Get Mystery Box with random crypto!

Tiriyachen | ጥሪያችን

የቴሌግራም ቻናል አርማ tiriyachen — Tiriyachen | ጥሪያችን T
የቴሌግራም ቻናል አርማ tiriyachen — Tiriyachen | ጥሪያችን
የሰርጥ አድራሻ: @tiriyachen
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.91K

Ratings & Reviews

1.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2023-03-31 23:47:09
335 views20:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-29 23:50:40 ሡነን ነሣኢይ መጽሐፍ 4, ሐዲስ 37
ጃቢር ኢብኑ ዐብደሏህ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "እኔ ወደ ሰዎች ሁሉ ተልኬአለሁ፥ ከእኔ በፊት የነበሩት ነቢያት ግን ለገዛ ሕዝቦቻቸው ተልከዋል"። عَنْ جَابِرِ بْنِ عَبْدِ اللَّهِ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ بُعِثْتُ إِلَى النَّاسِ كَافَّةً وَكَانَ النَّبِيُّ يُبْعَثُ إِلَى قَوْمِهِ خَاصَّةً ‏"‏ ‏.‏

ኢየሱስ፦ "ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ! ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ" አለ ተብሎ የሚጠቀሰው ጥቅስ በኢየሱስ ላይ የተቀጠፈ ቅጥፈት ነው፦
ማርቆስ 16፥15 እንዲህም አላቸው፦ "ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ! ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ"።

ማርቆስ ወንጌሉ የሚያልቀው 16፥8 ላይ ብቻ ነው፥ ከቁጥር 9-20 ድረስ ያለው በጥንታዊ ግሪክ እደክታባት ላይ የለም። እሩቅ ሳንሄድ "ከዚህም በኋላ ኢየሱስ ራሱ ለዘላለም ድኅነት የሆነውን የማይለወጠውን ቅዱስ ወንጌል ከፀሐይ መውጫ እስከ መጥለቂያው ድረስ በእጃቸው ላከው" የሚለው አንቀጽ ግሪኩ ላይ፣ እንግሊዝኛ ላይ እና አዲሱ መደበኛ ትርጉም ላይ የሌለ እና የኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር የቀሰጠው ቅሰጣ ነው፦
ማርቆስ 16፥8 ከዚህም በኋላ ኢየሱስ ራሱ ለዘላለም ድኅነት የሆነውን የማይለወጠውን ቅዱስ ወንጌል ከፀሐይ መውጫ እስከ መጥለቂያው ድረስ በእጃቸው ላከው።

ኢየሱስ የመላው ዘር ነቢይ ለማድረግ የተሄደበት ርቀት ሳስበው ያጅበኛል፥ ነገር ግን ኢየሱስ ለእራኤል ልጆች የተላከ ነቢይ ነው። አሏህ ለእናንተ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ

መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
‐‐‐
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen

ወሠላሙ ዐለይኩም
144 views20:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-29 23:50:40 የእስራኤል ነቢይ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

3፥49 ወደ እስራኤልም ልጆች መልእክተኛ ያደርገዋል፡፡ وَرَسُولًا إِلَىٰ بَنِي إِسْرَائِيلَ

አምላካችን አሏህ ዒሣን መልእክተኛ አድርጎ የላከው ወደ እስራኤል ልጆች ስለሆነ እርሱ፦ "የእስራኤል ልጆች ሆይ! እኔ ወደ እናንተ የተላኩኝ የአላህ መልእክተኛ ነኝ" በማለት ተናግሯል፦
61፥6 የመርየም ልጅ ዒሳም፡- «የእስራኤል ልጆች ሆይ! እኔ ከተውራት በፊቴ ያለውን የማረጋግጥ እና ከእኔ በኋላ በሚመጣው መልእክተኛ ስሙ አሕመድ በኾነው የማበስር ስኾን ወደ እናንተ የተላኩኝ የአላህ መልእክተኛ ነኝ» ባለ ጊዜ አስታውስ፡፡ وَإِذْ قَالَ عِيسَى ابْنُ مَرْيَمَ يَا بَنِي إِسْرَائِيلَ إِنِّي رَسُولُ اللَّهِ إِلَيْكُم مُّصَدِّقًا لِّمَا بَيْنَ يَدَيَّ مِنَ التَّوْرَاةِ وَمُبَشِّرًا بِرَسُولٍ يَأْتِي مِن بَعْدِي اسْمُهُ أَحْمَدُ

ይህ ሐቅ በባይብል ላይ በቅሪት ደረጃ ኢየሱስ፦ "ከእስራኤል ቤት ለጠፉት በጎች በቀር አልተላክሁም" ብሏል፦
ማቴዎስ 15፥24 እርሱም መልሶ፦ "ከእስራኤል ቤት ለጠፉት በጎች በቀር አልተላክሁም" አለ።

"በቀር" የሚለው ግድባዊ ተውሳከ ግሥ ከእስራኤል ቤት ውጪ ለሌላ አለመላኩን ቁልጭ እና ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ነው። በተጨማሪ ጴጥሮስ፦ "የእስራኤል ሰዎች ሆይ! የናዝሬቱ ኢየሱስ ከእግዚአብሔር ዘንድ "ለ"-እናንተ የተገለጠ ሰው ነበረ" በማለት የናዝሬቱ ኢየሱስ ለእስራኤል ሰዎች እንደተላከ ይናገራል፦
የሐዋርያት ሥራ 2፥22 "የእስራኤል ሰዎች" ሆይ! ይህን ቃል ስሙ፤ ራሳችሁ እንደምታውቁ፥ የናዝሬቱ ኢየሱስ እግዚአብሔር በመካከላችሁ በእርሱ በኩል ባደረገው ተአምራትና በድንቆች በምልክቶችም ከእግዚአብሔር ዘንድ "ለ"-እናንተ" የተገለጠ ሰው ነበረ።

ጳውሎስ ምንም እንኳን በኃላ ላይ አሳቡን ቢቀይርም በጅምሩ ላይ፦ "እግዚአብሔር እንደ ተስፋው ቃል "ለ"-እስራኤል መድኃኒትን እርሱም ኢየሱስን አመጣ" በማለት እግዚአብሔር ኢየሱስን ለእስራኤል እንዳመጣው ተናግራል፦
የሐዋርያት ሥራ 13፥23፤ ከዚህም ሰው ዘር እግዚአብሔር እንደ ተስፋው ቃል "ለ"-እስራኤል መድኃኒትን እርሱም ኢየሱስን አመጣ።

ልጅነት፣ ኪዳን፣ የተስፋው ቃል ወዘተ ለእስራኤል ቤት ብቻ የተሰጠ ሲሆን መሢሕም "ይመጣላችኃል ይላክላችኃል" ተብሎ ቃል የተገባላቸውም ለእስራኤል ቤት ብቻ ነው፥ ይህንን የልጆችን የእስራኤል ቤት እንጀራ ይዞ ለቡችሎች መጣል አይገባም፦
ማቴዎስ 15፥26 እርሱ ግን መልሶ፦ "የልጆችን እንጀራ ይዞ ለቡችሎች መጣል አይገባም" አለ።
ማቴዎስ 15፥27 እርስዋም፦ "አዎን ጌታ ሆይ! ቡችሎችም እኮ ከጌቶቻቸው ማዕድ የወደቀውን ፍርፋሪ ይበላሉ" አለች።

"ቡችሎች" የተባሉት ከእስራኤል ቤት ውጪ ያሉት ሰዎች ናቸው፥ ከእስራኤል ቤት ውጪ ያሉት ሰዎች ከእስራኤል ቤት ማዕድ የወደቀውን ፍርፋሪ እንጂ ዋናው የኢየሱስ መልእክት ለእስራኤል ቤት ብቻ እና ብቻ ነው። ኢየሱስ ወደ ዓለም የመጣ ነቢይ ነው፦
ዮሐንስ 6፥14 ከዚህ የተነሣ ሰዎቹ ኢየሱስ ያደረገውን ምልክት ባዩ ጊዜ፦ "ይህ በእውነት ወደ ዓለም የሚመጣው ነቢይ ነው" አሉ።

የእስራኤል ቤት እኮ ዓለም ነው፥ "ዓለም" የሚለው የእስራኤልን ቤት ያመለክታል፦
ዮሐንስ 15፥18 ዓለም ቢጠላችሁ ከእናንተ በፊት እኔን እንደ ጠላኝ እወቁ።

ኢየሱስን የጠሉት እነማን ናቸው? የእስራኤል ቤት ወይስ መላው የሰው ልጆች? ፈሪሳውያን፦ "ዓለሙ በኋላው ተከትሎት ሄዶአል" ሲሉ ተከትለው የሄዱት ሰዎች አንድ ሺህም አይሞሉም ነበር፦
ዮሐንስ 12፥19 ሰለዚህ ፈሪሳውያን እርስ በርሳቸው፦ አንድ ስንኳ ልታደርጉ እንዳይቻላችሁ ታያላችሁን? እነሆ፥ ዓለሙ በኋላው ተከትሎት ሄዶአል" ተባባሉ።

ስለዚህ "ዓለም" ሲባል መላው የሰው ዘር ሳይሆን የእስራኤል ቤትን በጉልኅ የሚያሳይ ነው፦
ቆላስይስ 2፥20 ከዓለማዊ ከመጀመሪያ ትምህርት ርቃችሁ ከክርስቶስ ጋር ከሞታችሁ።
ገላትያ 4፥3 እንዲሁ እኛ ደግሞ ሕፃናት ሆነን ሳለን ከዓለም መጀመሪያ ትምህርት በታች ተገዝተን ባሪያዎች ነበርን።

"ከዓለም መጀመሪያ ትምህርት" የሚለው የፊተኛውን ኪዳን እንደሆነ ገላትያ 4፥9 ቆላስይስ 2፥8 ላይ ያሉትን ጥቅስ ተመልከት! የሙሴ ሕጉም ሁሉ እና የነቢያት ትንቢት "ተሰቅለዋል" ሲባል ጳውሎስ "ዓለም ለእኔ የተሰቀለበት" ሲል በሕግ በኩል ለሕግ መሰቀሉን ለማመልከት "እኔም ለዓለም የተሰቀልሁበት" በማለት ዓለም የሚለው የእስራኤልን ቤት እንደሆነ ተናግሯል፦
ማቴዎስ 22፥40 በእነዚህ በሁለቱ ትእዛዛት ሕጉም ሁሉ ነቢያትም ተሰቅለዋል።
ገላትያ 2፥19 በሕግ በኩል ለሕግ ሞቼ ነበርና፥ ከክርስቶስ ጋር ተሰቅዬአለሁ።
ገላትያ 6፥14 ነገር ግን ዓለም ለእኔ የተሰቀለበት እኔም ለዓለም የተሰቀልሁበት ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በቀር ሌላ ትምክህት ከእኔ ይራቅ።

"በሕግ በኩል ለሕግ ሞቼ" የሚለው ይሰመርበት! የሙሴ ሕግ የያዘው የእስራኤል ቤት ሲሆን ኢየሱስ ከአብ የሰማውን መልእክት "ለዓለም እናገራለሁ" ሲል "ለእስራኤላውያን እናገራለን" ማለቱ እንጂ ለሰው ዘር ሁሉ ማለቱ አይደለም፦
ዮሐንስ 8፥26 ዳሩ ግን የላከኝ እውነተኛ ነው እኔም ከእርሱ የሰማሁትን "ይህን ለዓለም እናገራለሁ"።
ኢየሱስ፦ "ከዚህም በረት ያልሆኑ ሌሎች በጎች አሉኝ" ሲል የእስራኤል ቤት የሆኑትን የጠፉ በጎች ነው፥ እርሱ የተላከው ከእስራኤል ቤት ለጠፉት በጎች ብቻ ነው፦
ማቴዎስ 10፥6 ይልቅስ የእስራኤል ቤት ወደሚሆኑ ወደ ጠፉት በጎች ሂዱ እንጂ።
ማቴዎስ 15፥24 እርሱም መልሶ፦ "ከእስራኤል ቤት ለጠፉት በጎች በቀር አልተላክሁም" አለ።
ዮሐንስ 10፥16 ከዚህም በረት ያልሆኑ ሌሎች በጎች አሉኝ፤ እነርሱን ደግሞ ላመጣ ይገባኛል ድምፄንም ይሰማሉ፥ አንድም መንጋ ይሆናሉ እረኛውም አንድ።

ክርስቲያኖች ሆይ! በኢየሱስ በማመናችሁ ትሩፋት በመካዳችሁ ቅጣት አታገኙም፥ ምክንያቱም ኢየሱስ ለእስራኤል ቤት የተላከ የእስራኤል ነቢይ ነው። ብትከተሉት ከልጆች እንጀራ የተረፈ ፍርፋሪ እንጂ ቡችሎች ናችሁ፥ ለእናንተ ፍርፋሪ ከመብላት መፍትሔው ነቢያችንን"ﷺ" መከተል ነው። ምክንያቱም ነቢያችን"ﷺ" ለሰዎች ሁሉ የተላኩ የአሏህ መልእክተኛ ናቸው፦
4፥79 "ለሰዎችም ሁሉ" መልእክተኛ ኾነህ ላክንህ፡፡ መስካሪም በአላህ በቃ፡፡ وَأَرْسَلْنَاكَ لِلنَّاسِ رَسُولًا ۚ وَكَفَىٰ بِاللَّهِ شَهِيدًا
7፥158 በላቸው፡- «እናንተ ሰዎች ሆይ! እኔ ወደ እናንተ "ወደ ሁላችሁም" የአላህ መልእክተኛ ነኝ»፡፡ قُلْ يَا أَيُّهَا النَّاسُ إِنِّي رَسُولُ اللَّهِ إِلَيْكُمْ جَمِيعًا
34፥28 አንተንም "ለሰዎች ሁሉ በሙሉ" አብሳሪ እና አስጠንቃቂ አድርገን ቢሆን እንጂ አላክንህም፡፡ ግን አብዛኞቹ ሰዎች አያውቁም፡፡ وَمَا أَرْسَلْنَاكَ إِلَّا كَافَّةً لِّلنَّاسِ بَشِيرًا وَنَذِيرًا وَلَـٰكِنَّ أَكْثَرَ النَّاسِ لَا يَعْلَمُونَ
148 views20:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-29 23:50:40
131 views20:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-28 23:25:15 لَكَ عِشْرُونَ دِينَارًا

በዚህ ሐዲስ መሠረት የአንድ ሰው ካፒታል 20 ዲናር ወይም 200 ዲርሀም ሲሆን ዘካህ ይወጅበታል፥ በሸሪዓህ የዘካህ አነስተኛ የክፍያ መጠን “ኒሷብ” نِصاب ይባላል፥ ይህም ኒሷብ የሚለካው 20 ዲናር ወይም 200 ዲርሀም ሲሆን ነው። “ዲናር” دِينَار‎ ማለት “የወርቅ ሳንቲም”gold coin” ማለት ሲሆን “ዲርሀም” دِرْهَم‎ ማለት ደግሞ “የብር ሳንቲም”silver coin” ማለት ነው። ይህ በጥንት “የኮሞዲቲ ገንዘብ”commodity money” ይባላል።
“ዲናር” እና “ዲርሀም” የሚለኩት በሚስቃል ነው፥ “ሚስቃል” مِثْقَال የሚለው ቃል “ሰቀለ” ثَقَلَ ማለትም “ከበደ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ክብደት” ማለት ነው።
1 ሚስቃል ወርቅ 4.25 ግራም ነው፥ 20 ሚስቃል ወርቅ ደግሞ 4,25x 20 = 85 ግራም ወርቅ ይሆናል ማለት ነው።
1 ሚስቃል ብር 2.975 ግራም ነው፥ 200 ሚስቃል ብር ደግሞ 2.975x 200= 595 ግራም ብር ይሆናል ማለት ነው።

በዘካህ ላይ የሚወጅበው ኒሷብ 85 ግራም ወርቅ ወይም 595 ግራም ብር ነው።
አንድ ሙሥሊም ያለው ካፒታል በዓመት ውስጥ 85 ግራም ወርቅ ወይም 595 ግራም ብር ያክል ከሆነ ዘካህ ማውጣት ግዴታው ነው። ይህ ኒሷብ ወደ ወረቀት ገንዘብ”Fiat money” ለመቀየር ወርቅን ዛሬ ባለው በ 24 ካራት የወቅቱ ግብይት ለናሙና ያክል መሥራት ይቻላል፦
1. በስውዲን አንድ ግራም ወርቅ 551.74 ክራውን ነው፥ 551.74 ×85= 46,897.9 ክራውን ይሆናል።
2. በኢትዮጵያ አንድ ግራም ወርቅ 1,836.6 ብር ነው፥ 1,836.6×85= 156,111 ብር ይሆናል።
3. በአሜሪካ አንድ ግራም ወርቅ 55.146 ዶላር ነው፥ 55.146×85= 4,687.41 ዶላር ይሆናል።

ስለዚህ አንድ ሙሥሊም ያለው ካፒታል በገንዘብ ሲተመን በስውዲን 551.74 ክራውን፣ በኢትዮጵያ 156,111 ብር፣ በአሜሪካ 4,687.41 ዶላር ወዘተ ከሆነ ከዚያ ወዲህ ዘካህ ማውጣቱ ፈርድ ነው። ለምሳሌ አንድ ሰው በኢትዮ 156,111 ሺ ብር ካለው ከ 156,111 ሺ ብር ላይ 2.5% ዘካ ያወጣል፥ ያ ማለት የዘካው ብር 156,111×2.5÷100= ውጤቱ 3,902.775 ብር ይሆናል ማለት ነው። ይህ በጎርጎሮሳውያን አቆጣጠር የ 2020 ድኅረ-ልደት ግብይት ነው፦
http://goldpricez.com/
ዘካን የማይሰጥ በመጨረሻይቱ ዓለም ከአላህ ዘንድ መተሳሰብ የለም ብሎ የሚክድ ሰው ነው፥ ለእዚያ ገንዘብን የሰበሰበ እና የቆጣጠረው ለኾነ ወዮለት፦
41፥7 *”ለእነዚያ ዘካን ለማይሰጡት እነርሱም በመጨረሻይቱ ዓለም እነርሱ ከሓዲዎች ለኾኑት ወዮላቸው”*፡፡ الَّذِينَ لَا يُؤْتُونَ الزَّكَاةَ وَهُم بِالْآخِرَةِ هُمْ كَافِرُونَ
104፥2 *”ለእዚያ ገንዘብን የሰበሰበ እና የቆጣጠረው ለኾነ ወዮለት”*፡፡ الَّذِي جَمَعَ مَالًا وَعَدَّدَهُ

አንድ ሙሥሊም ይህንን ዘካ ካላወጣ የትንሳኤ ቀን ገንዘቡ እንደ ሁለት አይኖቹ ላይ ጥቁር ነጥቦች የተጣሉበት ወንድ መላጣ እባብ ተመስሎ ይመጣና ማንገጭላውን አጥብቆ በመያዝ፦ “እኔ ገንዘብህ ነኝ፥ እኔ ድልብህ ነኝ” ይለዋል፦
3፥180 *”እነዚያም አላህ ከችሮታው በሰጣቸው ገንዘብ የሚነፍጉ እርሱ ለእነርሱ ደግ አይምሰላቸው፡፡ ይልቁንም እርሱ ለእነርሱ መጥፎ ነው፡፡ ያንን በእርሱ የነፈጉበትን በትንሣኤ ቀን እባብ ኾኖ ይጠለቃሉ”*፡፡ የሰማያትና የምድርም ውርስ ለአላህ ብቻ ነው፡፡ አላህም በሚሠሩት ሁሉ ውስጥ ዐዋቂ ነው፡፡ وَلَا يَحْسَبَنَّ الَّذِينَ يَبْخَلُونَ بِمَا آتَاهُمُ اللَّهُ مِن فَضْلِهِ هُوَ خَيْرًا لَّهُم ۖ بَلْ هُوَ شَرٌّ لَّهُمْ ۖ سَيُطَوَّقُونَ مَا بَخِلُوا بِهِ يَوْمَ الْقِيَامَةِ ۗ وَلِلَّهِ مِيرَاثُ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ ۗ وَاللَّهُ بِمَا تَعْمَلُونَ خَبِيرٌ
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 90, ሐዲስ 5
አቢ ሁራይራ”ረ.ዐ.” እንደተረከው፦ “የአላህ መልእክተኛም”ﷺ” አሉ፦ *”አላህ ገንዘብ ሰጥቶት የእሱን ዘካህ ያላወጣ የትንሳኤ ቀን ገንዘቡ እንደ ሁለት አይኖቹ ላይ ጥቁር ነጥቦች የተጣሉበት ወንድ መላጣ እባብ ተመስሎ ይመጣና ማንጋጭላውን አጥብቆ በመያዝ፦ “እኔ ገንዘብህ ነኝ፥ እኔ ድልብህ ነኝ ይለዋል”*። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ ـ رضى الله عنه ـ قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏”‏ يَكُونُ كَنْزُ أَحَدِكُمْ يَوْمَ الْقِيَامَةِ شُجَاعًا أَقْرَعَ، يَفِرُّ مِنْهُ صَاحِبُهُ فَيَطْلُبُهُ وَيَقُولُ أَنَا كَنْزُكَ‏.‏ قَالَ وَاللَّهِ لَنْ يَزَالَ يَطْلُبُهُ حَتَّى يَبْسُطَ يَدَهُ فَيُلْقِمَهَا فَاهُ

አላህ ከዚህ ቅጣት ይጠብቀን። የዘካህ ብር የሚውለው ለድኾች፣ ለምስኪኖችም፣ ዘካን በማሰጠት ለሚያስተባብሩ፣ ልቦቻቸውም በኢሥላም ለሚለማመዱት፣ በባርነት ተገዢዎችን ነጻ ለማውጣት፣ ለባለ ዕዳዎችም፣ በአላህ መንገድም ለሚሠሩ፣ ለመንገደኛ ነው፦
9፥60 *ግዴታ ምጽዋቶች የሚከፈሉት ለድኾች፣ ለምስኪኖችም፣ በርሷም ላይ ለሚሠሩ ሠራተኞች፣ ልቦቻቸውም በኢሥላም ለሚለማመዱት፣ በባርነት ተገዢዎችን ነጻ በማውጣት፣ በባለ ዕዳዎችም፣ በአላህ መንገድም በሚሠሩ፣ በመንገደኛም ብቻ ነው፡፡ ከአላህ የተደነገገች ግዴታ ናት”*፡፡ አላህም ዐዋቂ ጥበበኛ ነው፡፡ إِنَّمَا الصَّدَقَاتُ لِلْفُقَرَاءِ وَالْمَسَاكِينِ وَالْعَامِلِينَ عَلَيْهَا وَالْمُؤَلَّفَةِ قُلُوبُهُمْ وَفِي الرِّقَابِ وَالْغَارِمِينَ وَفِي سَبِيلِ اللَّهِ وَابْنِ السَّبِيلِ ۖ فَرِيضَةً مِّنَ اللَّهِ ۗ وَاللَّهُ عَلِيمٌ حَكِيمٌ

አምላካችን አላህ ሙንፊቂን ከሚላቸው ባሮቹ ያድርገን! አሚን።

ከወንድም ወሒድ ዑመር

መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
‐‐‐
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen

ወሠላሙ ዐለይኩም
99 views20:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-28 23:25:15 ዘካህ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

2፥277 እነዚያ ያመኑ፣ መልካም ሥራዎችንም የሠሩ፣ ሶላትንም ያስተካከሉ፣ *”ዘካንም የሰጡ ለእነርሱ በጌታቸው ዘንድ ምንዳቸው አላቸው፡፡ በእነርሱም ላይ ፍርሃት የለባቸውም እነርሱም አያዝኑም”*፡፡ إِنَّ الَّذِينَ آمَنُوا وَعَمِلُوا الصَّالِحَاتِ وَأَقَامُوا الصَّلَاةَ وَآتَوُا الزَّكَاةَ لَهُمْ أَجْرُهُمْ عِندَ رَبِّهِمْ وَلَا خَوْفٌ عَلَيْهِمْ وَلَا هُمْ يَحْزَنُونَ

“ኢሥላም” إِسْلَٰم የሚለው ቃል “አሥለመ” أَسْلَمَ ማለትም “ታዘዘ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “መታዘዝ” ማለት ነው። “አርካን” أَرْكان‎ ማለት “ምሰሶ” ማለት ነው፥ “አርካኑል ኢሥላም” أَرْكَان الْإِسْلَٰم ማለት “የኢሥላም ምሰሶ” ማለት ነው። የኢሥላም ምሰሶ ደግሞ አምስት ናቸው፥ እነርሱም፦ ሸሃደተይን፣ ሶላት፣ ዘካህ፣ ሰውም እና ሐጅ ናቸው፦
ጃምዒ አት-ተርሚዚ መጽሐፍ 40, ሐዲስ 4
ኢብኑ ዑመር እንደተረከው፦ “የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ *”ኢሥላም በአምስቱ መሠረቶች ላይ ተገንብቷል፤ እነርሱም፦ “ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም፥ ሙሐመድም የአላህ መልእክተኛ ነው” በሚል ምስክርነት፣ ሶላትን በመቆም፣ ዘካህን በመስጠት፣ ረመዷንን በመፆም እና የአላህ ቤት በመጎብኘት”*። عَنِ ابْنِ عُمَرَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ بُنِيَ الإِسْلاَمُ عَلَى خَمْسٍ شَهَادَةُ أَنْ لاَ إِلَهَ إِلاَّ اللَّهُ وَأَنَّ مُحَمَّدًا رَسُولُ اللَّهِ وَإِقَامُ الصَّلاَةِ وَإِيتَاءُ الزَّكَاةِ وَصَوْمُ رَمَضَانَ وَحَجُّ الْبَيْتِ

ዘካህ ከእርካኑል ኢሥላም አንዱ ነው። “ዘካህ” زَكَوٰة የሚለው ቃል “ዘካ” زَكَىٰ ማለትም “ጠራ” ከሚል የግስ መደብ የመጣ ሲሆን “መጥራራት” ማለት ነው፦
20፥76 ከሥሮቻቸው ወንዞች የሚፈሱባቸው የመኖሪያ ገነቶች በውስጣቸው ዘውታሪዎች ሲኾኑ አሏቸው፡፡ *ይህም “የተጥራራ” ሰው ምንዳ ነው*፡፡ جَنَّاتُ عَدْنٍ تَجْرِي مِن تَحْتِهَا الْأَنْهَارُ خَالِدِينَ فِيهَا ۚ وَذَٰلِكَ جَزَاءُ مَن تَزَكَّىٰ

“የተጥራራ” ለሚለው ግስ የገባው ቃል “ተዘካ” تَزَكَّىٰ ሲሆን የስም መደቡ “ዘካህ” زَكَوٰة ነው። ይህ ቋንቋዊ ፍቺው ሲሆን ሃይማኖታዊ ፍቺው ደግሞ “ዘካህ” ማለት “የግዴታ ምጽዋት” ማለት ነው፥ አምላካችን አላህ ከሰጠን ሲሳይ ላይ የምንለግሰው ልግስና ዘካህ ይባላል፦
2፥277 እነዚያ ያመኑ፣ መልካም ሥራዎችንም የሠሩ፣ ሶላትንም ያስተካከሉ፣ *”ዘካንም የሰጡ ለእነርሱ በጌታቸው ዘንድ ምንዳቸው አላቸው፡፡ በእነርሱም ላይ ፍርሃት የለባቸውም እነርሱም አያዝኑም”*፡፡ إِنَّ الَّذِينَ آمَنُوا وَعَمِلُوا الصَّالِحَاتِ وَأَقَامُوا الصَّلَاةَ وَآتَوُا الزَّكَاةَ لَهُمْ أَجْرُهُمْ عِندَ رَبِّهِمْ وَلَا خَوْفٌ عَلَيْهِمْ وَلَا هُمْ يَحْزَنُونَ
8፥3 እነዚያ ሶላትን ደንቡን አሟልተው የሚሰግዱ *”ከሰጠናቸውም ሲሳይ የሚለግሱ ናቸው”*፡፡ الَّذِينَ يُقِيمُونَ الصَّلَاةَ وَمِمَّا رَزَقْنَاهُمْ يُنفِقُون

ዘካን የሚሰጡ አላህ ዘንድ ምንዳ አላቸው፥ በእነርሱም ላይ ፍርሃት የለባቸውም እነርሱም አያዝኑም። “ሪዝቅ” رِزْق ማለት “ሲሳይ” ማለት ሲሆን አምላካችን አላህ ደግሞ “አር-ረዛቅ” الرَّزَّاق ማለትም “ሲሳይን ሰጪ” ነው። “ኢንፋቅ” إِنفَاق ማለት “ልግስና” ማለት ሲሆን “ሙንፊቂን” مُنفِقِين ደግሞ “ለጋሾች” ማለት ነው። አምላካችን አላህ ከሰጠን ሲሳይ የምለግሰው ልግስና የበረከት ምንጭና ለአላህ ውዴታ ያለን መገለጫ ነው። ዘካህ መስጠት በረከትን ያፋፋል፥ ነገር ግን መስጠት ያለብን የአላህን ውዴታ ለመሻት እንጂ ትርፍ ፈልገን መሆን የበትም፦
2፥276 *”አላህ አራጣን በረከቱን ያጠፋል፡፡ ምጽዋቶችንም ያፋፋል”*፡፡ አላህም ኃጠኢተኛ ከሓዲን ሁሉ አይወድም፡፡ يَمْحَقُ اللَّهُ الرِّبَا وَيُرْبِي الصَّدَقَاتِ ۗ وَاللَّهُ لَا يُحِبُّ كُلَّ كَفَّارٍ أَثِيمٍ
30፥39 *”ከሪባም በሰዎች ገንዘቦች ውስጥ ይጨመር ዘንድ የምትሰጡት አላህ ዘንድ አይጨምርም፡፡ ከምጽዋትም የአላህን ፊት የምትሹ ሆናችሁ የምትሰጡት እነዚያ ሰጪዎች አበርካቾች እነርሱ ናቸው”*፡፡ وَمَا آتَيْتُم مِّن رِّبًا لِّيَرْبُوَ فِي أَمْوَالِ النَّاسِ فَلَا يَرْبُو عِندَ اللَّهِ ۖ وَمَا آتَيْتُم مِّن زَكَاةٍ تُرِيدُونَ وَجْهَ اللَّهِ فَأُولَـٰئِكَ هُمُ الْمُضْعِفُونَ
74፥6 *"ማብዛትንም የምትፈልግ ኾነህ አትለግስ"*። وَلَا تَمْنُن تَسْتَكْثِرُ

ዘካህ ከጥንት ጀምሮ ነቢያት እስካሉ ድረስ የነበረ ከኢሥላም ምሰሶ አንዱ ነው፥ አላህ ዘካንም ስለ መስጠት ትእዛዝ ከነቢያችን”ﷺ” በፊት ወደ ነበሩት ነቢያት አውርዷል፦
21፥73 *”ወደ እነርሱም መልካም ሥራዎችን መሥራትን፣ ሶላትንም መስገድን፣ ዘካንም መስጠትን አወረድን”*፡፡
وَأَوْحَيْنَآ إِلَيْهِمْ فِعْلَ ٱلْخَيْرَٰتِ وَإِقَامَ ٱلصَّلَوٰةِ وَإِيتَآءَ ٱلزَّكَوٰة
ስለዚህ የኢሥላም ማዕዘን የሆነው ዘካህ ኢሥላም እስካለ ድረስ ከጥንት ጀምሮ አለ ማለት ነው። ዘካህ ከነቢያችን”ﷺ” በፊት በነበሩት ነቢያት ጊዜ ከመቶ 2.5 % ላይሰጥ ይችል ይሆናል፥ ወይ ያንሳል አሊያም ይበዛ ይሆናል። ምናልባት ከመቶ 10 % አሥራት ሊሆን ይችል ይሆናል፥ ወሏሁ አዕለም።
በነቢያችን”ﷺ” ሸሪዓህ ግን ዘካህ ከካፒታል ላይ ከመቶ 2.5 % የሚሰጥ ነው፥ ነቢያችን”ﷺ” ከሁለት መቶ ዲርሀም 5% ዘካህ እንደሚወጣ ተናግረዋል። ያ ማለት የዘካህ ሒሳብ በመቶ ዲርሀም 5፥2=2.5 ይሆናል፦
2፥219 *”ምንን እንደሚመጸውቱም መጠኑን ይጠይቁሃል፡፡ «ትርፍን መጽውቱ» በላቸው”*፡፡ እንደዚሁ ታስተነትኑ ዘንድ አላህ ለእናንተ አንቀጾችን ይገልጽላችኋል፡፡ وَيَسْأَلُونَكَ مَاذَا يُنفِقُونَ قُلِ الْعَفْوَ ۗ كَذَٰلِكَ يُبَيِّنُ اللَّهُ لَكُمُ الْآيَاتِ لَعَلَّكُمْ تَتَفَكَّرُونَ
ሡነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 9, ሐዲስ 18 ዐሊይ”ረ.ዐ” እንደተረከው፦ “ነቢዩም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ *”ሁለት መቶ ዲርሀም ለአንተ በሆነች ጊዜና ዓመት ከሞላች አምስት ደራሂም ይወጣል፥ በአንተ ምንም ነገር አይሆንም ሃያ ዲናር እስኪሆን ድረስ”*። عَنْ عَلِيٍّ، – رضى الله عنه – عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم بِبَعْضِ أَوَّلِ هَذَا الْحَدِيثِ قَالَ ‏”‏ فَإِذَا كَانَتْ لَكَ مِائَتَا دِرْهَمٍ وَحَالَ عَلَيْهَا الْحَوْلُ فَفِيهَا خَمْسَةُ دَرَاهِمَ وَلَيْسَ عَلَيْكَ شَىْءٌ – يَعْنِي فِي الذَّهَبِ – حَتَّى يَكُونَ
90 views20:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-28 23:25:00
85 views20:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-27 22:56:32 ሃይማኖት ያድናል!

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

3፥19 አላህ ዘንድ የተወደደ ሃይማኖት ኢሥላም ብቻ ነው፡፡ إِنَّ الدِّينَ عِندَ اللَّهِ الْإِسْلَامُ

ፕሮቴስታንት፦ "እምነት እንጂ ሃይማኖት አያድንም" የሚል መፈክር አላቸው፥ ከፕሮቴስታንት የተሃድሶ አምስቱ የብቸኝነት መፈክር አንዱ "መዳን በእምነት ብቻ"sola fide" የሚል ነው። እኛም እንደ ሙሥሊምነታችን እውነት ሃይማኖት አያድንምን? ለሚለው ጥያቄ ምላሽ ኢንሻሏህ እንሰጣለን። 
"ዲን" دِين የሚለው ቃል "ዳነ" دَانَ ማለትም "ሃይመነ" "ደነገገ"  "ፈረደ" "በየነ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ሃይማኖት" "ፍትሕ" "ፍርድ" "ሕግ" "መርሕ"doctrine" ማለት ነው፦
2፥256 "በሃይማኖት" ማስገደድ የለም፡፡ لَا إِكْرَاهَ فِي الدِّينِ
1፥4 "የፍርዱ" ቀን ባለቤት ለኾነው፡፡ مَالِكِ يَوْمِ الدِّينِ
12፥76 አላህ ባልሻ ኖሮ በንጉሡ "ሕግ" ወንድሙን ሊይዝ አይገባውም ነበር፡፡ كَانَ لِيَأْخُذَ أَخَاهُ فِي دِينِ الْمَلِكِ إِلَّا أَن يَشَاءَ اللَّهُ

እነዚህ አናቅጽ ላይ "ሃይማኖት" "ፍርድ" "ሕግ" ለሚለው የገባው ቃል "ዲን" دِين መሆኑ አንባቢ ልብ ይለዋል፥ ዲን የእምነት እሴት፣ የእምነት አንቀጽ እና የሥነ-ምግባር መርሕ ነው። ዲን ምእመናንን ወንድማማች የሚያደርግ መርሕ ነው፦
9፥11 ቢጸጸቱም፣ ሶላትንም ቢሰግዱ፣ ዘካንም ቢሰጡ "የሃይማኖት ወንድሞቻችሁ" ናቸው፡፡ فَإِن تَابُوا وَأَقَامُوا الصَّلَاةَ وَآتَوُا الزَّكَاةَ فَإِخْوَانُكُمْ فِي الدِّينِ
49፥10 "ምእመናን ወንድማማቾች ናቸው"፡፡ إِنَّمَا الْمُؤْمِنُونَ إِخْوَةٌ

"አኽ" أَخ ማለት "ወንድም" ማለት ሲሆን "ኡኽት" أُخْت ማለት ደግሞ "እኅት" ማለት ነው፥ "ኢኽዋህ" إِخْوَة ወይም "ኢኽዋን" إِخْوَان ለሁለቱም ብዜት ሆኖ የሚያገለግል ቃል ነው። ዲን ማለት የእምነት መርሕ መሆኑ ካየን ዘንዳ ይህም ዲን ዲኑል ኢሥላም ነው፦
3፥19 አላህ ዘንድ የተወደደ ሃይማኖት ኢሥላም ብቻ ነው፡፡ إِنَّ الدِّينَ عِندَ اللَّهِ الْإِسْلَامُ
3፥85 ከኢሥላም ሌላ ሃይማኖትን የሚፈልግ ሰው ፈጽሞ ከእርሱ ተቀባይ የለውም፡፡ እርሱም በመጨረሻይቱ ዓለም ከከሳሪዎቹ ነው፡፡ وَمَن يَبْتَغِ غَيْرَ الْإِسْلَامِ دِينًا فَلَن يُقْبَلَ مِنْهُ وَهُوَ فِي الْآخِرَةِ مِنَ الْخَاسِرِينَ

"ኢሥላም" إِسْلَام የሚለው ቃል "አሥለመ" أَسْلَمَ‎ ማለትም "ታዘዘ" "ተገዛ" "አመለከ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "መታዘዝ" "መገዛት" "ማምለክ" ማለት ነው፥ አሏህ ዘንድ ከዲኑል ኢሥላም ሌላ ሃይማኖትን ተቀባትነት የሌለው እና በመጨረሻይቱ ዓለም የሚያከስር ነው። አምላካችን አሏህ ለኢብራሂም፦ "አሥሊም" أَسْلِمْ ሲለው እርሱም፦ "አሥለምቱ" أَسْلَمْتُ አለ፦
2፥131 ጌታው ለእርሱ ”ታዘዝ” ባለው ጊዜ መረጠው፡፡ ለዓለማት ጌታ ”ታዘዝኩ” አለ፡፡ إِذْ قَالَ لَهُۥ رَبُّهُۥٓ أَسْلِمْ ۖ قَالَ أَسْلَمْتُ لِرَبِّ ٱلْعَٰلَمِينَ
22፥34 አምላካችሁም አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ ለእርሱም ብቻ "ታዘዙ"! ለአላህ ተዋራጆችንም አብስራቸው፡፡ فَإِلَـٰهُكُمْ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ فَلَهُ أَسْلِمُوا ۗ وَبَشِّرِ الْمُخْبِتِينَ

"አምላካችሁም አንድ አምላክ ብቻ ነው" የሚለው ኃይለ-ቃል ይስመርበት! በቀጣይ "ታዘዙ" ለሚለው ቃል የተቀመጠው "አሥሊሙ" أَسْلِمُوا ነው፥ ስለዚህ አንዱን አምላክ በብቸኝነት መታዘዝ፣ መገዛት፣ ማምለክ "ኢሥላም" ይባላል።
"ኢማን" إِيمَٰن የሚለው ቃል "አሚነ" أَمِنَ ማለትም "አመነ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "እምነት" ማለት ነው፥ የምናምነው ደግሞ ዲናችን ላይ የተቀመጠውን መርሕ ነው እንጂ ጣዖትን እኮ እንክዳለን፦
2፥256 “በጣዖትም የሚክድ እና በአላህ የሚያምን ሰው ለእርሷ መበጠስ የሌላትን ጠንካራ ዘለበት በእርግጥ ጨበጠ”፡፡ فَمَن يَكْفُرْ بِالطَّاغُوتِ وَيُؤْمِن بِاللَّهِ فَقَدِ اسْتَمْسَكَ بِالْعُرْوَةِ الْوُثْقَىٰ لَا انفِصَامَ لَهَا

የምናምነው የምናውቀውን ነው፥ የምናውቀው ደግሞ ከአሏህ ዘንድ የመጣውን መርሕ ነው። "ኢማን እንጂ ዲን አያድንም" የሚሉ ፕሮቴስታንቶች ሃይማኖት የእምነት መርሕ መሆኑን በቅጡ ስላልተረዱት እና የሚያምኑበት መርሕ ስለሌላቸው ነው፥ ይህ መረን አልባ ልቅነት ነው። ሃይማኖት ሥርወ-እምነት ነው፥ "ዶግማ" δόγμα ማለት "አንቀጸ-እምነት"creed" ማለት ሲሆን ያለ ዶግማ እምነት የማይታሰብ ነው።  ስለዚህ ዲኑል ኢሥላም ድብን አድርጎ ያድናል፦
3፥103 የአላህን ገመድ ሁላችሁም ያዙ! አትለያዩም። ጠበኞችም በነበራችሁ ጊዜ በእናንተ ላይ የዋለውን የአላህን ጸጋ አስታውሱ! በልቦቻችሁም መካከል አስማማ፥ በጸጋውም ወንድማማቾች ኾናችሁ፡፡ በእሳት ጉድጓድ አፋፍም ላይ ነበራችሁ፥ ከእርስዋም አዳናችሁ፡፡ እንደዚሁ ትመሩ ዘንድ አላህ ለእናንተ አንቀጾቹን ያብራራል፡፡  وَاعْتَصِمُوا بِحَبْلِ اللَّهِ جَمِيعًا وَلَا تَفَرَّقُوا ۚ وَاذْكُرُوا نِعْمَتَ اللَّهِ عَلَيْكُمْ إِذْ كُنتُمْ أَعْدَاءً فَأَلَّفَ بَيْنَ قُلُوبِكُمْ فَأَصْبَحْتُم بِنِعْمَتِهِ إِخْوَانًا وَكُنتُمْ عَلَىٰ شَفَا حُفْرَةٍ مِّنَ النَّارِ فَأَنقَذَكُم مِّنْهَا ۗ كَذَٰلِكَ يُبَيِّنُ اللَّهُ لَكُمْ آيَاتِهِ لَعَلَّكُمْ تَهْتَدُونَ

ከእሳት ጉድጓድ ተንጠልጥሎ ለመውጣት የሚያስችል ብቸኛው የአሏህ ገመድ ዲኑል ኢሥላም ብቻ ነው፥ ከእሳት ጉድጓድ አፋፍ ላይ ሳለን አድኖ በሃይማኖት ወንድማማቾች አርጎናል። ሱመ አል-ሓምዱ ሊሏህ!
አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ

መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
‐‐‐
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen

ወሠላሙ ዐለይኩም
278 views19:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-27 22:56:02
263 views19:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-24 21:36:12 https://vm.tiktok.com/ZMYCD4F85/
 
ቲክቶክ ቻነላችን ላይ አዲስ ቪዲዬ


መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
‐‐‐
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
449 views18:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ