Get Mystery Box with random crypto!

Tiriyachen | ጥሪያችን

የቴሌግራም ቻናል አርማ tiriyachen — Tiriyachen | ጥሪያችን T
የቴሌግራም ቻናል አርማ tiriyachen — Tiriyachen | ጥሪያችን
የሰርጥ አድራሻ: @tiriyachen
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.91K

Ratings & Reviews

1.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2023-04-11 04:37:01 መካህ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

90፥1 *"በዚህ አገር እምላለሁ"*፡፡ لَا أُقْسِمُ بِهَـٰذَا الْبَلَدِ

"መካህ" مَـكَّـة‎ ማለት "የተመጠመጠ" ማለት ሲሆን "በካህ" بَكَّة ማለት ደግሞ የመካህ ተለዋዋጭ ቃል ነው። ልክ አንድ ሕጻን ልጅ የእናቱን ጡት ምጥጥ እንደሚያደርግ ሁሉ ስፍራው ውኃ ምጥጥ የሚያረግ ስለሆነ ይህንን ስም ተሰየመ። ይህ አገር አላህ የማለበት እና ነቢያችን"ﷺ" የሰፈሩበት አገር ነው፥ አላህም የዚህ አገር ጌታ ተብሏል፦
90፥1 *"በዚህ አገር እምላለሁ"*፡፡ لَا أُقْسِمُ بِهَـٰذَا الْبَلَدِ
90፥2 *"አንተ በዚህ አገር ሰፋሪ ስትኾን"*፡፡ وَأَنتَ حِلٌّ بِهَـٰذَا الْبَلَدِ
27፥91 *"የታዘዝኩት የዚህችን አገር ጌታ ያንን ክልል ያደረጋትን እንዳመልክ ብቻ ነው"*፡፡ ነገሩንም ሁሉ የእርሱ ነው፡፡ ከሙስሊሞችም እንድኾን ታዝዣለሁ" በላቸው፡፡ إِنَّمَا أُمِرْتُ أَنْ أَعْبُدَ رَبَّ هَـٰذِهِ الْبَلْدَةِ الَّذِي حَرَّمَهَا وَلَهُ كُلُّ شَيْءٍ ۖ وَأُمِرْتُ أَنْ أَكُونَ مِنَ الْمُسْلِمِين

ይህ አገር ጸጥተኛ አገር ነው፥ ኢብራሂም በዱዓው ይህ አገር ጸጥተኛ እንዲሆን እና እርሱና ልጆቹንም ጣዖታትን ከማምለክ እንዲያርቅ አላህን የለመነበት አገር ነው፦
95፥3 *"በዚህ በጸጥተኛው አገርም እምላለሁ"*፡፡ وَهَـٰذَا الْبَلَدِ الْأَمِينِ
2፥126 ኢብራሂም ባለ ጊዜ አስታውስ፦ "ጌታዬ ሆይ! *"ይህንን ጸጥተኛ አገር አድርግ"*፡፡ وَإِذْ قَالَ إِبْرَاهِيمُ رَبِّ اجْعَلْ هَـٰذَا بَلَدًا آمِنًا
14፥35 ኢብራሂምም ባለ ጊዜ አስታውስ፦ «ጌታዬ ሆይ! *"ይህንን አገር ጸጥተኛ አድርገው፡፡ እኔንም ልጆቼንም ጣዖታትን ከማምለክ አርቀን"*፡፡ وَإِذْ قَالَ إِبْرَاهِيمُ رَبِّ اجْعَلْ هَـٰذَا الْبَلَدَ آمِنًا وَاجْنُبْنِي وَبَنِيَّ أَن نَّعْبُدَ الْأَصْنَامَ

አምላካችን አላህ በዚህ አገር በሚገኘው ጥንታዊ ቤት አጽንዖት ለመስጠት ምሏል፥ እልቅና እና ክብር በመስጠት ወደ ራሱ በማስጠጋት “በይቲይ” بَيْتِىَ ማለትም “ቤቴ” በማለት ይናገራል፦
52፥4 *"በደመቀው ቤትም እምላለው"*፡፡ وَالْبَيْتِ الْمَعْمُورِ
22፥26 ለኢብራሂምም፦ *”የቤቱን” ስፍራ መመለሻ ባደረግንለት ጊዜ፣ በእኔ ምንንም አታጋራ! ”ቤቴንም” ለሚዞሩትና ለሚቆሙበት፣ ለሚያጎነብሱትና በግንባራቸውም ለሚደፉት ንጹሕ አድርግላቸው፣ ”ባልነው ጊዜ አስታውስ”*። وَإِذْ بَوَّأْنَا لِإِبْرَٰهِيمَ مَكَانَ ٱلْبَيْتِ أَن لَّا تُشْرِكْ بِى شَيْـًۭٔا وَطَهِّرْ بَيْتِىَ لِلطَّآئِفِينَ وَٱلْقَآئِمِينَ وَٱلرُّكَّعِ ٱلسُّجُودِ

"ሚዞሩት” ተብሎ የተቀመጠው ቃል “ጧዒፊን” طَّائِفِين መሆኑ አንባቢ ልብ ይለዋል። “ጦዋፍ” طَواف የሚለው ቃል “ጧፈ” طَافَ ማለትም “ዞረ” ከሚለው ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ዙረት” ማለት ነው። ቤቱን በመጎብኘት ሰባት ጊዜ መዞር አምላካችን አላህ ለኢብራሂም የሰጠው ትእዛዝ ነው፦
22፥29 ከዚያም እንደ ጠጉርና ጥፍር ያሉትን ትርፍ አካላቸውንና ዕድፋቸውን ያስወግዱ፡፡ ስለቶቻቸውንም ይሙሉ፤ *በጥንታዊውም ቤት ይዙሩ*፡፡ ثُمَّ لْيَقْضُوا تَفَثَهُمْ وَلْيُوفُوا نُذُورَهُمْ وَلْيَطَّوَّفُوا بِالْبَيْتِ الْعَتِيقِ

“ይዙሩ” ተብሎ የተቀመጠው ቃል “የጠወፉ” يَطَّوَّفُوا መሆኑ አንባቢ ልብ ይለዋል። ቤቱን የሚዞሩት ዘዋሪዎች ደግሞ “ጧዒፍ” طَآئِف ይባላሉ፥ ለሰዎች መጸለያ መጀመሪያ የተኖረው ቤት በዚህ አገር ውስጥ ይገኛል፦
3፥96 *"ለሰዎች መጸለያ መጀመሪያ የተኖረው ቤት ብሩክና ለዓለማት ሁሉ መመሪያ ሲኾን ያ በበካህ ያለው ነው"*፡፡ إِنَّ أَوَّلَ بَيْتٍ وُضِعَ لِلنَّاسِ لَلَّذِي بِبَكَّةَ مُبَارَكًا وَهُدًى لِّلْعَالَمِينَ

የዚህን ቤት መሠረት የጣለው ኢብራሂም ነው፥ መካህን የቀደሰውም እርሱ ነው። ነቢያችን"ﷺ" መዲናን ለመሥጂድ እንደቀደሱት ኢብራሂም መካህን ለመስጂደል ሐረም ቀድሶታል፦
2፥127 *ኢብራሂምና ኢስማኢልም* «ጌታችን ሆይ! ከእኛ ተቀበል፡፡ አንተ ሰሚውና ዐዋቂው አንተ ነህና» የሚሉ ሲኾኑ *"ከቤቱ መሠረቶቹን ከፍ ባደረጉ ጊዜ አስታውስ"*፡፡ وَإِذْ يَرْفَعُ إِبْرَاهِيمُ الْقَوَاعِدَ مِنَ الْبَيْتِ وَإِسْمَاعِيلُ رَبَّنَا تَقَبَّلْ مِنَّا ۖ إِنَّكَ أَنتَ السَّمِيعُ الْعَلِيمُ
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 15, ሐዲስ 521
ጃቢር እንደተረከው፦ "ነቢዩም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ *"ኢብራሂም መካን ቀድሷል፥ እኔም መዲናን ቀድሻለው"*። عَنْ جَابِرٍ، قَالَ قَالَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ إِنَّ إِبْرَاهِيمَ حَرَّمَ مَكَّةَ وَإِنِّي حَرَّمْتُ الْمَدِينَةَ

"ሐረምቱ" حَرَّمْتُ የሚለው ኃይለ-ቃል ይሰመርበት። "ሐረመ" حَرَّمَ ማለት "ቀደሰ" ወይም "አከበረ" ማለት ነው፥ ይህ መካህ የሚገኘው ቤት እራሱ "በይተል ሐረም” ْبَيْتَ ٱلْحَرَامَ ማለትም “የተቀደሰው ቤት” ወይም "የተከበረው ቤት" ይባላል፦
14፥37 «ጌታችን ሆይ! እኔ *"አዝመራ በሌለው ሸለቆ ውስጥ በተከበረው ቤት አጠገብ ከዘሮቼ አስቀመጥኩ፡፡ ጌታችን ሆይ! ሶላትን ያቋቁሙ ዘንድ አስቀመጥኳቸው"*፡፡ ከሰዎችም ልቦችን ወደ እነርሱ የሚናፍቁ አድርግ፡፡ ያመሰግኑህም ዘንድ ከፍሬዎች ስጣቸው፡፡ رَّبَّنَا إِنِّي أَسْكَنتُ مِن ذُرِّيَّتِي بِوَادٍ غَيْرِ ذِي زَرْعٍ عِندَ بَيْتِكَ الْمُحَرَّمِ رَبَّنَا لِيُقِيمُوا الصَّلَاةَ فَاجْعَلْ أَفْئِدَةً مِّنَ النَّاسِ تَهْوِي إِلَيْهِمْ وَارْزُقْهُم مِّنَ الثَّمَرَاتِ لَعَلَّهُمْ يَشْكُرُون

ኢብራሂም በተከበረው ቤት አጠገብ ከዘሮቼምቹ ሶላትን ያቋቁሙ ዘንድ አስቀምጧል፥ ከዘሮቹም አዘውትረው ለአላህ የሚሰግዱ እና የሚታዘዙ እንዲሆኑ ዱዓ አርጓል፦
10፥40 «ጌታዬ ሆይ! *ሰላትን አዘውትሬ የምሰግድ አድርገኝ፡፡ ከዘሮቼም አድርግ*፡፡ ጌታችን ሆይ! ጸሎቴንም ተቀበለኝ። رَبِّ اجْعَلْنِي مُقِيمَ الصَّلَاةِ وَمِن ذُرِّيَّتِي ۚ رَبَّنَا وَتَقَبَّلْ دُعَاءِ
2፥128 «ጌታችን ሆይ! *"ለአንተ ታዛዦችም አድርገን፡፡ ከዘሮቻችንም ለአንተ ታዛዦች ሕዝቦችን አድርግ"*፡፡ ሕግጋታችንንም አሳውቀን፡፡ በእኛም ላይ ተመለስን፤ አንተ ጸጸትን ተቀባዩ ሩኅሩኅ አንተ ብቻ ነህና፡፡» رَبَّنَا وَاجْعَلْنَا مُسْلِمَيْنِ لَكَ وَمِن ذُرِّيَّتِنَا أُمَّةً مُّسْلِمَةً لَّكَ وَأَرِنَا مَنَاسِكَنَا وَتُبْ عَلَيْنَا ۖ إِنَّكَ أَنتَ التَّوَّابُ الرَّحِيمُ
245 views01:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 04:36:51
234 views01:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-09 01:16:02 ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 65, ሐዲስ 4720
ዐብደላህ ኢብኑ መሥዑድ”ረ.ዐ.” እንደተረከው፦ *”ነቢዩ”ﷺ” ወደ መካህ ሲገቡ በካዕባህ ዙሪያ ሦስት መቶ ስልሳ ጣዖታት ነበሩ፤ በመንሽ እየሰባበሯቸው፦ “እውነት መጣ ውሸትም ተወገደ፤ እነሆ ውሸት ተወጋጅ ነውና” “እውነቱ መጣ፡፡ ውሸትም መነሻም መድረሻም የለውም ተወገደ” አሉ”*። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ مَسْعُودٍ ـ رضى الله عنه ـ قَالَ دَخَلَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم مَكَّةَ وَحَوْلَ الْبَيْتِ سِتُّونَ وَثَلاَثُمِائَةِ نُصُبٍ فَجَعَلَ يَطْعُنُهَا بِعُودٍ فِي يَدِهِ وَيَقُولُ ‏{‏جَاءَ الْحَقُّ وَزَهَقَ الْبَاطِلُ إِنَّ الْبَاطِلَ كَانَ زَهُوقًا‏}‏ ‏{‏جَاءَ الْحَقُّ وَمَا يُبْدِئُ الْبَاطِلُ وَمَا يُعِيدُ‏}‏

የተያያዝነው የሃይማኖት ንጽጽር ትምህርት እስከሆነ ድረስ በባብይል ቢሆን የአምላክ ቤት መሰረቱ ድንጋይ እንደሆነ ማነጻጸር አለባችሁ፦
ዘፍጥረት 28፥18-19 ያዕቆብም ማልዶ ተነሣ፥ ተንተርሶት የነበረውንም *ድንጋይ ወስዶ ሐውልት” አድርጎ አቆመው፥ በላዩም “ዘይትን አፈሰሰበት”። ያዕቆብም ያንን ስፍራ ”ቤቴል”* ብሎ ጠራው፤
ዘፍጥረት 28፥22 *ለሐውልት የተከልሁት ይህም ”ድንጋይ የእግዚአብሔር ቤት” ይሆናል*፤
ዘፍጥረት 35፥14 ያዕቆብም እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር በተነጋገረበት ቦታ *”የድንጋይ ሐውልት” ተከለ፤ የመጠጥ መሥዋዕትንም በእርሱ ላይ ”አፈሰሰ”፥ ዘይትንም *”አፈሰሰበት”*።
ኢያሱ 24፥26 ኢያሱም ይህን ቃል ሁሉ በእግዚአብሔር ሕግ መጽሐፍ ጻፈ *”ታላቁንም ድንጋይ” ወስዶ ”በእግዚአብሔር ”መቅደስ” አጠገብ ከነበረችው ከአድባሩ ዛፍ በታች አቆመው*።

ልብ አድርጉ “ቤት-ኤል” ማለት “የአምላክ ቤት” ማለት ነው። ያዕቆብ ድንጋዩን ወስዶ ሐውልት አድርጎ “የአምላክ ቤት” ብሎታል፥ ከዚያም ባሻገር የመጠጥ መሥዋዕትን እና ዘይትንም በእርሱ ላይ አፈሰሰበት። ኢያሱም ይህን ታላቁንም ድንጋይ ወስዶ በእግዚአብሔር መቅደስ አጠገብ ከነበረችው ከአድባሩ ዛፍ በታች አቆመው፥ ሰዎች የትም ሆነው ወደዚህ ቤት ይጸልያሉ ወይም ይሰግዳሉ፦
1ኛ ነገሥት 8፥48-49 በማረኩአቸው በጠላቶቻቸው አገር ሳሉ በፍጹም ልባቸውና በፍጹም ነፍሳቸው ወደ አንተ ቢመለሱ፥ ለአባቶቻቸው ወደ ሰጠሃት ወደ ምድራቸው ወደ መረጥሃትም ከተማ ለስምህም *”ወደ ሠራሁት ቤት ቢጸልዩ”*፥ ጸሎታቸውንና ልመናቸውን በማደሪያህ በሰማይ ስማ፥
መዝሙር 5፥7 እኔ ግን በምሕረትህ ብዛት *”ወደ ቤትህ” እገባለሁ፤ አንተን በመፍራት ”ወደ ቅድስናህ መቅደስ እሰግዳለሁ”*።
መዝሙር 138፥2 *”ወደ ቅዱስ መቅደስህ እሰግዳለሁ”*፤

“ወደ መቅደሱ” ወይንም “ወደ ቤቱ” መስገድ እና መፀለይ ለመቅደሱ እና ለቤቱ መፀለይ እና መስገድ ነውን? መልሱ፦ "አይ የሚሰገደው እና የሚፀለየው ለፈጣሪ እንጂ “ለመቅደሱ” ወይንም “ለቤቱ” አይደለም" ነው። “ወደ” እና “ለ” የሚባሉትን መስተዋድድ በአፅንዖትና በአንክሮት መመልከት ያሻል። ያለበለዚያ ቂብላህ የተቀጣጫችሁበት ስፍራ መሰረቱ ድንጋይ ስለሆነ ጣዖት አምልኮ ይሆናል፦
ዘሌዋውያን 26፥1 እኔ ያህዌህ አምላካችሁ ነኝና ለእናንተ *”ጣዖት አታድርጉ”፥ ”የተቀረጸም ምስል” ወይም *”ሐውልት” አታቁሙ፤ ትሰግዱለትም ዘንድ በምድራችሁ ላይ ”የተቀረጸ ድንጋይ” አታኑሩ*።

ታዲያ ያዕቆብ ሐውልት አድርጎ ያቆመው ድንጋይ ጣዖት ካልሆነ ምንድን ነው? ስንል መልሱ የአምላክ ቤት ነው። ይህ ቤት አቅጣጫ መቀጣጫ ነው እንጂ ፈጣሪ ”ሐውልት አታቁሙ፤ ትሰግዱለትም ዘንድ በምድራችሁ ላይ የተቀረጸ ድንጋይ አታኑሩ” ካለው ጣዖት ጋር ይለያያል ከሆነ መልሱ እንግዲያውስ ስለ ሐጀሩል አሥወድ በዚህ ስሌትና ቀመር ተረዱት።

ወሒድ ዐቃቢ ኢሥላም

መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
‐‐‐
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen

ወሠላሙ ዐለይኩም
397 views22:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-09 01:16:02 ሐጀሩል አሥወድ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

29፥56 እናንተ ያመናችሁ ባሮቼ ሆይ! ምድሬ በእርግጥ ሰፊ ናት፤ ብትቸገሩ ተሰደዱ፡፡ *”እኔንም ብቻ አምልኩኝ”*፡፡ يَٰعِبَادِىَ ٱلَّذِينَ ءَامَنُوٓا۟ إِنَّ أَرْضِى وَٰسِعَةٌۭ فَإِيَّٰىَ فَٱعْبُدُونِ

አምላካችን አላህ ብዙ አንቀጾች ላይ “አምልኩኝ” እያለ በመጀመሪያ መደብ ይናገራል፦
29፥56 እናንተ ያመናችሁ ባሮቼ ሆይ! ምድሬ በእርግጥ ሰፊ ናት፤ ብትቸገሩ ተሰደዱ፡፡ *”እኔንም ብቻ አምልኩኝ”*፡፡ يَٰعِبَادِىَ ٱلَّذِينَ ءَامَنُوٓا۟ إِنَّ أَرْضِى وَٰسِعَةٌۭ فَإِيَّٰىَ فَٱعْبُدُونِ
21፥92 ይህች አንዲት መንገድ ስትሆን በእርግጥ ሃይማኖታችሁ ናት፤ *”እኔም ጌታችሁ ነኝና አምልኩኝ”*፡፡ إِنَّ هَٰذِهِۦٓ أُمَّتُكُمْ أُمَّةًۭ وَٰحِدَةًۭ وَأَنَا۠ رَبُّكُمْ فَٱعْبُدُونِ
21፥25 ከአንተ በፊትም እነሆ *”ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና አምልኩኝ”* በማለት ወደ እርሱ *”የምናወርድለት”* ቢኾን እንጅ ከመልክተኛ አንድንም አልላክንም፡፡ وَمَآ أَرْسَلْنَا مِن قَبْلِكَ مِن رَّسُولٍ إِلَّا نُوحِىٓ إِلَيْهِ أَنَّهُۥ لَآ إِلَٰهَ إِلَّآ أَنَا۠ فَٱعْبُدُونِ
51፥56 *ጂኒን እና ሰውንም ሊያመልኩኝ እንጅ ለሌላ አልፈጠርኳቸውም*፡፡ وَمَا خَلَقْتُ الْجِنَّ وَالْإِنسَ إِلَّا لِيَعْبُدُونِ

የማይጠቅም እና የማይጎዳን ማንነት እና ምንነት ማምለክ ደግሞ ትልቅ በደል ነው፥ መመለክ የሚገባው የሰማያትና የምድር ጌታ አላህ ብቻ ነው፦
10፥106 *«ከአላህም በቀር የማይጠቅምንና የማይጎዳን አትገዛ*፡፡ ብትሠራም አንተ ያን ጊዜ ከበደለኞቹ ትሆናለህ?» ተብያለሁ በላቸው፡፡ وَلَا تَدْعُ مِن دُونِ اللَّهِ مَا لَا يَنفَعُكَ وَلَا يَضُرُّكَ ۖ فَإِن فَعَلْتَ فَإِنَّكَ إِذًا مِّنَ الظَّالِمِينَ
5፥76 *«ከአላህ ሌላ ለእናንተ መጉዳትንና መጥቀምን የማይችልን ትገዛላችሁን?»* በላቸው፡፡ አላህም እርሱ ሰሚው ዐዋቂ ነው፡፡ قُلْ أَتَعْبُدُونَ مِن دُونِ اللَّهِ مَا لَا يَمْلِكُ لَكُمْ ضَرًّا وَلَا نَفْعًا ۚ وَاللَّهُ هُوَ السَّمِيعُ الْعَلِيمُ
13፥16 *«የሰማያትና የምድር ጌታ ማን ነው» በላቸው፡፡ «አላህ ነው» በል፡፡ «ለነፍሶቻቸው ጥቅምንም ጉዳትንም የማይችሉን ረዳቶች ከእርሱ ሌላ ያዛችሁን?»* በላቸው፡፡ قُلْ مَن رَّبُّ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ قُلِ اللَّهُ ۚ قُلْ أَفَاتَّخَذْتُم مِّن دُونِهِ أَوْلِيَاءَ لَا يَمْلِكُونَ لِأَنفُسِهِمْ نَفْعًا وَلَا ضَرًّا

“ሐጀሩል አሥወድ” حَجَرُ الأَسْوَد ማለት መጥቀምም መጉዳትም የማይችል ድንጋይ ስለሆነ በፍጹም አይመለክም፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 25, ሐዲስ 83
ዓቢሥ ኢብኑ ረቢዓህ እንደተረከው፦ *”ዑመር”ረ.ዐ.” ወደ ሐጀሩል አሥወድ መጥቶ ሳመውና፦ “ዐውቃለው አንተ ድንጋይ ነህ፥ አትጠቅምም አትጎዳም። ነቢዩ”ﷺ” ሲስሙህ ባላይ ኖሮ አልስምህም ነበር” አለ"*። عَنْ عَابِسِ بْنِ رَبِيعَةَ، عَنْ عُمَرَ ـ رضى الله عنه ـ أَنَّهُ جَاءَ إِلَى الْحَجَرِ الأَسْوَدِ فَقَبَّلَهُ، فَقَالَ إِنِّي أَعْلَمُ أَنَّكَ حَجَرٌ لاَ تَضُرُّ وَلاَ تَنْفَعُ، وَلَوْلاَ أَنِّي رَأَيْتُ النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم يُقَبِّلُكَ مَا قَبَّلْتُكَ‏

“አትጠቅምም አትጎዳም” የሚለው ኃይለ-ቃል ይሰመርበት። ምን ትፈልጋለህ? ሐጀሩል አሥወድ የማይጠቅም የማይጎዳ ነገር ነው። የፈጣሪ ሐቅ ደግሞ አምልኮ ነው፥ ከአምልኮ አይነቶች መካከል መለማመን፣ ስእለት መሳል፣ መስገድ ወዘተ ናቸው። ነገር ግን “መሳም” የመውደድ መገለጫ እንጂ በራሱ መውደድ አይደለም፥ ምክንያቱም ሳንስማቸው የምንወዳቸው ሰዎች ስላሉ። ሲቀጥል “መሳም” የፈጣሪ ሐቅ አይደለም፥ ፈጣሪ አይሳምምና። ሢሠልስ “መሳም” የፍጡራን መብት ነው፥ አምልኮም አይደለም። አንድ ሰው አባቱን ሳመ ማለት አመለከ ማለት አይደለም፥ አንድ ሰው በእግር ኳስ አሸንፎ ዋንጫ ቢስም አመለከ አይባልም። ሲያረብብ ለሐጀሩል አሥወድ አምልኮ ሆነ የአምልኮ ክፍሎች የሆኑት መለማመን፣ ስእለት መሳል፣ መስገድ ወዘተ ቢቀርብ ኖሮ ይህ ማሻረክ ወይም ባዕድ አምልኮ ይሆን ነበር፥ ቅሉ ግን ይህ ድርጊት በኢሥላም ፈፅሞ ሽርክ ይሰኛል አይደረግም። በድንጋይና በድንጋይ ላይ የሚደረግ አምልኮ “ኑሱብ” نُصُب እና “አዝላም” أَزْلَٰم ናቸው፥ “ኑስብ” نُصْب ማለት “ሐውልት” ማለት ሲሆን የኑስብ ብዙ ቁጥር ደግሞ “ኑሱብ” نُصُب ወይም “አንሷብ” أَنْصَاب ነው። “አዝላም” أَزْلاَم ማለት ደግሞ “የጥንቆላ ቀስት” ማለት ነው። አንሷብም አዝላምም ከሰይጣን ሥራ የኾኑ እርኩስ ብቻ ናቸው፦
5፥90 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! የሚያሰክር መጠጥ ቁማርም *”አንሳብ” እና “አዝላምም” ከሰይጣን ሥራ የኾኑ እርኩስ ብቻ ናቸው፡፡ እርኩስን ራቁትም ልትድኑ ይከጀላልና*፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا إِنَّمَا الْخَمْرُ وَالْمَيْسِرُ وَالْأَنصَابُ وَالْأَزْلَامُ رِجْسٌ مِّنْ عَمَلِ الشَّيْطَانِ فَاجْتَنِبُوهُ لَعَلَّكُمْ تُفْلِحُونَ

ሐጀሩል አሥወድ በምስሉ ላይ እንደምትመለከቱት የተሰባበረ ድንጋይ ነው። መስማት፣ መናገር፣ ማየት፣ ማወቅ የማይችል ሕያው ያልሆነው ለአላህ ቤት መሰረት ለመሆን ከጀነት የመጣ ነው፦
ሡነን ነሳኢ መጽሐፍ 24, ሐዲስ 2938
ኢብኑ ዐባሥ”ረ.ዐ.” እንደተረከው ነቢዩም”ﷺ” አሉ፦ *”ሐጀሩል አሥወድ ከጀነት ነው”*። عَنِ ابْنِ عَبَّاسٍ، أَنَّ النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ “‏ الْحَجَرُ الأَسْوَدُ مِنَ الْجَنَّةِ ‏”‏ ‏.
ይህ በሚሽነሪዎች እንደ ባዕድ አምልኮ ለምን እንደሚታሰብ አይገባኝም። ሐጀሩል አሥወድ በዘመነ- ጃህሊያህ ጊዜ ከሦስት መቶ ስድሳ ጣዖታት መካከል ይመለክ እንደነበር የሚያሳይ የቁርኣን፣ የሐዲስ፣ የታሪክ እና የሥነ-ቅርስ ጥናት መረጃ የለም። አለ የሚል ሰው ካለ ጠቅሶና አጣቅሶ በእማኝነትና በአስረጂነት ይንገረን! እኛም በአጽንዖትና በአንክሮት እንሰማለን። ነቢያችን”ﷺ” ወደ መካ ሲገቡ በካዕባህ ዙሪያ የሚመለኩ ሦስት መቶ ስድሳ ጣዖታትን ነበሩ፥ ሁሉንም ሰባብረዋል። ያስቀሩት አንድም ጣዖት የለም፦
ነቢያችን”ﷺ” ወደ መካ ሲገቡ በካዕባህ ዙሪያ የሚመለኩ 360 ጣዖታትን ነበሩ፤ ሁሉንም ሰባብረዋል፤ ያስቀሩት አንድም ጣዖት የለም፦
376 views22:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-09 01:15:46
327 views22:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-04 21:44:33
የተደበቀው የስቅለት ጉዳይ! ክፍል 1
| ኡስታዝ ወሒድ ዑመር | ጥሪያችን

መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
‐‐‐
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
324 views18:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-03 01:23:01 መንፈስ "ፈጣሪ" ነውን?

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

40፥62 ይሃችሁ ጌታችሁ አላህ ነው፤ የነገሩ ሁሉ ፈጣሪ ነው፤ ከእርሱ ሌላ አምላክ የለም፤ ታዲያ ከእምነት ወዴት ትመለሳላችሁ?፡፡ ذَٰلِكُمُ اللَّهُ رَبُّكُمْ خَالِقُ كُلِّ شَيْءٍ لَّا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ ۖ فَأَنَّىٰ تُؤْفَكُونَ

በባይብል ሁሉንም ሰው የፈጠረ አንድ አምላክ አለ፥ ይህ አንድ አምላክ የሁሉ ነገር ፈጣሪ ነው፦
ሚልክያስ 2፥10 ለሁላችን አንድ አባት ያለን አይደለምን? አንድ አምላክስ የፈጠረን አይደለምን?
ኤርምያስ 51፥19 የያዕቆብ እድል ፈንታ እንደ እነዚህ አይደለም፥ እርሱ የሁሉ ፈጣሪ ነውና፤ እስራኤልም የርስቱ ነገድ ነው፥ ስሙም የሠራዊት ጌታ "ያህዌህ" ነው።

ያህዌህ አምላክ ሰውን ከምድር አፈር አበጀው፥ ይህ አንድ አምላክ ሰው ያበጀውም በእጆቹ ነው፦
ዘፍጥረት 2፥7 ያህዌህ አምላክም ሰውን ከምድር አፈር አበጀው።
መዝሙር 119፥73 እጆችህ ሠሩኝ አበጃጁኝም።

የያህዌህ እጆች ልክ እንደ ያህዌህ እራሳቸውን የቻሉ ማንነት ሳይሆኑ የምንነቱ መገለጫ ባሕርያት ናቸው፥ እነርሱ "ሠሩ" ስለተባሉ በስም መደብ "ሠሪዎች" እንደማይባሉ ሁሉ በተመሳሳይ ያህዌህ በአፍንጫውም የሕይወት እስትንፋስ እፍ ስላለበት እና በአፉ እስትንፋስ ስለፈጠረ የአፉ እስትንፋስ "ፈጣሪ" አይደለችም፦
ዘፍጥረት 2፥7 በአፍንጫውም የሕይወት እስትንፋስን እፍ አለበት።
ኢዮብ 33፥4 የያህዌህ መንፈስ ፈጠረችኝ፥ የሁሉን ቻዩ እስትንፋስ ሕይወት ሰጠችኝ። רֽוּחַ־אֵ֥ל עָשָׂ֑תְנִי וְנִשְׁמַ֖ת שַׁדַּ֣י תְּחַיֵּֽנִי׃

በሴት አንቀጽ "ዓሳቴኒይ" עָשָׂתְנִי ተብሎ የተቀመጠው የግሥ መደብ "ፈጠረችኝ" ማለት ነው፥ "የያህዌህ መንፈስ" ማለት "የሁሉን ቻዩ እስትንፋስ" ማለት ነው፥ እስትንፋሱ "ፈጠረች" ስለተባለ "ፈጣሪ" ከተባለች እጆቹ "ሠሩ" ስለተባሉ በስም መደብ "ፈጣሪዎች" ይባሉ ነበር። ቅሉ ግን እስትንፋስ ሆነ እጆቹ መፍጠሪያ እንጂ ፈጣሪዎች አይደሉም። ሌላ ናሙና እንመልከት፦
መዝሙር 8፥3 የጣቶችህን ሥራ ሰማዮችን ባየሁ ጊዜ።
መዝሙር 102፥25 ሰማያትም የእጆችህ ሥራ ናቸው። וּֽמַעֲשֵׂ֖ה יָדֶ֣יךָ שָׁמָֽיִם׃

የያህዌህ ጣቶች እና እጆች ሰማያትን ስለሠሩ በስም መደብ "ፈጣሪዎች" እንደማይባሉ ሁሉ በተመሳሳይ የያህዌህ መንፈስ ስለፈጠረች "ፈጣሪ" አትባልም። ተጨማሪ ናሙና እንመልከት፦
ኢሳይያስ 48:13 እጄም ምድርን መሥርታለች ቀኜም ሰማያትን ዘርግታለች።

የያህዌህ እጅ ምድርን ስለመሠረት እና ቀኙ ሰማያትን ስለዘረጋች በስም መደብ "መሥራቾች" "ዘርጊዎች" ወይም "ፈጣሪዎች" እንደማይባሉ ሁሉ በተመሳሳይ የያህዌህ መንፈስ ስለፈጠረች "ፈጣሪ" አትባልም።
እንግዲህ የያህዌህ መንፈስ ልክ እንደ ያህዌህ ማንነት ካለው የያህዌህ እጆች፣ ጣቶች፣ ቀኙ ብዙ ማንነቶች ሊሆኑ ነው፥ ያ ደግሞ ሥላሴን ከሦስት በላይ ሊያደርግ ነው። ነገር ግን በግሥ መደብ የሚመጣ ድርጊት ባለቤቱ ያህዌህ ስለሆነ "ሠሪ" "ፈጣሪ" "መሥራች" "ዘርጊ" እርሱ ብቻ ነው እንጂ የእርሱን ባሕርይን እየሸነሸንን ማንነት አበጅተን ፈጣሪ አናረጋቸው። ለምሳሌ፦
ኢሳይያስ 1፥20 እምቢ ብትሉ ግን ብታምፁም፥ ሰይፍ ይበላችኋል፤ የያህዌህ አፍ ይህን ተናግሮአልና።

"የያህዌህ አፍ ይህን ተናግሮአል" የሚለው ይሰመርበት! የያህዌህ አፍ ስለተናገረ "ተናጋሪ" የሚለው የስም መደብ የምንጠቀመው ለያህዌህ እንጂ ለአፉ አይደለም፥ ሩቅ ሳንሄድ አንድ ሰው በአንደበቱ ስለሚያስተምር አስተማሪ ይባላል እንጂ አፉ "አስተማሪ" አይደለም፦
መዝሙር 37፥30 የጻድቅ አፍ ጥበብን ያስተምራል፥ አንደበቱም ፍርድን ይናገራል።

አፍ ስላስተማረ "አስተማሪ" እንደማይባል እና አንደበት ስለተናገረ "ተናጋሪ" እንደማይባል ሁሉ እስትንፋስም ስለፈጠረች "ፈጣሪ" በፍጹም አትባልም፥ የሰው አፍ እና አንደበት እንደ ሰው ራሳቸውን የቻሉ ማንነቶች እንዳልሆኑ ሁሉ እስትንፋስም እንደ አምላክ ራሷን የቻለች ማንነት አይደለችም። የመጨረሻ ናሙና እንመልከት፦
ሉቃስ 11፥49 ስለዚህ ደግሞ የአምላክ ጥበብ እንዲህ አለች፦ ወደ እነርሱ ነቢያትንና ሐዋርያትን እልካለሁ፥ ከእነርሱም ይገድላሉ ያሳድዱማል።
ሲራክ 24፥3 እኔ(ጥበብ) ከልዑል "አፍ ወጣሁ" ምድርንም እንደ ጉም ሽፈንኋት።

ከአምላክ አፍ የምትወጣ የአምላክ ጥበብ ስለምትልክ "ላኪ" እንደማትባል ሁሉ እስትንፋስም ስለፈጠረች "ፈጣሪ" በፍጹም አትባልም። ዕውቀት እና ማስተዋል ከአምላክ አፍ የሚወጡ ባሕርያት ናቸው፥ በማስተዋሉ ሰማያትን አጸና እንዲሁ በእውቀቱ ቀላያት ተቀደዱ፦
ምሳሌ 2፥6 "ከ-"አፉም" ዕውቀት እና ማስተዋል "ይወጣሉ"።
ምሳሌ 3፥19 ያህዌህ በጥበብ ምድርን መሠረተ፥ በማስተዋልም ሰማያትን አጸና። በእውቀቱ ቀላያት ተቀደዱ፥ ደመናትም ጠልን ያንጠባጥባሉ።
ኤርምያስ 10፥12 ምድርን በኃይሉ የፈጠረ፥ ዓለሙን በጥበቡ የመሠረተ ሰማያትንም በማስተዋሉ የዘረጋ እርሱ ነው።

እንግዲህ እስትንፋስ ማንነት ከሆነች እጆች፣ ጣቶች፣ ቀኝ፣ አፍ፣ ጥበብ፣ ማስተዋል፣ እውቀት፣ ኃይል ስንት ማንነቶች አሉ? መፍጠሪያውን ፈጣሪ ካረግን ስንት ፈጣሪዎች አሉ? ስለዚህ እንደባይብሉ የአምላክ እስትንፋስ ልክ እንደ ዕውቀት፣ ማስተዋል፣ ጥበብ ከአፉ የምትወጣ ባሕርይ ናት፦
መዝሙር 33፥6 ሠራዊታቸውም ሁሉ "በ-"አፉ እስትንፋስ" ጸኑ። וּבְר֥וּחַ פִּ֝֗יו כָּל־צְבָאָֽם׃

እዚህ አንቀጽ ላይ "እስትንፋስ" ተብሎ የተቀመጠው ቃል "ሩሓህ" רוּחַ ሲሆን "መንፈስ" ማለት ነው፥ መንፈስ በተለያየ ጊዜ ለተለያየ ሥራ ከአፉ ወይም ከአፍንጫው የሚወጣ እስትንፋስ ከሆነ እራሱን የቻለ ማንነት እና ፈጣሪ በፍጹም አይደለም፦
ዘጸአት 15፥8 በአፍንጫህ እስትንፋስ ውኆች ተከመሩ። וּבְר֤וּחַ אַפֶּ֙יךָ֙ נֶ֣עֶרְמוּ מַ֔יִם

እዚህ አንቀጽ ላይ "እስትንፋስ" ተብሎ የተቀመጠው ቃል በተመሳሳይ "ሩሓህ" רוּחַ ነው፥ አፍ እና አፍንጫ ሁለት የተለያዩ ከሆኑ ከሁለቱ የሚወጡትን እስትንፋሶች እየሸነሸንን አካላት የምንሰጥ እና "ፈጣሪዎች" የምንል ከሆነ ሥንት አካሎች እና ፈጣሪዎች ሊኖሩ ነው?
ወደ ቁርኣን ስንመጣ አምላካችን አሏህ አንድ ማንነት እና ምንነት ሲሆን የነገሩ ሁሉ ፈጣሪ ነው፥ ከእርሱ ሌላ አምላክ የለም፦
40፥62 ይሃችሁ ጌታችሁ አላህ ነው፤ የነገሩ ሁሉ ፈጣሪ ነው፥ ከእርሱ ሌላ አምላክ የለም። ታዲያ ከእምነት ወዴት ትመለሳላችሁ?፡፡ ذَٰلِكُمُ اللَّهُ رَبُّكُمْ خَالِقُ كُلِّ شَيْءٍ لَّا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ ۖ فَأَنَّىٰ تُؤْفَكُونَ

ክርስቲያኖች ሆይ! እንዲህ ተወሳስቦ ከሚያወዛግብ ትምህርት ወጥታችሁ አንዱን አምላክ አሏህን እንድታመልኩ ጥሪያችን ነው። አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ

መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
‐‐‐
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen


ወሠላሙ ዐለይኩም
243 viewsedited  22:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-03 01:22:58
237 views22:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-31 23:47:26 ቁርኣን ለኦሮሞ በኦሮምኛ፣ ለትግሬ በትግርኛ፣ ለዐማራ በዐማርኛ ስላልወረደ እና በዐረቢኛ ስለወረደ "ለዐረቦች ብቻ ወረደ" ካልን በዓለም ላይ 7,117 ቋንቋዎች ስላሉ ለ 7,117 ቋንቋዎች ተናጋሪዎች በራሳቸው 7,117 ቁርኣኖች እና ነቢያት መላክ ነበረባቸውን? ይህ ሕፀፃዊ አስተሳሰብ ነው፥ አምላካችን አሏህ ለሁሉም የሰው ልጆች አንድ ሰው መርጦ ነቢያችንን"ﷺ" ነቢይ እንዳደረገ ሁሉ እሳቸው የመጡበትን ቋንቋ ዐረብኛን መርጦ መልእክቱን አውርዶበታል። አሏህ ቁርኣንን በነቢያች"ﷺ" ቋንቋ ያገራው የመልእክቱ ጥልቀት እና ምጥቀት እንድንገነዘብ ብቻ ነው፦
3፥74 በችሮታው (በነቢይነት) የሚሻውን ይመርጣል፡፡ አላህም የታላቅ ችሮታ ባለቤት ነው፡፡ يَخْتَصُّ بِرَحْمَتِهِ مَن يَشَاءُ ۗ وَاللَّهُ ذُو الْفَضْلِ الْعَظِيمِ
44፥58 ቁርኣንን በቋንቋህም ያገራነው ይገነዘቡ ዘንድ ብቻ ነው፡፡ فَإِنَّمَا يَسَّرْنَاهُ بِلِسَانِكَ لَعَلَّهُمْ يَتَذَكَّرُونَ
42፥7 እንደዚሁም የከተሞችን እናት እና በዙሪያዋ ያሉትን ሰዎች ልታስጠነቅቅ እና የመሰብሰቢያውን ቀን በእርሱ ጥርጣሬ የሌለበት ሲኾን ልታስጠነቅቅ ዐረብኛ የኾነን ቁርኣን ወደ አንተ አወረድን፡፡ وَكَذَٰلِكَ أَوْحَيْنَا إِلَيْكَ قُرْآنًا عَرَبِيًّا لِّتُنذِرَ أُمَّ الْقُرَىٰ وَمَنْ حَوْلَهَا وَتُنذِرَ يَوْمَ الْجَمْعِ لَا رَيْبَ فِيهِ

"መን ሐውለ-ሃ" مَنْ حَوْلَهَا ማለት "በዙሪያዋ ያሉት ሰዎች" ማለት ሲሆን ቁርኣን ማስጠንቀቂያ ሆኖ የወረደው የከተሞችን እናት የሆነችውን መካን ብቻ ሳይሆን በዙሪያ ያሉትን መላው ሰዎችን ሁሉ ነው፥ "ዐረብኛ የኾነን ቁርኣን ወደ አንተ አወረድን" ማለቱ ደግሞ ቁርኣን ለመላው የሰው ዘር ሁሉ በዐረብኛ መውረዱን ያሳያል። አምላካችን አሏህ የቁርኣንን ጥልቀት እና ምጥቀት የምንገነዘብ ያድርገን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ

መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
‐‐‐
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen


ወሠላሙ ዐለይኩም
424 views20:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-31 23:47:25 የቁርኣን ቋንቋ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

26፥195 ግልጽ በኾነ ዐረብኛ ቋንቋ አወረደው፡፡ بِلِسَانٍ عَرَبِيٍّ مُّبِينٍ

የቋንቋዎቻችን መለያየት ከአስደናቂ የአሏህ ተአምራት ነው፥ አምላካችን አሏህ መልእክተኞች ሲልክ በወቅቱ የተወለዱበት ማኅበረሰብ ሊግባቡበት በሚችል ቋንቋ ነው፦
30፥22 ሰማያትንና ምድርንም መፍጠሩ፤ የቋንቋዎቻችሁ እና የመልኮቻችሁም መለያየት ከአስደናቂ ተአምራቶቹ ነው፡፡ وَمِنْ ءَايَٰتِهِۦ خَلْقُ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلْأَرْضِ وَٱخْتِلَٰفُ أَلْسِنَتِكُمْ وَأَلْوَٰنِكُمْ
14፥4 ከመልክተኛ ማንኛውንም ለእነርሱ ያብራራላቸው ዘንድ በሕዝቦቹ ቋንቋ እንጂ በሌላ አልላክንም፡፡ ﻭَﻣَﺂ ﺃَﺭْﺳَﻠْﻨَﺎ ﻣِﻦ ﺭَّﺳُﻮﻝٍ ﺇِﻟَّﺎ ﺑِﻠِﺴَﺎﻥِ ﻗَﻮْﻣِﻪِۦ ﻟِﻴُﺒَﻴِّﻦَ ﻟَﻬُﻢْ ۖ ﻓَﻴُﻀِﻞُّ ﭐﻟﻠَّﻪُ ﻣَﻦ ﻳَﺸَﺂﺀُ ﻭَﻳَﻬْﺪِﻯ ﻣَﻦ ﻳَﺸَﺂﺀُ ۚ ﻭَﻫُﻮَ ﭐﻟْﻌَﺰِﻳﺰُ ﭐﻟْﺤَﻜِﻴﻢُ

"ቀውም" قَوْم ማለት "ህዝብ" ማለት ሲሆን በአንድ አካባቢ ተመሳሳይ ባህል፣ ቋንቋ፣ አኗኗር፣ ታሪክ፣ መንግሥት እና ቦታ ያለው ማኅበረሰብን ያመለክታል፥ ለምሳሌ፦ ሙሣ ነቢይ ሆኖ በተነሳበት ዘመን አሏህ ሙሣን ወደ ሕዝቦቹ "በተአምራት" እንደላከው እና እነዚያም ሕዝቦች ፈርዖን እና ሹማምንቶቹ የሚጠቀልል መሆኑን ለማመልከት ወደ ፈሮዖንና ወደ ሹማምንቶቹ በእርግጥ ላክን” በማለት ይናገራል፦
14፥5 ሙሳንም፦ "ሕዝቦችህን" ከጨለማዎች ወደ ብርሃን አውጣ! የአላህንም ቀኖች አስገንዝባቸው" በማለት "በተአምራታችን" በእርግጥ ላክነው። وَلَقَدْ أَرْسَلْنَا مُوسَىٰ بِـَٔايَٰتِنَآ أَنْ أَخْرِجْ قَوْمَكَ مِنَ ٱلظُّلُمَٰتِ إِلَى ٱلنُّورِ وَذَكِّرْهُم بِأَيَّىٰمِ ٱللَّهِ
43፥46 ሙሳንም "በተአምራታችን" ወደ ፈርዖን እና ወደ ሹማምንቶቹ በእርግጥ ላክን። እኔ የአለማት ጌታ መልክተኛ ነኝ አላቸውም። وَلَقَدْ أَرْسَلْنَا مُوسَىٰ بِـَٔايَٰتِنَآ إِلَىٰ فِرْعَوْنَ وَمَلَإِي۟هِۦ فَقَالَ إِنِّى رَسُولُ رَبِّ ٱلْعَٰلَمِينَ

እዚህ ድረስ ከተግባባን ዘንድ አምላካችን አሏህ ቁርኣንን ግልጽ በኾነ ዐረብኛ ቋንቋ ወደ ተወዳጁ ነቢያችን"ﷺ" አውርዶታል፦
26፥195 ግልጽ በኾነ ዐረብኛ ቋንቋ አወረደው፡፡ بِلِسَانٍ عَرَبِيٍّ مُّبِينٍ
13፥37 እንደዚሁ በዐረብኛ የተነገረ ፍትሕ ሲኾን አወረድነው፡፡ وَكَذَٰلِكَ أَنزَلْنَاهُ حُكْمًا عَرَبِيًّا

"ሑክም" حُكْم ማለት "ሕግ" "ፍርድ" "ፍትሕ" ማለት ሲሆን "አሕካም" أَحْكَام‎ ደግሞ "ሕግጋት" ማለት ነው፥ አምስቱ አሕካም ፈርድ፣ ሙሥተሐብ፣ ሙባሕ፣ መክሩህ እና ሐራም ምን እንደሆኑ አሏህ ግልጽ በኾነ ዐረብኛ ቋንቋ አውርዷል። የቁርኣንን ሰዋስው መሠረት እና ውቅር እንዲሁ ዋልታና ማገር እንድንገነዘብ አሏህ ቁርኣንን ዐረብኛ አርድርጎ አውርዶታል፦
43፥3 እኛ ትገነዘቡ ዘንድ ዐረብኛ ቁርኣን አደረግነው፡፡ إِنَّا جَعَلْنَاهُ قُرْآنًا عَرَبِيًّا لَّعَلَّكُمْ تَعْقِلُونَ
12፥2 እኛ ትገነዘቡ ዘንድ ዐረብኛ ቁርኣን ሲሆን በእርግጥ አወረድነው፡፡ إِنَّا أَنزَلْنَاهُ قُرْآنًا عَرَبِيًّا لَّعَلَّكُمْ تَعْقِلُونَ

"ትገነዘቡ ዘንድ" ለሚለው የገባው ቃል "ለዐለኩም ተዕቂሉን" لَّعَلَّكُمْ تَعْقِلُون ሲሆን ሥርወ ቃሉ "ዐቀለ" عَقَلَ ማለትም "ተገነዘበ" "ተረዳ" "ዐወቀ" ነው፥ ለመገንዘብ፣ ለመረዳት፣ ለማወቅ የምታስተነትንበት እእምሮ እራሱ "ዐቅል" عَقْل ይባላል። የቁርኣን የአቀራሩ ስልት የሆኑት ሐረካት፣ ተንዊን፣ መድ፣ ስኩን፣ ኢዝሃር፣ ኢድጋም፣ ኢቅላብ፣ ኢኽፋእ፣ ተፍኺም፣ ተርቂቅ፣ ተሽዲድ እራሱን የቻለ አምሳያ የሌለው የቁርኣኑ ተአምር ነው፦
52፥34 እውነተኞችም ቢኾኑ መሰሉ የኾነን ንግግር ያምጡ፡፡ فَلْيَأْتُوا بِحَدِيثٍ مِّثْلِهِ إِن كَانُوا صَادِقِينَ

ቁርኣኑ እራሱ ችሎ በተጅዊድ ሐረካት፣ ተንዊን፣ መድ፣ ስኩን፣ ኢዝሃር፣ ኢድጋም፣ ኢቅላብ፣ ኢኽፋእ፣ ተፍኺም፣ ተርቂቅ፣ ተሽዲድ አለው፥ የቁርኣን መሰሉ የኾነን ንግግርን ማንም ማምጣት አይችልም። አምላካችን አሏህ የቁርኣንን ሑሩፉል ሙፍረዳት በማርባት እና በማባዛት ሶርፍ፣ የቁርኣንን ሑሩፉል ሙፍረዳት በማብራራት ሉጋህ፣ የቁርኣንን ሑሩፉል ሙረከባት በዓረፍተ ነገር በማዋቀር ነሕው፣ የቁርኣንን ሑሩፉል ሙረከባት የዓረፍተ ነገሩን መልእክት በመግለጽ በላጋህ በማድረግ መዛባት በሌለበት ዐረብኛ አብራርቶታል፦
39፥28 መዛባት የሌለበት ዐረብኛ ቁርኣን ሲኾን አብራራነው፡፡ ሊጠነቀቁ ይከጀላልና፡፡ قُرْآنًا عَرَبِيًّا غَيْرَ ذِي عِوَجٍ لَّعَلَّهُمْ يَتَّقُونَ
41፥3 አንቀጾቹ የተብራሩ የኾነ መጽሐፍ ነው፡፡ ዐረብኛ ቁርኣን ሲኾን ለሚያውቁ ሕዝቦች የተብራራ ነው፡፡ كِتَابٌ فُصِّلَتْ آيَاتُهُ قُرْآنًا عَرَبِيًّا لِّقَوْمٍ يَعْلَمُونَ
በዐማርኛ፣ በእንግሊዝኛ፣ በፈረንሳይኛ ወዘተ... የምናነባቸው የቁርኣን ትርጉም እንጂ ቁርኣን አይደሉም፥ ትርጉም የመልእክቱ አሳብ የምንረዳበት እንጂ የቁርኣኑን ምጥቀት እና ጥልቀት ያለው አሏህ እራሱ ባወደረበት በግልጹ እና መዛባት በሌለበት ዐረብኛ ቁርኣን ነው። ይህ ከላሙል ዐረቢይ የሆነው ቁርኣን የወረደው ለመላው የሰው ልጆች ሁሉ ነው፦
6፥90 «በእርሱ በቁርአን ላይ ምንም ዋጋ አልጠይቃችሁም፡፡ እርሱ ለዓለማት ግሣጼ እንጅ ሌላ አይደለም» በላቸው፡፡ قُل لَّا أَسْأَلُكُمْ عَلَيْهِ أَجْرًا ۖ إِنْ هُوَ إِلَّا ذِكْرَىٰ لِلْعَالَمِينَ

ቁርኣን ለዓለማት ግሣጼ እንደወረደ በተጨማሪ 68፥52 38፥87 12፥104 81፥27 ላይ ተመልከት!
"ዓለማት" የሚለው ቃል በቁርኣን ሰፊ እና ጠባብ ትርጉም አለው፥ በሰፊ ትርጉሙ "የዐለማቱ ጌታ" በሚል ከመጣ "አጽናፈ ዓለማትን" ያመለክታል፦
7፥54 የዓለማት ጌታ አላህ ክብሩ ላቀ፡፡ تَبَارَكَ اللَّهُ رَبُّ الْعَالَمِينَ

"ዓለማት" በጠባብ ትርጉሙ ከመጣ "መላውን የሰው ልጆች ሁሉ" ያመለክታል፦
29፥10 አላህ "በዓለማት ልቦች" ውስጥ ያለውን ሁሉ ዐዋቂ አይደለምን? أَوَلَيْسَ اللَّهُ بِأَعْلَمَ بِمَا فِي صُدُورِ الْعَالَمِينَ

በተጨማሪ "ዓለማት" በጠባብ ትርጉሙ "መላውን የሰው ልጆች ሁሉ" እንደሚያመለክት 2፥47 3፥33 3፥42 21፥91 29፥15 37፥79 3፥96 21፥107 7፥80 26፥165 ላይ ተመልከት!
ስለዚህ አምላካችን አሏህ ለመላውን የሰው ልጆች ሁሉ መገሰጫ ይሆን ዘንድ ቁርኣንን ግልጽ በሆነ ዐረብኛ አውርዶታል።
395 views20:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ