Get Mystery Box with random crypto!

ካሊድ ታረቀኝ(ye umi) official

የቴሌግራም ቻናል አርማ kalidoyeumi — ካሊድ ታረቀኝ(ye umi) official
የቴሌግራም ቻናል አርማ kalidoyeumi — ካሊድ ታረቀኝ(ye umi) official
የሰርጥ አድራሻ: @kalidoyeumi
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 318
የሰርጥ መግለጫ

ሀሳብ አስተያየት መስጫ 👉 @kaludi_bot
👉 @kalidoyeumi
👉 https://www.instagram.com/
👉 https://www.facebook.com/profile.php?id=100051553322923
Another chanel 👉 @zburafilms

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-08-23 21:09:41 #አትፍረድ

ፀሀፊ ካሊድ ታረቀኝ (ye umi)

Part ❶❽

እሽ ችግር የለውም ነገ ስራ ትጀምራለህ እንዴ?
አይ ነገ እንኳን አልገባም እኔ ምልሽ ግን የወንድምሽን ስሙን እኮ አላውቀውም።
ስል ወደ ዋናው ነጥብ ተጠጋሁ።
ሲጀመር በደንብ መቼ ተዋወቃችሁ እና ነው ለማንኛውም ፋሪስ ይባላል ደግሞ እርሳውና ዋ!

ከተጋደምኩበት አልጋ በፍጥነት ከወገቤ ቀና ስል ተቀመጥኩ
እየሆነ ያለው ነገር ህልም መስሎ እየታየኝ ነው እይሆንም አይሆንም ፋሪስ የሀኒም ወንድም በፍጹም አይሆንም ስል ከእራሴ ጋር መሟገት ጀመርኩ

እ የት ሄደክ
ተኛህ እንዴ
እንቅልፋም በል ደህና እደር።
በድንጋጤ ዝምታን በገባሁ ሰአት ከ ሀኒም የተላኩ ቴክስቶች ናቸው።

በጠዋት ተነስቼ ለድርጅቱ የሚሆኑትን አዳዲስ እቃዎች የሚያስረክበንና የሚጠግንልን አካል ሙሉ ስራውን ስለጨረሰ በውላችን መሰረት ነገ ቀሪውን ክፍያ መፈፀም እንዳለብን በስልክ አወራሁኝ።

ዛሬም ግን ስራ የመግባት ጉጉቴ ማታ በተፈጠረው ነገር ገደል ገብቷል። አሁን ምን ተሻለ ሀኒምን አፍቅሬያታለሁ ወንድሞ እህቴን እንዳጣ ትልቁ ምክንያት እሱና እሱ ብቻ እንደሆነ አረጋግጫለሁ።

ስልኬ መጥራት ጀመረች ሰአዳ ናት።

ሄለው አብዲዬ ሰላም አለይኩም እንዴት አደርክ ተኝታ እያወራችኝ እንደሆነ በደንብ ያስታውቅባታል።
ወአለይኩምሰላም ሰአዲ እንዴት አደርሽ
አልሃምዱሊላህ
ተኝተሽ ነው?
እ ማታ እኮ እንቅልፍ እንዲች ባይኔ ሳይዞር ፈጅር ከሰገድኩ ቡኋላ ትንሽ ተኛው።
ምነው በሰላም
አብዲዬ ይቅርታ አድርግልኝና እኔ ትላንትና ያየውት ነገር እውነተኛ ፋሪስ መሆኑን ውስጤ አምኖ ተቀብሏል።

እንባዬን እያወረድኩ እንደመሳቅ አልኩና ሰአዲዬ ልጅቷን እኮ ጠይቄያት ነበር እና ሌላ ስም ነው የነገረችኝ ስል ዋሸኋት
እየተዋጠላትም ባይሆን እረ እ.. እ.. ምን አልባት ይሆናል ግን እኮ አብዲዬ አላህ አጋልጦት ፋሪስ የተባለውን ክፋ በአይንህ ብታየው ትላንትና ያየነው እራሱ ነው ትል ነበር።
አይ አንዳዴ እንደዚህ አይነት ነገር ያጋጥማል።
ይሆናል። አለች አሁንም ነገሩ እንዳልተዋጠላት በማሳወቅ።
በቃ በይ እረፍት አድርጊ አላህ ያለ ቀን እናገኘዋለን።
እሱማ አይቀርም በል መልካም ቀን። ብላ ተሰናበተችኝ

ከሰአት ቡሃላ ወደ ጀሞ ተመለስኩ መኪናዬን ከነ ሀኒም ሱቅ ፊትለፊት እንደሁሌውም አቁሜ ሀኒም ጋር ጎራ አልኩ ከወንድሟ ጋር እየተጨዋወቱ ከት እያለ ይስቃል ሰላም አለይኩም ስል ተቀላቀልኳቸው ሀኒም በደስታ ተቀበለችኝ ወንድሟ ሰካራም ስለሆንኩ ብዙም ቦታ ሊሰጠኝ አልፈለገም። ወሬያቸውን ቀጥለው ይሳሳቁ ጀመር ሀኒም ጨዋታውን እንድቀላቀል የማትፈነቅለው ድንጋይ የለም ወንድሟ እህቴን ነጥቆኝ እንዲህ ሊስቅ አይገባም ስል ደመደምኩ። ከቆምኩበት እግሬን አንቀሳቀስኩ።
እንዴ አትጫወትም እንዴ አለች ሀኒም። ቆይ ተመልሼ እመጣለሁ እቤትም አልጋባሁም ብዬ ወጣሁ ብፍጥነት ወጣሁ።

እቤት እንደገባሁ ጥቂት ቆይቼ በእጄ መዳፎች ላይ ካስቀመጥኩት ስልክ፡ እስክሪኑ ላይ አይኖቼን በመጣል ምንም ከማይናገረውና ከማይጋገረው የናዲ ፎቶ ጋር አወራ ጀመር።

ናዲ ላንቺ ስል የማፈቅረውን ሰው ልበድል ነው እኔ እንዳለቀስኩት እኔ ሰካራም እንደተባልኩት ፋሪስም ይባላል። እስክሪኑ ላይ ከአይኔ የሚወርድ አንድ ዘለላ እንባ ጠብ አለ፡


Part ❶❾ ይቀጥላል !

any comments
@kaludi_bot


@kalidoyeumi
join telegram
3.2K viewsĸãlidö Ye ũmi , 18:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-15 12:13:41 የተለያዩ ሳይኮሎጃዊ ምክሮችን ከፈለጉ ቻናላችንን JOIN ይበሉ


ቆይ ግን መለወጥ አትፈልጉም??? እና መለወጥን ከፈለጋችሁ ቻናላችንን JOIN በሉ!!
2 viewsILahi, 09:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-15 10:39:06 ሱረቱል ካህፍ

ቃሪዕ ኻሊድ አል-ጀሊል

#ሸጋ_ጁመዓ
@kalidoyeumi
187 viewsĸãlidö Ye ũmi , 07:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-14 21:22:58 #በ ጁመአው ለይል ሹክ ልበላችሁ

አዘጋጅና ፀሀፊ ፦ ካሊድ (kalido ye umi)

የዋሻው እግረኛ እንዴት ነው ሷሂቡ

ቁረይሾች ነብዩን ﷺ ለመግደል የመጨረሻ በዳይ ውሳኔ ላይ በደረሱበት ወቅት ጅብሪል የቁረይሾችን ሴራ በወህይ አሳወቃቸው። አላህ እንዲሰደዱ መፍቀዱንም አበሰራቸው።

የአላህ መልእክተኛ ﷺ በ14ኛው ዓመተ ነብይነት በወርሃ ሶፈር 27ኛው ሌሊት ማለትም ሴፕቴምበር 12/13_622 ቤታቸውን ለቀው ወደ ባልንጀራቸው አቡበክር ቤት ሄዱ። አቡበከር ከርሳቸው ዘንድ ለጉዞ ጓደኝነት ከማንም በላይ ታማኝ፣ ገንዘባቸውንም ለመሰዋት ዝግጁ ነበሩ። ከ አቡበክር ቤት በጓዳው በኩል በመውጣት ጎህ ሳይቀድ በፊት መካን በፍጥነት ለቀቁ።

ቁረይሾች ለፍለጋ እንደሚሰማሩና መጀመሪያ የሚያስቡት ወደሰሜን አቅጣጫ የተዘረጋውን የመዲና ዋነኛ መንገድ መሆኑን ነቢዩ ﷺ በመረዳታቸው በስተደቡብ በኩል ወደ የመን የሚያደርሰውን መንገድ ይዘው ወደ ተቃራኒ አቅጣጫ ተጓዙ።በዚህ መንገድ 5 ማይሎች ያህል ተጉዘው "ሰውር" ከተባለው ተራራ ደረሱ። ትልቅና መንገዱም አስፈሪ፣ ድንጋያማና አስቸጋሪ ነው። በጉዞው ምክንያት የመልእክተኛው እግር ቆሰለ። ቁስላቸውን ለመደበቅ በእግራቸው ጫፍ ይጓዙ እንደነበር ይነገራል።

ከጋራው ሲደርሱ አቡበክር ተሸከሟቸው። በከፍተኛ ድካምም ከተራራው ጫፍ ወዳለ ዋሻ አደረሷቸው። የዚህ ዋሻ ስም በታሪክ ጸሐፍት ዘንድ "ጋር ሰውር" (ሰውር ዋሻ) በመባል ይታወቃል።

ከዋሻው አጠገብ ደርሰው ሊገቡ ሲሉ አቡበክር፦ "እኔ ከመግባቴ በፊት አይገቡም። አንዳች መጥፎ ነገር ቢኖር እንኳ እርስዎን ሳይሆን እኔን ይጉዳኝ።"በማለት ወደ ውስጥ ዘለቁ።

ከጎኑ ሦስት ሽንቁሮች አዩ። ሽርጣቸውን በመቅደድ አንዱን ደፈኑት። ሁለቱን በእግሮቻቸው ደፈኗቸውና መልእክተኛውን "ይግቡ" አሏቸው። "የአላህ መልእክተኛ ﷺ ገቡና የአቡበክርን ጭን ተንተርሰው ጋደም አሉ። ወዲያውም እንቅልፍ አሸለባቸው። በዚህ መሀከል አቡበክርን እግራቸውን አንዳች ነገር ነደፋቸው። ነብዩ ﷺ ከእንቅልፍ እንዳይነቁ በመስጋት አልተንቀሳቀሱም ነበር። በስተመጨረሻም ከአይናቸው የሚወርደው እንባ ከነቢዩ ﷺ ፊት ላይ ሊያርፍ ቻለ። ነቢዩም፦ እንባው ቢያገኛቸው "አቡበክር ሆይ ምን አገኘህ?" በማለት ጠየቋቸው። "አንዳች ነገር ነደፈኝ፣ ወላጆቼ ለርስዎ መስዋእት ይሁኑ" አሉ። የአላህ መልእክተኛ ﷺ ከተነደፉበት ቦታ ላይ ተፉላቸው። ሕመሙ ወዲያውኑ ለቀቃቸው።

በዚህ ዋሻ ውስጥ ሦስት ሌሊቶችን ፣ማለትም ጁመዓ፣ ቅዳሜና እሁድ ሌሊት ፣አሳለፉ። አብደላህ ቢን አቡበክር ከነርሱ ጋር ያድር ነበር። አኢሻ እንዳሉት አብደላህ ብልህ ወጣት ነበር። ከነርሱ ጋር አድሮ ጎህ ከመቅደዱ በፊት ወደ መካ በመመለስ እዚያው ያደረ መስሎ ይተኛል። መካውያን የሚነጋገሯቸውን ጉዳዮች ሁሉ ይዞም መሸትሸት ሲል ወደነርሱ በመሄድ ያደርስላቸዋል። የአቡበክር አገልጋይ ዓሚር ቢን ፈሒራህ የሚታለቡ ፍየሎችን ምሽት ላይ ይወስድላቸዋል። እነርሱም በቂ ወተት ያገኛሉ። ጎህ ከመቅደዱ በፊትም ይዟቸው ይመለሳል። በነዚህ በሦስት ሌሊቶቹ ያለማቋረጥ ይህን ያደርግ ነበር። አሚር ፍየሎችን ይዞ አብደላህ ቢን አቡበክር እስከ መካ ድረስ በመከተል ኮቴውን ያጠፉለት ነበር።

የአቡበክርና የነቢዩ መሰውር ያንገበገባቸው ቁረይሾች አስቸኳይ ስብሰባ በመቀመጥ ሁለቱን ለመያዝ የሚያስችላቸውን የትኛውንም መንገድ ለመጠቀም ወሰኑ። ወደ መካ የሚያደርሱ ጎዳናዎችን ሁሉ በጥብቅ የመሳሪያ ጥበቃ ስር አዋሉ። ሁለቱንም በሕይወት ወይም ገድሎ ወደ መካ ለሚያመጣ ማንኛውም ሰው ስለእያንዳንዳቸው መቶ ግመል ሽልማት ለመስጠት ቃል ገቡ። በዚህ ጊዜ ፈረሰኞች፣ እግረኞችና የኮቴ አዋቂዎች በፍለጋ ላይ ተሰማሩ። ጋራዎችን ፣ሸንተረሮችን ፣ሸለቆዎችንና ሜዳዎችን ሁሉ አሰሱ።ግና ድካማቸው ፍሬ አልያዘም። ያለ ውጤት ተመለሱ።

ነገር ግን አሳዳጆች ከዋሻው በር ላይ መድረስ ችለው ነበር። ግና አላህ ፈቃዱን ፈጻሚ ነው። ቡኻሪ አነስን በመጥቀስ እንደዘገቡት አቡበክር እንዲህ ብለዋል፦

ከነቢዩ ﷺ ጋር ከዋሻው ውስጥ ነበርኩ። ራሴን ቀና ሳደርግ የሰዎችን እግሮች አየሁ። "የአላህ መልእክተኛ ሆይ፡ ከመካከላቸው አንዱ ወደ ታች ቢመለከት ያየናል።" አልኳቸው። "አቡበክር ሆይ ፣አይዞህ ፣ አላህ አብሮን አለ።" አሉ።

በሌላ ዘገባም፦ "አቡበክር ሆይ ፡አላህ ሦስተኛ አብሯቸው ያለ ፡ሁለት ሰዎችን ምን ክፋት ያገኛቸዋል ብለህ ታስባለህ?" ብለዋል።

በዚህ ጊዜ አላህ ነቢዩን ﷺበተአምር አዳናቸው። አሳዳጆቻቸው ከርሳቸው ለመድረስ ጥቂት እርምጃዎች ሲቀሯቸው ትተዋቸው ተመለሱ።

ፍለጋው ጋብ ሲል በቁረይሾች የገነፈለው የብቀላ ስሜታቸው ሲሰክን የአላህ መልእክተኛ ﷺእና ባልንጀራቸው ወደ መዲና ለመጓዝ ተዘጋጁ።

{ፊዳከ ነፍሲ ኡሚ ወ አቢ ያረሱለላህ}

ሳምንት በአላህ ፍቃድ በሌላ ፅሁፍ እመለሳለሁ !

መልካም ኸሚስ (የጁመዓ ለይል) ውዶቼ

join @kalidoyeumi
858 viewsĸãlidö Ye ũmi , 18:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-14 21:21:54 #የአባቴ_ገዳይ

በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመረኮዘ !

ፀሀፊ፦ ካሊድ (kalido ye umi)

ከዳኒ ጋር የፍቅር ቃላትን በቴክስት እንቀባበላለን አመቺ ቦታ ላይም ስሆን ደውዬ ለት አወራዋለሁ እንደሚወደኝ ደጋግሞ ይገልፅልኛል እኔም እንደዛው ነኝ ምን እንዳስነካኝ ሊገባኝ ግን አልቻለም
ሁለተኛው ሴሚስተር.....

PART ❶❼

ከዳኒ ጋር የፍቅር ቃላትን በቴክስት እንቀባበላለን አመቺ ቦታ ላይም ስሆን ደውዬ ለት አወራዋለሁ እንደሚወደኝ ደጋግሞ ይገልፅልኛል እኔም እንደዛው ነኝ ምን እንዳስነካኝ ሊገባኝ ግን አልቻለም

ሁለተኛው ሴሚስተር ላይ ነን ትምሀርት ከጀመርን፣ ያውም በጣት የሚቆጠሩ ቀናቶች አልፈዋል፡ ሁሉም ነገር በዛውም ልክ አልፎአል ለቀጣይ ውጤቴን ወደ በፊቱ ቦታ ለመመለስ በደንብ አቅጃለሁ ለቀሪው ተማሪ የውጤት መግለጫ ወረቀት ተሰጥቷል ብዙም አልተጎዳሁም አስራ አንደኛ ቤት ውስጥ ነው ያለሁት ሃያት ከ ሰላሳ አምስት ተማሪ ሰላሳኛ ነው የወጣችው ግን ምንም ነገር አላስገረማትም ይሄ ነገሯ አስገርሞኛል ምክንያቱም እንዴት ቅር አልተሰኘችም እንደኔ ብዬ ነው

የገባው መምህር ጊዜውን ጠብቆ እንደወጣ ሰማሽ ሀሉዬ ቀጣይ ሳምንት ከለር ደይ እናከብራለን አለች እና ስል ጠየኳት አትመጪም አለችኝ ሀዩ እንደዚህ አይነት ፕሮግራም እንደማይመቸኝ ስንቴ ነገርኩሽ አልኳት እሷም የዋዛ አይደለችም ደካማ ጎኔን ተጠቅማ ዳኒም እኮ አለ አለች እየተቅለሰለሰች፡ ትንሽ ዝም ከተሰኘሁ ቡሃላ

እሺ እመጣለሁ አልኳት ግን ሀዩ እቤት እንደዛ ሆኜ ብገባ አክስቴ ታብድብኛለች ስል ዋነኛው ስጋቴን ነገርኳት እሺ እንደዚህ ብናደርግስ ስትል የመጣላትን ሀሳብ አጋራችኝ እኔ ተቀያሪ ልብስ ለራሴም ላንቺም ላምጣ፡ ከዛስ፡ ከዛማ በቃ እሱን ለብሰሽ ከኛ ጋር ፈታ ትያለሽ ዳኒም እኮ ከኛ ጋር ነው ከኛ ክፍል ተማሪዎች ውጪ ሌሎችም ይሳተፋሉ አብረሽን ብትሆኚ ደስ ስለሚለኝ ነው እኮ ሀሉ ከደበረሽ ይቅር አለች፡ እስኪ ላስብበትና እናወራለን ስል ገለፅኩላት

ዛሬ ከለር ደይ ይከበርበታል የተባለበት ቀን ነው ዳኒ እናዳልቀር አሳስቦኛል እኔም በሀያት ሀሳብ ተስማምቻለሁ

ከ አባቴ ጋር ትንሽ እረፈድ አድርጌ ከቤት ወጣሁ ግማሽ መንገድ አብሬው ከሄድኩ ቡሃላ ታክሲ አሲዤው ወደ ትምህርት ቤት ሄድኩኝ ክፍል ተገብቶ ነበር የደረስኩት፡ ወደ ውስጥ እንደገባሁ ሃያትን ከቦታችን ላይ ላያት አልቻልኩም የት ሄዳ ነው እኔን እንዳትቀሪ ብላኝ መቼም ቀርታ አይሆንም እያልኩ ከራሴ ጋር መነጋገር ጀመረኩ ጥቂት እንደቆየ ሀያት የክፍሉን በር አንኳክታ ወደ ውስጥ ገባች በእጇ ጠቆር ያለ ፌስታል ይዛለች በግምት አመጣለው ያለችው ልብስ ይመስለኛል አጠገቤ እንደተቀመጠች ወደ ፌስታሉ ተመለከትኩ ግምቴ ትክክል ስለነበር የሀያትን ፊት አይቼ ፈገግ አልኩኝ

የከሰአቱን ክፍለ ጊዜ ክፍል አልገባንም ከዚህ በፊት ዳኒ ይዞኝ ወደ ሄደው ደስ የሚለው ያ ነፋሻማ መዝናኛ ውስጥ ነበርን ደስ የሚል ኘሮግራም ነበር ብዙ ተማሪዎች ተሳትፈዋል እኔም ሀያት ያመጣችልኝን እጁ ትልትል ተደርጎ ለማሳመር በተሞከረው ነጭ ቲሸርትና ከስር ጥቁር ከለር ባለው አጠር ብሎ ጠበብ ባለው ቀሚስ ፏ ብያለሁ ሁሉም ፊቱ በተለያዩ ቀለማት ከነ ልብሱ ተጨመላልቋል ሰአት እየሄደ ነው አየሩ ብርዳማ ነው ሰማዩ በደመናው ጨለምለም ብሏል በቃ ዳኒ እኔ ልሂድ አልኩት የአክስቴን ነገር ስለሚያውቅ እሺ በቃ እኛ ጋር ሄደሽ ሻወር ውሰጂና ልብስ ቀያይረሽ ወደ ቤት እሸኝሻለሁ አለኝ እሺ አልኩት ምክንያቱም እቤት እንደዚህ ሆኜ መግባት ስለማልችል ሀያት ከቀሪ ተማሪዎች ጋር ፎቶ ቤት ሄደው ፎቶ ተነስተው ወደየ ቤታቸው እንደሚበታተኑ ነገረችኝ ያን ለማድረግ ሰአት እንደሌለኝና ከዳኒ ጋር ያሰብነውን ነገርኳት እሺ የኔ ውድ በቃ ጥሩ የኔን ልብስ እዛው ዳኒ ጋር አስቀምጪልኝ እኔ እራሴ እወስዳለሁ ብላኝ ጉንጬን ስማኝ ተለያየን

እንደዚህ እብድ መስለን ከ ዳኒ ጋር ታክሲ ይዘን ወደ እነሱ ቤት አመራን እየተቀላለድን የፎቁን ደረጃ ወጣን ከቤቱ ውስጥ እንደገባን ቦርሳዬን ተቀብሎኝ በቃ በዚህ ብርድ ቻይው አለኝ ወደ ሻወር ቤቱ እጁን ዘርግቶ ቶሎ በይ ደግሞ መክሰስ በልተን ዝናብ ሳይጥል እንድሸኝሽ ብሎ ቦርሳዬን ከ ሶፋው ላይ አሰቀመጠው

የሻወር ቤቱ ውስጥ ገብቼ እንዳለሁ ዳ....

PART ❶❽ ይቀጥላል !

any comment @kaludi_bot

join
@kalidoyeumi
@kalidoyeumi
@kalidoyeumi
788 viewsĸãlidö Ye ũmi , 18:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 21:51:23 #የአባቴ_ገዳይ

በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመረኮዘ !

ፀሀፊ፦ ካሊድ ታረቀኝ (ye umi)

አትቀልጂ አለኝ በፍቅር አይን እያየሁት ድምፄን ቀንሼ እየቀለድኩ አይደለም አልኩት እዛው መሬቱ ላይ እንደተኛው አንገቱን ዝቅ አድርጎ ወደ ከንፈሬ ተጠጋ አይኖቼን ጨፈንኳቸው በስሱ ከን........

Part ❶➏

አትቀልጂ አለኝ በፍቅር አይን እያየሁት ድምፄን ቀንሼ እየቀለድኩ አይደለም አልኩት እዛው መሬቱ ላይ እንደተኛው አንገቱን ዝቅ አድርጎ ወደ ከንፈሬ ተጠጋ አይኖቼን ጨፈንኳቸው በስሱ ከንፈሬን ሳመኝ ሌላ የማላውቀው አለም ሄጃለሁ በዚህ መሀል ስልኬ ጠራ ሁለታችንም ወደራሳችን ተመለስን ወዲያው ዳኒ ከላዬ ላይ ተነሳ ስልኩ ጠርቶ ሳይጨርስ ለማንሳት ተጣደፍኩ ስመለከት ሀያት ናት አላነሳሁትም አሁንም ደግማ መደወል ጀመረች ከቤቱ እየወጣሁ ስልኩን አነሳሁት እናንተ የት ሄዳችሁ ስትል ጠየቀችኝ የትም መጣን ስል መለስኩላት

ከነ ዳኒ ቤት ወተን ወደትምህርት ቤት መሄድ ጀምረናል ከ ዳኒ ጋር ከቤት ከወጣን ጀምሮ ምንም ንግግር በመሃላችን አልተፈጠረም ለምን እንደሆነ አላውቅም ምናልባት ተፋፍረንም ሊሆን ይችላል

እ.. እሮጥ እሮጥ አለ የጊቢው በር ላይ የቆመው ጥበቃ ሰአቱ ትንሽ እረፈድ ብሏል ዱብ ዱብ እያልን ወደ ውስጥ ገባን ዳኒ ቻው በቃ ብሎ ሲሮጥ ወደ ክፍሉ ሄደ ባለፈው የያዘን ዳይሬክተር ጊቢ ውስጥ እየተንጎራደደ ስለተመለከተው እንጂ ሰላም ሳይለኝ እንደዚህ ሲርጥ አይሄድም ነበር እኔም ቀልጠፍ ብዬ ወደ ክፍል አመራው ወደ ውስጥ ለመግባት በሩ ላይ ቆሜ ውስጥ ካለው መምህር ለመግባት ፍቃድ ጠይቄ ወደ ውስጥ ገባው ቦታዬ ላይ እንዳረፍኩኝ ሀያት ወደ ጆሮዬ ጠጋ ብላ የት ሄዳችሁ ነው ስትል ጠየቀችኝ የትም እዚሁ ነበርን ከጊቢ ውጪ ነበርን አልኳት ምሳ በላሽ እሺ ስትል ሌላ ጥያቄ አነሳች አንገቴን በመነቅነቅ አዎ አልኳት ፈገግ ብላ ጠቀሰችኝ ፈገግ ብዬ ላት ትኩረቴን ወደ ሚሰጠው ትምህርት አደረኩ።

ዛሬስ ከትንሿ ሀናን ዘግየት ብዬ ነው ከኡስታዝ ጋር የተገናኘሁት ሀናን በጣፋጭ አንደበቷ ቁርአን አንብባ ጨረሰች ተራው የኔ ነው አርፍጄ መምጣቴ ሳያንስ ከቀልቤ አለመሆኔ ያስገርማል እ.. ሀሊማ ጀምሪያ አሉ ምኑን አልኳቸው ፊታቸውን ኮስተር አድርገው ቁርአኑን ነዋ አንቺው ቀልብሽን ምን ሰለበው አሉኝ ትንሽ ፈገግ ብዬ ላቸው በውጤቴ ዙሪያ የተፈጠረውን ነገር ከባድ ጭንቀት እንደሆነብኝ ነገርኳቸው አብሽር ይሄማ እኮ ይስተካከላል ለዚህ ነው ጭንቀትሽ አብሽር እንዴ አንዳንዴ ነገሮች እንደዚህ ነው በሰብር በዱአ መጠንከር ነው ከኛ የሚጠበቀው ሲሉ እንደ አባትም እንደ ኡስታዝም ሆነው መከሩኝ የነበርኩበትን ሱራ አንብቤላቸሁ ተለያየን።

ሁሌም እንደማደርገው አባቴ ወደ ክፍሉ ሲሄድ ተከትዬው ወጣሁ ከበረንዳው ላይ ስደርስ ባባ ብዬ በመራመድ ላይ የነበሩ እግሮቹን አስቆምኳቸው ስለውጤቴ የተፈጠረውን እንባዬን እያፈሰስኩ ነገርኩት እሱም እንደ አባትነቱ ተረዳኝ አቅፎ አንባዬን እየጠራረገልኝ ያጋጥማል እኮ የኔ ልጅ ደግሞ ምነው ችግር አለ እንዴ ሲል ጠየቀኝ ከ ዳኒ ጋር የጀመርኩትን ጉድ ደብቄ ወደ ላይ ቀና ብዬ አይን አይኑን እያየሁት የለም አባ የራሴ ክፍተት ነው አልኩት በቃ በቀጣይ አሪፍ ውጤት አምጥተሽ ታስደስቺኛለሽ ደግሞ አልተከፋውብሽም ብሎ ግንባሬን ሳመኝና በቃ የምን ማኩረፍ ፈገግ በይ አለኝ ፈገግ ብዬለት እሺ ለአክስቴ ንገርልኝ አልኩት እንዴ ንገሪያት ምን አስፈራሽ ብትቆጣሽ ነው ብሎ አሳቀኝ ሳቄን ከጨረስኩ ቡሃላ እረ ባባ ንገርልኝ ትቆጣኛለች አልኩት በተፈጠረው ነገር እንዳልከፋበት በሚመስል መልኩ እየሳቀ እሺ ነግርልሻለሁ አለኝ ከመለያየታችን በፊት ግን አባ ተሽሎሀላ አልኩት አዎ ዛሬ ያው ስራም ወጣሁ አይደል አለኝ እሱማ አዎ በቃ ሁሌም ደህና ሁንልኝ ስል ተሰናብቼው ወደ ክፍሌ ተመለስኩኝ

የአንደኛው መንፈቅ አመት አጋማሽ ትምህርት ተዘግቷል ያመጣሁትን ወጤት አክሴ ሰምታለች ትንሽ ቶቆጥታኝ ብዙ ምክር ለግሳኛለች ከሀዩ ጋር አልፎ አልፎ እንደዋወላለን ከዳኒ ጋር የፍቅር ቃላትን በቴክስት እንቀባበላለን አመቺ ቦታ ላይም ስሆን ደውዬ ለት አወራዋለሁ እንደሚወደኝ ደጋግሞ ይገልፅልኛል እኔም እንደዛው ነኝ ምን እንዳስነካኝ ሊገባኝ ግን አልቻለም

ሁለተኛው ሴሚስተር.....


PART ❶❼ ይቀጥላል !

any comment @kaludi_bot

join
@kalidoyeumi
@kalidoyeumi
@kalidoyeumi
1.5K viewsĸãlidö Ye ũmi , 18:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-12 21:07:46 #የአባቴ_ገዳይ

በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመረኮዘ !

ፀሀፊ፦ ካሊድ (kalido ye umi)

ሀሉዬ አይዞሽ አለ እንደበርበሬ የቀሉትን አይኖቼን እየተመለከተ ተነሽ ብሎ እጁን ዘረጋልኝ ከክፍል ባልወጣ ደስ ይለኝ ነበር ግን ያው በሱ ላይ ልቤ አልጨክን ብሏል....

PART ❶➎

ሀሉዬ አይዞሽ አለ እንደበርበሬ የቀሉትን አይኖቼን እየተመለከተ ተነሽ ብሎ እጁን ዘረጋልኝ ከክፍል ባልወጣ ደስ ይለኝ ነበር ግን ያው በሱ ላይ ልቤ አልጨክን ብሏል እጁን ይዤ ከተቀመጥኩበት ተነስቼ አብሬው ክፍሉን ለቅቄ ወጣሁ በእረፍተ ሰአት ላይ የኔን ውጤት ለማወቅና እነደ አምናው አብረን ደስታችንን ልንከፋፈል አስበው መተው አፅናንተው የተመለሱት ኢልሃምና ሲትራ ወደ እኔ ሲመጡ ከደረጃው ላይ ተገጣጠምን አመጣጣቸው አምና በአንድ ላይ ስንበላ የነበረውን ምሳ ዛሬ ለትውስታ እንድንደግመው የፈለጉ ይመስለኛል ሁለቱም በእጃቸው የምሳ እቃቸውን ይዘዋል እግረ መንገዳቸውንም በተፈጠረው ነገር አፅናንተወኝም ሊመለሱ ይመስለኛል፡

እንዳዩኝ ከዳኒ ጋር የተጀመረው ነገር ያ ወዛገባቸው ይመስለኛል ሀሊማ አለችና ቀደም ብላ ጉንጬን ሳም ሳም አደረገችው ሲትራ ቀደም ብሎ ዳኒ ትቶኝ ወደታች ወርዶ እኔን መጠበቅ ጀመረ ኢልሃምም እንደ ሲትራ ጉንጮቼን ስማ ወዴት ነው ስትል ጠየቀችኝ ከነጋ ያልተ
ታየው ፈገግታዬን እያሳየውሃት እኔንጃ ወዴት እየወሰደኝ እንደሆነ አልኳቸው ምን እየሰራሁ እንደሆነ እንደኔው ግራ የገባቸው ይመስለኛል ሲትራ እሺ ቶሎ ትመለሻለሽ አለችኝ እኔንጃ ቆይ እስኪ ብዬ ዳኒን ጠርቼ ጠየኩት አዎ እንመለሳለን አለ በቃ እስክትመጪ እንጠብቅሻለን አብረን ምሳ እንድንበላ ነው የመጣነው አሉኝ ወይኔ በአላህ ውዶቼ እኔ ዛሬ መብላት አላሳኘኝም በቃ እናንተ ብሉ ምናልባት ልቆይባችሁም እችል ይሆናል ብያቸው ሀሳቤን ተቀብለውኝ አብሬያቸው ከደረጃው መውረድ ጀመርን

ዳኒ ወዴት ነው የምንሄደው አልኩት የትምህርት ቤቱ የጊቢው በር ጋር ስንደርስ ከፍቶሻል ደብሮሻል ምሳ አልበላሽም ይሄን ሁሉ እያየሁ እንዴት ዝም እላሻለሁ ፈታ ብለን አሪፍ ምሳ ጋብዤሽ እንመለሳለን አለ ደስ ብሎኛል በሃሳቡ ተስማምቻለሁ ጊቢውን ለቀን ወጣን፡

ከትምህርት ቤቱ ትንሽ እራቅ ካልን ቡሃላ፡ መጨረሻው ነው አለ እረዳቱ ዳኒ የት ነው ይዘኸኝ የመጣከው አልኩት የታክሲውን ሂሳብ ከፍሎ ወደ እኔ እንደተጠጋ እንዴ ከቤት ወተሽ ስለማታቂ ላስጎበኝሽ እኮ ነው ብሎ ትንሽ ቀለደብኝ እየሳኩለት እጄን ወደ ክንዱ ወስጥ አስገብቼ መጎዝ ጀመርኩ ሰማዩ ጠዋት እንደታየው የኔ ፊት ጠቆርቆር ብሏል ንፋሱም በመጠኑ ይነፍሳል ዝናብ ሊጥል መሆኑን በደንብ ያስታውቃል ዳኒ ዝናብ መጣ ብዬ ንግግሬን ሳልጀምር ማካፋት ጀመረ ነይ ደርሰናል በደንብ ሳይዘንብ ዱብ ዱብ እንበል አለኝ እሺ እሩቅ ነው እንዴ አልኩት አይ ደርሰናል አለ ሀሊማዬ ሲል ጠራኝና እኔኮ አፈቅርሻለሁ አለኝ ከሶምሶማ በማያንስ እሩጫ ከጎኔ ሆኖ እየተከተለኝ እኔም ዝምታን መርጬ ከጎኑ ሆኜ እየተጓዝኩኝ ነው

ከጥቂት ደቂቃዎች ቡሃላ በዛ ያሉ ኮንዶሚኔዬሞችን በውስጡ ከያዘ ውብ ጊቢ ደረስን ሀሳባችን ከዝናቡ ለማምለጥ ስለነበር ቀጥታ ወደ ጊቢው ገብተን ወደ አንዱ ብሎክ በፍጥነት ተከታትለን አመራን በፍጥነት እየተነፈስኩ የት ነው ግን ይዘከኝ የመጣኸው ስል ጠየኩት ከፎቁ ውስጥ እንደገባን ፡እቤት አለኝ ማለት አልኩት እኛ ጋር እቤት ነዋ አለኝ ከኮሪደሩ ላይ እንዳለን ጠቋሚ ጣቱን ቀስሮ የሀያት ቤት ያኛው ብሎክ ላይ ነው ሲል አሳየኝ ዞሬ ከተመለከትኩ ቡሃላ እሺ የኛ እዚህ መምጣት ለምን አስፈለገ ስል ጠየኩት ምነው ቅር አለሽ እኔ አሪፍ ምሳ በልተን ትንሽ ፈታ ብለን እንሄዳለን ብዬ ነው ቅር ከተሰኘሽ እንመለስ አለኝ አይ አላለኝም ና እሺ እስኪ ምሳህን ልቅመሰው አልኩት እሺ ስላልኩት ደስ ያለው ይመስለኛል

ከእቤቱ እንደገባን ቆንጆ ምሳ እራሱ ሰርቶ ሊያበላኝ መንጎዳጎድ ጀምሯል እኔ ከሶፉው ላይ ቁጭ ብዬ የከፈተውን ቴሌቭዥን እመለከታለሁ ዝናቡ በሀይል እየጣለ መሆኑን ከውጪ የሚሰማው ድምፅ በጣም ያስታውቃል

ቆንጆ ምሳ ሰርቶ አቀረበ እጄን ታጥቤ ከጎኑ ተቀመጥኩና አስተያየት የምሰጥህ በልቼ ስጨርስ ነው አልኩት እየሳቀ ችግር የለውም አለኝ እኔ ምልህ ቤተሰቦችህስ ስል ጠየኩት የምኖረው ከታላቅ እህቴ ጋር ነው ማታ ነው ከስራ የምትገባው ሌላ ቤተሰብስ ማለቴ እናትና አባትህ አልኩት በእጄ የያስኩትን እየጎረስኩ እነዛው ከቴሌቭዥኑ ጎን ወደተደረደሩት ፎቶዎች እጁን ቀስሮ ቆይ በልተን ስንጨርስ አያቸዋለሁ አልኩት እሺ ችግር የለውም እንዴ ደግሞ በደንብ ብይ እንጂ አይጣፍጥም እንዴ አለ እረ በጣም ቆንጆ ነው ጎበዝ ነህ ሳላደንቅህ አላልፍም አልኩት አመሰግናለሁ ለማንኛውም ብይ ብሎ በትልቁ አንስቶ ሊያጎርሰኝ እጁን ወደ አፌ ዘረጋ እ. እ. ስል ተግደረደርኩ እሱም ትንሽ ቀንሶ አጎራረሱን አስተካክሎ አጎረሰኝ እኔም አንድ አጎረስኩት እንዲህ እንዲህ እያልን የቀረበውን ምግብ ጥርግ አድርገን ጨረስን ላደረገልኝ ሁሉ ምስጋና አቀረብኩለት ለብርዱ ይሆነናል ብሎ አሪፍ ሻይም አፍልቶ አጠጣኝ

በመስኮቱ በኩል ወደ ውጭ ተመልክቶ በቃ ዝናብ አባርቷል ሰአት ሳይረፍድ ወደ ጊቢ እንሂድ አለኝ እሺ ብዬ ከተቀመጥኩበት ተነሳሁ እሱም ቴሌቭዥኑን አጥፍቶ ሻይ የጠጣንበትን ብርጭቆዎች ወደ ኪችኑ ይዞ ገባ በዚህ መሃል ቅድም በእጁ ወደ ጠቆመው ፎቶ ተጠግቼ ማየት ጀመርኩ ከውስጥ ተመልሶ ወጣና በሩን ዘግቶ ወደ እኔ መጣ እረስቼው ሳላሳይሽ ልንሄድ ነበራ ብሎ ከላይ የተሰቀለውን ፎቶ ከነ ፍሬሙ አውርዶ እነዚህ እናትና አባቴ ናቸው አሁን እዚህ የሉም በስራ ምክንያት ከሀገር ውጪ ናቸው ሲመጡ አስተዋውቅሻለሁ አለኝ ቀጣይ ፎቶውን አንስቶ ይቺ የመጀመሪያዋ እህቴ ናት አግብታ ከ አዲስ አበባ ውጪ ነው የምትኖረው ሁሉንም ፎቶ አብራርቶ እያሳየኝ የመጨረሻው ጋር ደረስን ይቺ ከኔ ጋር ያለችው ሁለተኛዋ እህቴ ነች አለኝ ቆንጆ እህት አለችህ አልኩት ፈገግ ብሎ ያነሳውን ፎቶ ወደ ቦታው ሊመልሰው ሲል በዚሁ ፎቶ ተከልሎ የነበረ አንድ ፎቶ አየው ቀደም ብዬ አነሳሁትና አይቼው ሳቄን ለቀኩት ዳኒ በልጅነትህ እንደዚህ ነበርክ ብዬ እያሳየሁት ሳኩ በእጁ የያዘውን ፎቶ አስቀምጦ ፈገግ አለ ይሄንንማ ለሀያት አሳያታለሁ አልኩ እንዴ ቀልድ አለ የያስኩትን ሊቀማኝ ወደ እኔ ተጠጋ እኔም ፎቶው እኔን እንዲህ ካሳቀ ሀያትን ስያታለሁ ፎቶውን እንዳይቀማኝ በሳቅ ውስጥ ሆኜ እየለመንኩት በጠረጴዛው መሽከርከር ጀመርኩ በዚህ መሃል ጠረጴዛውን ዘሎት ወደ እኔ ሲመጣ እግሩ እረዘም ያለው ቀሚሴ ላይ አረፈ ላመልጠው አልቻልኩም ይባስ ጠልፎኝ ወደኩ ዳኒም አልቀረለትም ከላዬ ላይ ተደረበ ፎቶው ከእጄ ወቶ ወደቀ ዳኒ ከላዬ ላይ ወድቋል ቅድም በሳቅ እንደዛ የቀወጥኩት ቤት ፀጥ አለ አንገቴ የዳኒ ጡንቻን ተንተርሷል ከላዬ ሆኖ አይን አይኔን ያየኛል ጥቂት ቆይቶ ወደ ጆሮዬ ጠጋ ብሎ በሹክሹክታ አፈቅርሻለሁ አለኝና ቀና አለ እኔም አፈቅርሃሉ ስል ህመሜን አወጣሁት ዳኒ ያመነኝ አልመስለኝም አሁንም ጠጋ ብሎ አትቀልጂ አለኝ በፍቅር አይን እያየሁት ድምፄን ቀንሼ እየቀለድኩ አይደለም አልኩት እዛው መሬቱ ላይ እንደተኛው አንገቱን ዝቅ አድርጎ ወደ ከንፈሬ ተጠጋ አይኖቼን ጨፈንኳቸው በስሱ ከን........


PART ❶➏ ይቀጥላል !

any comment @kaludi_bot

join
@kalidoyeumi
@kalidoyeumi
@kalidoyeumi
1.9K viewsĸãlidö Ye ũmi , 18:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-12 17:33:05

Zbura production

[ለመንዙማና ለነሺዳ ፣ ለዳእዋ ፕሮግራሞች፣ ለመውሊድና ለመድረሳ ፕሮግራሞች ፣ ለምርቃት ፣ ለኢስላማው ዘጋቢ ፊልሞች(documentary) ፣ ለመድረክ ፕሮግራም፣ ለዩቲዩብ ስራዎቾት፣ ለቻናሎ ኢንትሮ(መግቢያ) ፣ ሎጎ ዲዛይን፣ ለማስታወቂያና ለተለያዩ ኢስላማዊ ስራዎቾት በ +251949440174 ወይንም +251946753017 ላይ ይደውሉ 4. ጥራትን የተላበሱ ምስሎችን ለማግኘት ]

ዘቡራ ፕሮዳክሽን!

በቴሌግራም
https://t.me/joinchat/TACAe3wQVdk2YjU0

በፌስቡክ
https://www.facebook.com/108334804596822

በዩቲዩብ
https://youtube.com/channel/UCAIgV6PupXL0kh-vXScMwZg
1.7K viewsĸãlidö Ye ũmi , 14:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-12 09:06:11 እየሰገደ ሞተ፡ ሱጁድ ላይ እያለ ሞተ፡ ፆመኛ ሁኖ ሞተ
እሄ ነገር በአጋጣሚ የመጣ ወይንም የሚመጣ እንዳይመስልህ፡፡ የሰው ልጁ ዱንያ ላይ ሲያበዛው በነበረው ነገር ላይ ነው የሚሞተው፡፡

እራስህን መርምር ምን ላይ ነህ?

#kaludi

መልካም ቀን
@kalidoyeumi
1.8K viewsĸãlidö Ye ũmi , 06:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ