Get Mystery Box with random crypto!

Tiriyachen | ጥሪያችን

የቴሌግራም ቻናል አርማ tiriyachen — Tiriyachen | ጥሪያችን T
የቴሌግራም ቻናል አርማ tiriyachen — Tiriyachen | ጥሪያችን
የሰርጥ አድራሻ: @tiriyachen
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.91K

Ratings & Reviews

1.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8

2023-02-28 21:16:56 የድምፅ ትምህርት |

ሪዝቅ፣ ሲሳይን ሰጪ ማነው?

ሚሽነሪዎች ይህንን የቁርአን አንቀጽ
“እነዚያ ከአላህ ሌላ የምታመልኳቸው ለእናንተ ሲሳይን ሊሰጧችሁ አይችሉም”
ይላልና ፍጡራን እንዴት “ሲሳይ ሰጪዎች” እንዴት ተባሉ? የሚል ጥያቄ ያነሳሉ!
ምላሹን እነሆ!

#Tiriyachen
#ንፅፅር_ሐይማኖት

በኡስታዝ ወሒድ ዑመር

መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
‐‐‐
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
397 views18:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-28 20:58:29 https://vm.tiktok.com/ZMYUgunM1/
 
ቲክቶክ ቻነላችን ላይ አዲስ ቪዲዬ


መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
‐‐‐
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
414 views17:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-26 21:14:45 ፍች በባይብል

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

4፥35 *"እናንተ ዋቢዎች የመካከላቸውንም ጭቅጭቅ ብታውቁ ከቤተሰቦቹ ሽማግሌን ከቤተሰቦችዋም ሽማግሌን ላኩ፡፡ ማስታረቅን ቢሹ አላህ በመካከላቸው ያስማማል"*፡፡ አላህ ግልጽን ዐዋቂ ውስጥንም ዐዋቂ ነውና፡፡ وَإِنْ خِفْتُمْ شِقَاقَ بَيْنِهِمَا فَابْعَثُوا حَكَمًا مِّنْ أَهْلِهِ وَحَكَمًا مِّنْ أَهْلِهَا إِن يُرِيدَا إِصْلَاحًا يُوَفِّقِ اللَّهُ بَيْنَهُمَا ۗ إِنَّ اللَّهَ كَانَ عَلِيمًا خَبِيرًا

በሙሴ ሕግ አንድ ወንድ አንድ ሴት መፍታት የሚችለው የፍችዋን ወረቀት በመስጠት ነው፦
ዘዳግም 24፥1 *ሰው ሴትን ወስዶ ቢያገባ፥ የእፍረት ነገር ስላገኘባት በእርሱ ዘንድ ሞገስ ባታገኝ፥ ”የፍችዋን ጽሕፈት ጽፎ በእጅዋ ይስጣት፥ ከቤቱም ይስደዳት”*።
ዘዳግም 24፥3 *"ሁለተኛውም ባል ቢጠላት፥ “የፍችዋንም ጽሕፈት ጽፎ በእጅዋ ቢሰጣት”፥ ከቤቱም ቢሰድዳት፥ ወይም ሚስት አድርጎ ያገባት ሁለተኛው ባልዋ ቢሞት"*።

ነገር ግን በአዲስ ኪዳን አንድ ወንድ አንድ ሴት መፍታት የሚችለው ዝሙት ስትሠራ ብቻ ነው፦
ማቴዎስ 5፥31-32 *"ሚስቱን የሚፈታት ሁሉ የፍችዋን ጽሕፈት ይስጣት ተባለ። እኔ ግን እላችኋለሁ፥ ያለ ዝሙት ምክንያት ሚስቱን የሚፈታ ሁሉ አመንዝራ ያደርጋታል፥ የተፈታችውንም የሚያገባ ሁሉ ያመነዝራል"*።
ማቴዎስ 19:9 እኔ ግን እላችኋለሁ *"ያለ ዝሙት ምክንያት ሚስቱን ፈትቶ ሌላዪቱን የሚያገባ ሁሉ ያመነዝራል፥ የተፈታችውንም የሚያገባ ያመነዝራል አላቸው"*።

አንዲት ሴት በጠባይ አለመግባባት ቢኖር ወይም የፍቅር አለመጣጣም ቢኖር በዝሙት ካልሆነ መፈታት አትችልም። ከዚህ ሁሉ የሚገርመው ሚስቱን ፈትቶ ሌላ የሚያገባ አመንዝራ መባሉ ብቻ ሳይሆን የተፈታችው ሴት እርሱ በፈታት ሌላ ሰው እንዳያገባት እቀባ ተጥሎባታል፥ የተፈታች ሴት ሌላ ወንድ ካገባት አመንዝራ ይባላል። ሚስቱን ፈትቶ ሌላዪቱን የሚያገባ ሁሉ ያመነዝራል፥ “የተፈታችውንም የሚያገባ ያመነዝራል አላቸው” የሚለው ኃይለ-ቃል ይሰመርበት። እና ምን ትሆናለች? ሲባል ባልዋ እስኪሞት ድረስ ምንን ማግባት አትችልም፦
ሮሜ 7፥2-3 *"ያገባች ሴት ባልዋ በሕይወት ሲኖር ከእርሱ ጋር በሕግ ታስራለችና”፤ ባልዋ ቢሞት ግን ስለ ባል ከሆነው ሕግ ተፈትታለች። ”ስለዚህ ባልዋ በሕይወት ሳለ ለሌላ ወንድ ብትሆን አመንዝራ ትባላለች”፤ ባልዋ ቢሞት ግን ከሕጉ አርነት ወጥታለችና ለሌላ ወንድ ብትሆን አመንዝራ አይደለችም"*።

ልብ አድርጉ “ባልዋ በሕይወት ሳለ ለሌላ ወንድ ብትሆን አመንዝራ ትባላለች” ባልዋ ቢሞት ግን ከሕጉ አርነት ወጥታለችና ሌላ ወንድ ማግባት ትችላለች። በተለይ የኢሥላምን ሕግ በምዕራባውያን ሚዛን ለሚመዝኑ ክርስቲያኖች ምን ይውጣቸው ይሆን? ዛሬስ በአገራችን ይህ የአዲስ ኪዳን ሕግ ይኖር ይሆን? ፍርድ ቤቱን ያጨናነቀው የክርስቲያኑን ፍቺ ያለ ዝሙት ነው። ከዚህ ሁሉ የሚገርመው ኢየሱስ ባል ሚስቱ ያለ ዝሙት ምክንያት ከፈታ አመንዝራ ነው ሲል ጳውሎስ ደግሞ በተቃራኒው ሚስት ከባልዋ መለያየት ትችላለች ግን ሌላ ወንድ ሳታገባ ትኑር በማለት ይቃረናል፦
1ኛ ቆሮንቶስ 7፥10-11 *"ሚስትም ከባልዋ አትለያይ፥ ”ብትለያይ ግን ሳታገባ ትኑር”*።

ሲጀመር ”ብትለያይ ግን ሳታገባ ትኑር” ማለት “ያለ ዝሙት ምክንያት ሚስቱን ፈትቶ ሌላዪቱን የሚያገባ ሁሉ ያመነዝራል” ከሚለው ጋር አይጋጭም? ሲቀጥል “ሳታገባ ትኑር” ፍትሐዊ ብይን ነውን? ሢሰልስ ” ባልዋ በሕይወት ሳለ ለሌላ ወንድ ብትሆን አመንዝራ ትባላለች” መባሉስ አግባብ ነውን? ጳውሎስን፦ "ይህንን ትምህርት በአንተ የሚናገረው ጌታ ነውን ወይስ እራስክ? ስንለው "እኔ እላለሁ፥ ጌታም አይደለም" ይለናል። ቀጥለን፦ "አንተስ ብትሆን የምትናገረው ጌታ ተናገር ብሎ አዞህ ነው ወይስ በሞኝነት? ስንለው አይ "የምናገረው በሞኝነት እንጂ ጌታ እንዳዘዘኝ አልናገርም" ይለናል፦
1 ቆሮንቶስ 7፥12 *"ሌሎችንም እኔ እላለሁ፥ ጌታም አይደለም"*።
2 ቆሮንቶስ 11፥17 እንደዚህ ታምኜ ስመካ የምናገረው በሞኝነት እንጂ ጌታ እንዳዘዘኝ አልናገርም።

ባሏ ከሞተስ? ትሉ ይሆናል፥ ባሏ ሲሞት ደግሞ መከራዋ አላለቀም። የባሏን ወንድም ታግባ የሚል ወፍራም ትእዛዝ ይጠብቃታል፦
ዘዳግም 25፥5-10 *"ወንድማማቾች በአንድነት ቢቀመጡ፥ አንዱም ልጅ ሳይኖረው ቢሞት፥ “”የሞተው ሰው ሚስት ሌላ ሰው ታገባ ዘንድ ወደ ውጭ አትሂድ፤ ነገር ግን የባልዋ ወንድም ወደ እርስዋ ገብቶ እርስዋን ያግባ””፥ ከእርስዋም ጋር ይኑር። የምዋቹ ስም ከእስራኤል ዘንድ እንዳይጠፋ ከእርስዋ የሚወለደው በኵር ልጅ በሞተው በወንድሙ ስም ይጠራ። ያም ሰው የወንድሙን ሚስት ማግባት ባይወድድ፥ ዋርሳይቱ በበሩ አደባባይ ወደሚቀመጡ ሽማግሌዎች ሄዳ፦ ዋርሳዬ በእስራኤል ዘንድ ለወንድሙ ስም ማቆም እንቢ አለ፤ ከእኔ ጋር ሊኖርም አልወደደም ትበላቸው። የከተማውም ሽማግሌዎች ጠርተው ይጠይቁት፤ እርሱም በዚያ ቆሞ፦ አገባት ዘንድ አልወድድም ቢል፥ ዋርሳይቱ በሽማግሌዎቹ ፊት ወደ እርሱ ቀርባ፦ የወንድሙን ቤት በማይሠራ ሰው ላይ እንዲህ ይደረግበታል ስትል ጫማውን ከእግሩ ታውጣ፥ በፊቱም እንትፍ ትበልበት። በእስራኤልም ዘንድ ስሙ የጫማ ፈቱ ቤት ተብሎ ይጠራ*።

“ያም ሰው የወንድሙን ሚስት ማግባት ባይወድድ” ስሙ የጫማ ፈቱ ቤት ተብሎ ይጠራ እንጂ በግድ አግባ አይባልም። እርሷን ግን እርሷ የሞተው ሰው ሚስት ሌላ ሰው ታገባ ዘንድ ወደ ውጭ አትሂድ ተብሎ ታዟል እንጂ እንደ ወንዱ የፈለገችውን ማግባት አትችልም። ይህ እኩልነት ነውን? ከዚያም አልፎ ሴቶች ምንም ባልሰሩት በባሎቻቸው ወንጀል ምክንያት ለሌላ ወንዶች ይሰጡ ነበር፦
ኤርሚያስ 8:10 ሰለዚህ *"ሚሰቶቻቸውንም ለሌሎች ወንዶች እሰጣለሁ"*።
2ኛ ሳሙኤል 12፥8 የጌታህንም ቤት ሰጠሁህ፥ *"የጌታህንም ሚስቶች” በብብትህ ጣልሁልህ"*።
2ኛ ሳሙኤል12፥11 እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እነሆ፥ ከቤትህ ክፉ ነገር አስነሣብሃለሁ፤ *”ሚስቶችህንም በዓይንህ ፊት እወስዳለሁ፥ ለዘመድህም እሰጣቸዋለሁ፥ በዚህችም ፀሐይ ዓይን ፊት ከሚስቶችህ ጋር ይተኛል"*።

እግር እራስን አያክም። በኢሥላም ያለውን የፍች እሳቤ ለመተቸት ቅድሚያ እነዚህ የባይብል አናቅጽ መልስ መስጠት ግድ ይላል እንጂ ሱሪ በአንገት ላድርግ አትበሉ። አሏህ ሂዳያ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ወሒድ ዐቃቢ ኢሥላም

መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
‐‐‐
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen

ወሠላሙ ዐለይኩም
236 views18:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-26 21:14:13
231 views18:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-24 21:03:04 ከጭቃ እንዴት?


በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

አላህ ለመላእክት እኔ ሰውን ከጭቃ ፈጣሪ ነኝ ብሏቸው ነበር፦
38:71 ጌታህ «ለመላእክት እኔ ሰውን *”ከጭቃ”* ፈጣሪ ነኝ ባለ ጊዜ» አስታውስ፡፡
15:28 ጌታህም ለመላእክት ባለጊዜ አስታውስ፡፡ እኔ ሰውን ከሚቅጨለጨል ሸክላ ከሚገማ *”ጭቃ”* እፈጥራለሁ፡፡

በእርግጥም አላህ ሰውን ከሚቅጨለጨል፣ ከሚገማ፣ ከነጠረ ጥቁር ጭቃ ፈጥሮታል፦
32:7 ያ የፈጠረውን ነገር ሁሉ ያሳመረው፣ የሰውንም ፍጥረት *”ከጭቃ”* የጀመረው ነው።
55:14 ሰውን እንደ ሸክላ ከሚቅጨለጨል ደረቅ *”ጭቃ”* ፈጠረው።
23:12 በእርግጥም ሰውን ከነጠረ *”ጭቃ”* ፈጠርነው፡፡
15:26 ሰውንም ከሚቅጨለጨል ሸክላ ከሚገማ ጥቁር *”ጭቃ”* በእርግጥ ፈጠርነው፡፡

የእኛም ስረ-መሰረት አደም ጭቃ ስለሆነ አላህ በሁለተኛ መደብ “ከጭቃ የፈጠራችሁ” ወይም በሶስተኛ መደብ “ከጭቃ ፈጠርናቸው” ይለናል፦
6:2 እርሱ ያ *”ከጭቃ”* የፈጠራችሁ ከዚያም የሞት ጊዜን የወሰነ ነው፡፡ እርሱም ዘንድ ለትንሣኤ የተወሰነ ጊዜ አለ፡፡ ከዚያም እናንተ በመቀስቀሳችሁ ትጠራላችሁ፡፡
37:11 ጠይቃቸዉም፤ እነርሱ በአፈጣጠር ይበልጥ የበረቱ ናቸዉን? ወይስ እኛ ከእነርሱ በፊት የፈጠርነዉ ፍጡር? እኛ ከሚጣበቅ *”ጭቃ”* ፈጠርናቸው።

ብዙ ክርስቲያኖች አላህ ሰውን ከጭቃ ፈጠርኩኝ ማለቱ ያስገርማቸዋል፤ እንዴት ከጭቃ ፈጠረው? ይላሉ፤ ምንም ቅኔ ስለሌለው ግልፅ የሆነው ቃል ማብራራት አያስፈልግም፤ ይህ የሚያሳየው የራሳችሁን መጽሐፍት ጠንቅቃችሁ ካለመረዳት የሚመጣ ጥያቄ ነው፦
ኢዮብ 33፥6 እኔ ደግሞ *”ከጭቃ የተፈጠርሁ ነኝ”*።
ኢሳይያስ 64፥8 *”እኛ ጭቃ ነን”* አንተም ሠሪያችን ነህ፥ እኛም ሁላችን የእጅህ ሥራ ነን።
ኢዮብ 10፥9 እንደ *”ጭቃ አድርገህ እንደ ለወስኸኝ”* አስብ፤ ወደ ትቢያም ትመልሰኛለህን?

ከኡስታዝ ወሒድ ዑመር

መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
‐‐‐
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen

ወሰላሙ አለይኩም
153 views18:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-24 21:02:59
149 views18:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-23 19:36:30 እውን ኢየሱስ የአብ ስም ነውን?


በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡

መግቢያ
ሥላሴአውያን ሳይሆኑ ሰባሌሳውያን ኢየሱስ የአብ ስም ነው የሚል አቋም አላቸው። ይህ ደምዳሜ ላይ ያደረሳቸው ጥቅስ እስቲ እንመልከት፦
ዮሐ.5:43 እኔ በአባቴ ስም መጥቻለሁ አልተቀበላችሁኝምም፤ ሌላው በራሱ ስም ቢመጣ እርሱን ትቀበሉታላችሁ።

ነጥብ አንድ
“በአባቴ ስም”
እኔ በአባቴ ስም መጥቻለሁ ማለቱ ኢየሱስ የአብ ስም አያደርገውም ምክንያቱም ኢየሱስ ብቻ ሳይሆን ዳዊትና የዳዊት መንግስት የመጡት በአብ ስም ነው፦
1. ዳዊት
ዳዊት የመጣው በያህዌህ ስም ነው። ነገር ግን ዳዊት የአብ ስም ኣይደለም፦ 1ሳሙ 17:45 ዳዊትም ፍልስጥኤማዊውን አለው። አንተ ሰይፍና ጦር ጭሬም ይዘህ ትመጣብኛለህ፤ እኔ ግን ዛሬ በተገዳደርኸው በእስራኤል ጭፍሮች አምላክ ስም በሠራዊት ጌታ “በያህዌህ ስም እመጣብሃለሁ”።
2. የዳዊት መንግሥት
የዳዊት መንግሥት የመጣችው በያህዌህ ስም ነው። ነገር ግን የዳዊት መንግሥት የአብ ስም አይደለችም፦ ማር 11:10 “በጌታ ስም የምትመጣ” የአባታችን የዳዊት መንግሥት የተባረከች ናት፤ ሆሣዕና በአርያም እያሉ ይጮኹ ነበር።

ነጥብ ሁለት
“በራሱ ስም”
ሌላው በራሱ ስም ቢመጣ እርሱን ትቀበሉታላችሁ ማለቱ እራሱ ሳይላክ በራሱ ስልጣን የሚናገር ሃሰተኛ ነብይ ማለት ነው፦
የዮሐንስ ወንጌል 8.42 እኔ ከእግዚአብሔር ወጥቼ መጥቻለሁና፤ “እርሱ ላከኝ እንጂ ከራሴ አልመጣሁምና”።
ዮሐ.10:25 ኢየሱስም መለሰላቸው፥ እንዲህ ሲል። ነገርኋችሁ አታምኑምም እኔ “በአባቴ ስም” የማደርገው ሥራ ይህ ስለ እኔ ይመሰክራል፤

በአባቴ ስም የማደርገው ሥራ እና ከራሴ አልመጣውም የሚለው አነጋገሩ በአምላክ ስም ተወክሎ እንደተላከ ፍንትው አድርጎ ያሳያል። በራሱ ስም ቢመጣ ኖሮ ማንም ሳይልከው ይመጣ ነበር። ግን በራሱ አልመጣም የላከውን ፈቃድ ለማድረግ በአብ ስም ታምራትን አድርጓል።
ነጥብ ሶስት
“ያህዌህ”
የኢየሱስ አባት ስሙ ያህዌህ ነው፦
አሞ 5:9፤ አምባውም እንዲፈርስ በብርቱ ላይ የድንገት ጥፋት የሚያመጣውን ፈልጉ፤ ስሙ יהוה “ያህዌህ” ነው።
ኤር 51:19 የያዕቆብ እድል ፈንታ እንደ እነዚህ አይደለም፥ እርሱ የሁሉ ፈጣሪ ነውና፤ እስራኤልም የርስቱ ነገድ ነው፥ ስሙም የሠራዊት ጌታ ” יהוה “ያህዌህ” ነው። ኤር 50:34 ተቤዢአቸው ብርቱ ነው፥ ስሙም የሠራዊት ጌታ ” יהוה “ያህዌህ” ነው፤
ኤር 10:16 የያዕቆብ እድል ፈንታ እንደ እነዚህ አይደለም፤ እርሱ የሁሉ ፈጣሪ ነውና፤ እስራኤልም የርስቱ ነገድ ነውና፤ ስሙ የሠራዊት ጌታ ” יהוה “ያህዌህ” ነው። ኤር 33:2 ስሙ ” יהוה “ያህዌህ” የሆነ፥ ያደረገው “ያህዌህ”፥ ያጸናውም ዘንድ የሠራው ” יהוה “ያህዌህ” እንዲህ ይላል። ዘጸ 15:3፤ “ያህዌህ” ተዋጊ ነው፥ ስሙም “ያህዌህ” ነው፥ ዘጸ 3:15 ለእስራኤል ልጆች እንዲህ ትላለህ። የአባቶቻችሁ አምላክ፥ የአብርሃም አምላክ የይስሐቅም አምላክ የያዕቆብም አምላክ ” יהוה “ያህዌህ” ወደ እናንተ ላከኝ፤ ይህ ለዘላለሙ ስሜ ነው፥ እስከ ልጅ ልጅ ድረስም መታሰቢያዬ ይህ ነው። ኢሳ 42:8፤ እኔ ” יהוה “ያህዌህ” ነኝ፤ “ስሜ” ይህ ነው፤ ኤር 16:21 ስለዚህ፥ እነሆ፥ አስታውቃቸዋለሁ፥ በዚህች ጊዜ እጄንና ኃይሌን አስታውቃቸዋለሁ፤ እነርሱም ስሜ ” יהוה “ያህዌህ” እንደ ሆነ ያውቃሉ። ”
ዮሐንስ ወንጌል 8:54 ኢየሱስም መለሰ አለም። እኔ ራሴን ባከብር ክብሬ ከንቱ ነው፤ የሚያከብረኝ እናንተ “አምላካችን የምትሉት አባቴ” ነው፤”

ነጥብ አራት
“ኢየሱስ”
ኢየሱስ የልጁ ስም ነው፦
ዮሐ 3:18 በእርሱ በሚያምን አይፈረድበትም፤ በማያምን ግን በአንዱ “በእግዚአብሔር ልጅ ስም” ስላላመነ አሁን ተፈርዶበታል። 1ዮሐ.5:13 የዘላለም ሕይወት እንዳላችሁ ታውቁ ዘንድ “በእግዚአብሔር ልጅ ስም” ለምታምኑ ይህን ጽፌላችኋለሁ። 1ዮሐ.3:23 ትእዛዚቱም ይህች ናት፥ “በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም” እናምን ዘንድ፥ ትእዛዝንም እንደ ሰጠን እርስ በርሳችን እንዋደድ ዘንድ። ዮሐ 20:31 ነገር ግን ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ “የእግዚአብሔር ልጅ” እንደ ሆነ ታምኑ ዘንድ፥ አምናችሁም “በስሙ” ሕይወት ይሆንላችሁ ዘንድ ይህ ተጽፎአል።

ኢየሱስ የአብ ስም ቢሆን ኖሮ “የኢየሱስ ልጅ” የሚል ጥቅስ ይገኝ ነበር። ነገር ግን በአባቱ ስምና በልጁ ስም መካከል ፈርቅ አለ፦
ራእ.14:1 አየሁም፥ እነሆም፥ በጉ በጽዮን ተራራ ቆሞ ነበር፥ ከእርሱም ጋር “ስሙ እና የአባቱ ስም” በግምባራቸው የተጻፈላቸው መቶ አርባ አራት ሺህ ነበሩ።

“ስሙ እና የአባቱ ስም” የሚለው ፈርቅ የልጁ ስም ኢየሱስ የአባቱ ስም ያህዌህ መሆኑን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው።

ነጥብ አምስት
“የሰው ስም”
ኢየሱስ የሚለው ስም በዕብራይስጥ ያህሹአ יְהוֹשֻׁ֣עַ በግሪክ ኤሱስ Ἰησοῦ ተብሎ ለሌሎች ሰዎች አገልግልግሎት ላይ ውሏል፦
ዘጸ.17:9፤ ሙሴም ኢያሱን*ያህሹአ* יְהוֹשֻׁ֣עַ ። ጕልማሶችን ምረጥልን፥ ወጥተህም ከአማሌቅ ጋር ተዋጋ፤ እኔ ነገ የእግዚአብሔርን በትር በእጄ ይዤ በኮረብታው ራስ ላይ እቆማለሁ አለው።
ሐጌ 1:1፤ በንጉሡ በዳርዮስ በሁለተኛው ዓመት በስድስተኛው ወር ከወሩም በመጀመሪያው ቀን የእግዚአብሔር ቃል… ወደ ታላቁም ካህን ወደ ኢዮሴዴቅ ልጅ ወደ ኢያሱ*ያህሹአ* יְהוֹשֻׁ֣עַ እንዲህ ሲል መጣ።
ሐዋ.7:45 አባቶቻችንም ደግሞ በተራ ተቀብለው እግዚአብሔር በፊታቸው ያወጣቸውን የአሕዛብን አገር በያዙት ጊዜ ከኢያሱ*ኤሱስ* Ἰησοῦ ጋር አገቡአት፥ እስከ ዳዊት ዘመንም ድረስ ኖረች።
ዕብ.4:8 ኢያሱ*ኤሱስ* Ἰησοῦ አሳርፎአቸው ኖሮ ቢሆንስ፥ ከዚያ በኋላ ስለ ሌላ ቀን ባልተናገረ ነበር።
ቆላ.4:10-11 ከተገረዙት ወገን ያሉት፥ አብሮ ከእኔ ጋር የታሰረ አርስጥሮኮስ የበርናባስም የወንድሙ ልጅ ማርቆስ ኢዮስጦስም የተባለ ኢያሱ*ኤሱስ*Ἰησοῦ ሰላምታ ያቀርቡላችኋል።

ኢየሱስ የፈጣሪ ስም ቢሆን ኖሮ ሰዎች ሲጠሩ ፈጣሪ ዝም ይል ነበርን?
ከዚያም ባሻገር ፈጣሪ ሰዎችን ኢየሱስ በሚል ስም ያነጋግራቸው ነበርን?
ኢየሱስ የፈጣሪ ስም ቢሆን ኖሮ ከጊዜ ወዲህ የወጣ ስም ይሆን ነበርን?

ከወሒድ ዐቃቢ ኢሥላም

መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
‐‐‐
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen

ወሰላሙ አለይኩም።
385 views16:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-23 19:35:51
325 views16:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-21 19:53:03 አምላክን ማየት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

5፥75 የመርየም ልጅ አልመሢሕ ከበፊቱ መልክተኞች በእርግጥ ያለፉ የኾነ መልክተኛ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡ مَّا الْمَسِيحُ ابْنُ مَرْيَمَ إِلَّا رَسُولٌ قَدْ خَلَتْ مِن قَبْلِهِ الرُّسُلُ

"እኔን ያየ አብን አይቶአል" የሚለውን ኃይለ-ቃል ይዘው የሐዋርያት ቤተክርስቲያን በተለምዶ ኢየሱስ ብቻ"only Jesus" የሚባሉት፦ "ኢየሱስ አብ ነው" ሲሉ ኦርቶዶክስ፣ ካቶሊክ፣ አንግሊካን እና ፕሮቴስታንት ደግሞ፦ "ኢየሱስ አምላክ ነው" የሚል ድምዳሜ ላይ ደርሰዋል፥ እውን ይህ ኃይለ-ቃል "ኢየሱስ አብ ነው" ወይም "ኢየሱስ አምላክ ነው" ለሚለው ዶክትሪን ድምዳሜ ላይ ያደርሳልን? ጥቅሱን በሰከነ እና በሰላ አእምሮ እንመልከተው፦
ዮሐ14፥7 እኔንስ ብታውቁኝ አባቴን ደግሞ ባወቃችሁ ነበር። ከአሁንም ጀምራችሁ ታውቁታላችሁ አይታችሁትማል አለው።
ዮሐ14፥8 ፊልጶስ ጌታ ሆይ፥ አብን አሳየንና ይበቃናል አለው። ኢየሱስም አለው።
ዮሐ14፥9 አንተ ፊልጶስ፥ ይህን ያህል ዘመን ከእናንተ ጋር ስኖር አታውቀኝምን? እኔን ያየ አብን አይቶአል።

"እኔን ያየ አብን አይቶአል" ማለት እና "እኔ አብ ነኝ ወይም እኔ አምላክ ነኝ" ማለት አንድ የሚሆነው በምን ሒሣብ ታሥቦ ነው? ኢየሱስ፦ "እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል" ብሏል፥ እና ሐዋርያት ኢየሱስ ናቸውን? ተመሳሳይ ሰዋስው ነው፦
ማቴዎስ 10፥40 እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል፥ እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል።

"እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል" ማለት "ሐዋርያትን መቀበል ኢየሱስን እንደ መቀበል ነው" ማለት ከሆነ እንግዲያውስ "እኔን ያየ አብን አይቶአል" ማለት "ወልድን ማየት አብን እንደ ማየት ነው" ማለት ነው፥ "እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል" ማለት "ወልድን መቀበል አብን እንደ መቀበል ነው" ማለት ከሆነ "ወልድን ማየት አብን እንደ ማየት ነው" ማለት ነው። ተመሳሳይ ሙግት እንመልከት፦
ሉቃ10፥16 እናንተንም የጣለ እኔን ይጥላል፤ እኔንም የጣለ የላከኝን ይጥላል።

"እናንተንም የጣለ እኔን ይጥላል" ማለት "ሐዋርያትን መጣል ኢየሱስን እንደ መጣል ነው" ማለት ከሆነ እንግዲያውስ "እኔን ያየ አብን አይቶአል ማለት ወልድን ማየት አብን እንደ ማየት ነው" ማለት ነው፥ "እኔንም የጣለ የላከኝን ይጥላል" ማለት "ወልድን መጣል አብን እንደ መጣል ነው" ማለት ከሆነ "ወልድን ማየት አብን እንደማየት ነው" ማለት ነው። እንቀጥል፦
ዮሐንስ 5፥46 ሙሴንስ ብታምኑት እኔን ባመናችሁ ነበር።

"ሙሴንስ ብታምኑት እኔን ባመናችሁ ነበር" ማለት ሙሴ ኢየሱስ ነውን? ወይስ "ሙሴን ማመን ኢየሱስ እንደ ማመን ነው" ማለት ነው? እንዲሁ ኢየሱስን ማየት አብን እንደ ማየት ነው፣ ኢየሱስን ማወቅ አብን እንደ ማወቅ ነው፣ ኢየሱስን መጥላት አብን እንደ መጥላት ነው፦
ዮሐንስ 12፥45 እኔንም የሚያይ የላከኝን ያያል።
ዮሐንስ 14፥7 እኔንስ ብታውቁኝ አባቴን ደግሞ ባወቃችሁ ነበር።
ዮሐንስ 15፥23 እኔን የሚጠላ አባቴን ደግሞ ይጠላል።

"እኔን" አንደኛ ማንነት "የላከኝ ወይም አባቴ" ሁለተኛ ማንነት፥ ስለዚህ ሁለት ማንነቶችን ቀልጭ አርጎ ያሳያል፦
ዮሐንስ 15፥24 አሁን ግን እኔንም አባቴንም አይተውማል ጠልተውማል።

ያዩት እና የጠሉት ሁለት ማንነት ነው፥ "እኔን" አንድ "አባቴን" ሁለት። አብን ታውቁታላችሁ አይታችሁትማል፦
ዮሐንስ 14፥7 ከአሁንም ጀምራችሁ ታውቁታላችሁ አይታችሁትማል" አለው።

"ማየት" ማለት በእማሬአዊ አብን በሥጋ ዓይን መመልከት ሳይሆን በመልእክተኛው ማንነት ውስጥ በፍካሬአዊ "መገንዘብ" ማለት ነው፦
ዮሐንስ 6፥46። አብን ያየ ማንም የለም፥ ከእግዚአብሔር ከሆነ በቀር እርሱ አብን አይቶአል።

"ከሆነ" የሚለው ቃል በቅጡ ይሰመርበት! "ከ"-እግዚአብሔር የሆነ መንፈሳዊ ሰው እርሱ አብን አይቷል፥ በሥጋ ዓይን ግን አብን ያየ ማንም የለም፦
ዮሐንስ 5፥37 የላከኝ አብም እርሱ ስለ እኔ መስክሮአል። ድምፁን ከቶ አልሰማችሁም፥ “መልኩንም አላያችሁም”፤
ዮሐንስ 1፥18 መቼም ቢሆን እግዚአብሔርን ያየው አንድ ስንኳ የለም።
1ኛ ዮሐንስ 4፥12 እግዚአብሔርን ማንም ከቶ አላየውም።
1ኛ ጢሞቴዎስ 6፥16 አንድ ሰው እንኳ አላየውም ሊያይም አይቻለውም።

ከኢየሱስ እርገት በኃላ "እግዚአብሔርን ማንም ከቶ አላየውም" ሲባል ኢየሱስ "አብን አይታችሁትማል" ከሚለው ጋር ለማስማማት የሚቻለው "ወልድን ማየት አብን እንደ ማየት ነው" በሚል ቀመር ብቻ ነው። ብሉይ ኪዳን ላይ መላእክት ሲገለጡ ሰዎች "እግዚአብሔር አይተናል" ይሉ ነበር።

ናሙና አንድ፦
ዘፍጥረት 16፥7 "የእግዚአብሔር መልአክም" በውኃ ምንጭ አጠገብ በበረሀ አገኛት።
ዘፍጥረት 16፥13 እርስዋም ይናገራት የነበረውን የእግዚአብሔርን ስም ኤልሮኢ ብላ ጠራች፤ የሚያየኝን በውኑ እዚህ ደግሞ አየሁትን? ብላለችና።

ናሙና ሁለት፦
ሆሴዕ 12፥4 "ከመልአኩም" ጋር ታግሎ አሸነፈ፤ አልቅሶም ለመነው።
ዘፍጥረት 32፥24 ያዕቆብ ግን ለብቻው ቀረ፤ አንድ "ሰውም" እስከ ንጋት ድረስ ይታገለው ነበር።
ዘፍጥረት 32፥30 ያዕቆብም፦ እግዚአብሔርን ፊት ለፊት አየሁ፥ ሰውነቴም ድና ቀረች" ሲል የዚያን ቦታ ስም ጵኒኤል ብሎ ጠራው።

ናሙና ሦስት፦
መሣፍንት 14፥21 ያን ጊዜም ማኑሄ "የእግዚአብሔር መልአክ" መሆኑን አወቀ።
መሣፍንት 13፥22 ማኑሄም ሚስቱን፦ እግዚአብሔርን አይተናልና ሞት እንሞታለን" አላት።

መላእክት መልእክተኞች ሲሆኑ በመላእክት የአምላክ መታየት "አስተርዮተ አምላክ"theophany" ሲሆን ይህም መታየት ፍካሬአዊ እንጂ እማሬአዊ አይደለም፦
ዘጸአት 33፥20 ደግሞም፦ ሰው አይቶኝ አይድንምና ፊቴን ማየት አይቻልህም፡ አለ።

መላእክትን ማየት እግዚአብሔር ማየት ከሆነ መልእክተኛውን "ኢየሱስን ማየት እግዚአብሔር ማየት ነው" ብሎ መረዳት እንጂ መልእክተኛው እራሱ አብ ወይም አምላክ ነው" ብሎ መደምደም የሾቀ ድምዳሜ ነው። የመርየም ልጅ አልመሢሕ ከበፊቱ መልክተኞች በእርግጥ ያለፉ የኾነ መልክተኛ እንጅ ሌላ አይደለም፦
5፥75 የመርየም ልጅ አልመሢሕ ከበፊቱ መልክተኞች በእርግጥ ያለፉ የኾነ መልክተኛ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡ مَّا الْمَسِيحُ ابْنُ مَرْيَمَ إِلَّا رَسُولٌ قَدْ خَلَتْ مِن قَبْلِهِ الرُّسُلُ

ኢየሱስን የላከውን አንዱን አምላክ አሏህ እንድታመልኩ ጥሪያችን ነው። አሏህን ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
‐‐‐
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen

ወሠላሙ ዐለይኩም
232 views16:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-21 19:52:53
225 views16:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ