የተቀጠቀጠ ብልቱም የተቈረጠ ወደ እግዚአብሔር ጉባኤ አይግባ። "
(ኦሪት ዘዳግም 23:1)

❖ ማጠቃለያ

እንግዲህ እነኝህ አንቀፆች አይደለም ከአምላክ ይቅርና ከቅዱሳን ሰዎች እንኳን ቢሠማ ያሰቅቃል፡፡ አምላክ ደግሞ ከማንም በላይ ቅዱስ ነውና ከሱ እንዲህ አይነት ወሲብ ቀስቃሽ ፁሁፎችን አንጠብቅም እናም እመኑኝ መፅሀፍ "ቅዱስ" የግለሰብ ድርሰት የተቀላቀለበት ፁሁፍ እንጅ ንጹህ የአምላክ ቃል አይደለም፡፡

አሏሁ አዕለም!!!
የሕያ ኢብኑ ኑህ

መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
‐‐‐
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
406 views17:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-18 20:22:30
342 views17:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-17 18:24:43 https://vm.tiktok.com/ZMYk2r37D/
 
ቲክቶክ ቻነላችን ላይ አዲስ ቪዲዬ


መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
‐‐‐
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
346 views15:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-15 20:03:55
ጥያቄዎቻችን - ዘፍጥረት

በተመሳሳይ አትክልቶች በሶስተኛው ቀን እንደተፈጠሩ ይገልፃል (ዘፍጥረት 1:11) የሚገርመው ደግሞ ለአትክልቶች ህልውና አስፈላጊና መሠረት የሆነው ፀሀይ ደግሞ ቆይቶ እንደተፈጠረ ይገልፃል (ዘፍጥረት 1:14-19)

ጥያቄ 1- አትክልቶች ካለ ፀሀይ ብርሀን እንዴት ሊኖሩ ቻሉ?

ጥያቄ 2- የዘፍጥረቱ ፀሀፊ ለአትክልት እድገት Photosynthesis አስፈላጊ እንደሆነ አያቅም ነበር?

የሕያ ኢብኑ ኑህ - Yahya Ibnu Nuhe

መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
‐‐‐
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
228 views17:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-15 15:15:02 https://vm.tiktok.com/ZMYhNvtmH/
 
ቲክቶክ ቻነላችን ላይ አዲስ ቪዲዬ


መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
‐‐‐
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
249 views12:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-14 23:02:48 የቫላንታይን ቀን

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

3፥31 በላቸው፡- «አላህን የምትወዱ እንደኾናችሁ ተከተሉኝ፤ አላህ ይወዳችኋልና፡፡ ኀጢኣቶቻችሁንም ለናንተ ይምራልና፡፡ አላህም መሓሪ አዛኝ ነው፡፡» قُلْ إِن كُنتُمْ تُحِبُّونَ اللَّهَ فَاتَّبِعُونِي يُحْبِبْكُمُ اللَّهُ وَيَغْفِرْ لَكُمْ ذُنُوبَكُمْ ۗ وَاللَّهُ غَفُورٌ رَّحِيمٌ

በክርስትና ታሪክ ውስጥ ቫለንቲኑስ ተብለው የሚጠሩ ሁለት ሰዎች ሲሆኑ ከሁለቱ የመጀመሪያው በ 100 ድኅረ ልደት ግብፅ ተወልዶ በ 160 ድኅረ ልደት ቆጵሮስ የሞተው ቫለንቲኑስ የኖስቲስ መሪ የነበረው የቴዎዳስ ተማሪ ነው፥ ቫለንቲኑስ “ኢየሱስ የማርያም ዘር አይደለም” የሚል አቋም ያለው ሲሆን የእርሱ ተማሪዎች ቫለንቱሳውያን ይህንን አቋም በጥንት ጊዜ ያራምዱ ነበር።
ሁለተኛው ደግሞ በ 226 ልደት ተወልዶ በ 269 ድኅረ ልደት በሮሙ ንጉሥ በክላውዲዮስ ዘመን የተሠዋው ሰማዕት ነው፥ ይህ ሰው በዘመነ ሰማዕታት ጊዜ እንደ ጎርጎሮሳውያን አቆጣጠር የካቲት 14 ቀን 269 ድኅረ ልደት ሰማዕት ሆኗል። እርሱ የሞተበትን ቀን በምዕራባውያን ካቶሊክ የካቲት 14 ቀን ሲዘከር በምሥራቃውያን ኦርቶዶክስ ደግሞ ሰኔ 6 ይዘከራል፥ ሰማዕቱ ቫለንቲኑስ በሕይወት ዘመኑ ወቅት የሮም መንግሥት ወታደሮች እንዳያገቡ ሲከለክል እርሱ ግን የሚፋቀሩትን ይድር ነበር፥ በዚህም ንጉሡ ክላውዲዮስ አቂሞበት ነበርና በወቅቱ "ጣዖት አላመልክም" በማለት ሰማዕት ሆኗል።

በዘመናችን ያሉ ሰዎች የቫላንታይን ቀን እያሉ በዓመት አንዴ የካቲት 14 ቀን የሚያከብሩት የፍቅረኛሞች ቀን መሠረቱ ይህ ነው፥ "ቫላንታይን"Valentine" የሚለው ቃል እራሱ "ቫለንቲኑስ" ከሚባለው የክርስትና ሰማዕት እንደመጣ አንባቢ ልብ ይለዋል። እንደ ኢሥላም አስተምህሮት የምናከብረው ዓመታዊ በዓል ሁለት ብቻ እና ብቻ ነው፥ እነርሱም ዒዱል ፊጥር እና ዒዱል አድሓ ናቸው፦
ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 8, ሐዲስ 121
ዓኢሻህ”ረ.ዐ.” እንደተረከችው የአላህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ “ዒዱል ፊጥር ሰዎች ጾም የሚፈቱበት ነው፥ ዒዱል አድሓ ደግሞ መሥዋዕት የሚያቀርቡበት ቀን ነው”። عَنْ عَائِشَةَ، قَالَتْ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ الْفِطْرُ يَوْمَ يُفْطِرُ النَّاسُ وَالأَضْحَى يَوْمَ يُضَحِّي النَّاسُ ‏”‏

“ዒድ” عِيد የሚለው ቃል “ዓደ” عَادَ ማለትም “ተመላለሰ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ምልሰት” ማለት ነው፥ ይህ “መደሰቻ” ወይም “በዓል” በየዓመቱ ስለሚመላለስ ይህንን ስያሜ አግኝቷል። አሏህን የምንወድ እንደሆንን ተወዳጁ ነቢያችንን"ﷺ" እንከተል፦
3፥31 በላቸው፡- «አላህን የምትወዱ እንደኾናችሁ ተከተሉኝ፤ አላህ ይወዳችኋልና፡፡ ኀጢኣቶቻችሁንም ለናንተ ይምራልና፡፡ አላህም መሓሪ አዛኝ ነው፡፡» قُلْ إِن كُنتُمْ تُحِبُّونَ اللَّهَ فَاتَّبِعُونِي يُحْبِبْكُمُ اللَّهُ وَيَغْفِرْ لَكُمْ ذُنُوبَكُمْ ۗ وَاللَّهُ غَفُورٌ رَّحِيمٌ

በተረፈ ከክርስትና ሾልኮ የመጣውን የቫላንታይን ቀን ከማክበር ሆነ ከማስከበር እንጠንቀቅ! የቫላንታይን ቀን ማክበር እና ማስከበር ግልጽ ፈሣድ ነው። አሏህ በኢሥላም ስም ፈሣድ ከሚያስፋፉ ሙፍሢዲን ይጠብቀን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
‐‐‐
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen

ወሠላሙ ዐለይኩም
293 viewsedited  20:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ