Get Mystery Box with random crypto!

Ethiopian Trading Businesses Corporation (ETBC)

የቴሌግራም ቻናል አርማ etbcinfo — Ethiopian Trading Businesses Corporation (ETBC) E
የቴሌግራም ቻናል አርማ etbcinfo — Ethiopian Trading Businesses Corporation (ETBC)
የሰርጥ አድራሻ: @etbcinfo
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.13K

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 14

2022-09-15 09:09:50
477 views06:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-09 13:04:13
627 views10:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-09 10:11:52

670 views07:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-09 09:44:58
578 views06:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-08 13:24:56
521 views10:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-08 11:02:25
ኮርፖሬሽኑን ለተቀላቀሉ አዲስ ሰራተኞች የትውውቅ ስልጠና ተሰጠ

የኢትዮጵያ ንግድ ስራዎች ኮርፖሬሽንን በቅርቡ ለተቀላቀሉ አዲስ ሰራተኞች የትውውቅ (ኢንዳክሽን) ስልጠና ጳጉሜ 03/ 2014 ዓ.ም ተካሄደ፡፡ ስልጠናውን ያዘጋጀው የኮርፖሬት የሰው ሃብት ልማትና ሥራ አፈጸጻም አመራር ቡድን ሲሆን የስልጠናው ዓላማ ለአዲስ ሰራተኞች የኮርፖሬሽኑን አጠቃላይ ገጽታ እና አሰራር ማስተዋወቅ ላይ ያተኮረ ነው፡፡

ስልጠናውን የሰጡት የኮርፖሬት ሰው ሃብት ስራ አመራር ዳይሬክቶሬት፣ የኮርፖሬት የህግ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት፣ የኮርፖሬት ሥነ-ምግባርና ጸረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት እና የኮርፖሬት ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት ሲሆኑ ከተለያዩ ዘርፎችና የስራ ክፍሎች የተውጣጡ ሰራተኞች በሥልጠናው ተካፍለዋል፡፡
478 views08:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-06 10:46:16
ለሲሚንቶ ተጠቃሚ ደንበኞች የወጣ የሽያጭ ፕሮግራምና ግዥ ለመፈፀም ማሟላት ያለባቸው መረጃዎች
185 views07:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-05 13:47:32 ኮርፖሬሽኑ የሲሚንቶ ምርት ሽያጭ በማካሄድ ላይ ይገኛል

መንግስት ከሲሚንቶ ምርት ግብይት አኳያ የሚታየውን ችግርና የዋጋ ንረት ለማረጋጋትና የምርት ስርጭቱን ቅደም ተከተል በማስቀመጥ ግብይቱን ግልጽና ተደራሽ ለማድረግ እንዲያስችል የአሰራር ስርዓት ዘርግቷል፡፡ በመሆኑም ከአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ በተላከው የሲሚንቶ ምርት፣ ግብይትና ስርጭት መመሪያ መሰረት የኢትዮጵያ ንግድ ስራዎች ኮርፖሬሽን ለሲሚንቶ ምርት ፈላጊዎች ሽያጭ እያከናወነ ይገኛል፡፡

አስፈላጊውን መረጃ ላሟሉ ለመንግስት ግንባታ እና ለግል ገንቢዎች እንዲሁም ለብሎኬት አምራቾች ከነሐሴ 17/ 2014 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆን የሽያጭ ፕሮግራም ኮርፖሬሽኑ ያወጣ ሲሆን ተጠቃሚ የሚሆኑት ክፍለ ከተሞች ቂርቆስ፣ ልደታ፣ አዲስ ከተማ፣ ኮልፌ ቀራንዮ፣ ጉለሌ እና ንፋስ ስልክ ላፍቶ ናቸው፡፡ ከነሐሴ 17- 27/2014 ዓ.ም የቂርቆስ፣ የልደታ እና የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተሞች ተጠቃሚ የነበሩ ሲሆን ከነሐሴ 28/ 2014 ዓ.ም ጀምሮ ደግሞ የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ተጠቃሚ በመሆን ላይ ይገኛል፡፡ የጉለሌ እና ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተሞች ደግሞ በመቀጠል በወጣላቸው ፕሮግራም መሰረት ተጠቃሚ ይሆናሉ፡፡
168 views10:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-05 09:26:22 የዝውውር/የውስጥ ዕድገት ማስታወቂያ
186 viewsedited  06:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-05 09:26:21 ከባድ የእምነት ማጉደል የሙስና ወንጀል የፈጸመ የኮርፖሬሽኑ ሠራተኛ በእስርና በገንዘብ ተቀጣ

አቶ ሙሉጌታ ጃሌ የተባለ በደሴ ቅርንጫፍ የሸዋሮቢት ግብይትና ክምችት ጣቢያ ሠራተኛ ሆኖ ሲሰራ በህዝብና በመንግስት የተሰጠው አደራ ወደ ጎን በመተው ተገቢ ያልሆነ ብልጽግና ለማግኘት በማሰብ ከ2.8 ሚሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያለው የመንግስት ንብረት በማጉደል በፈጸመው የሙስና ወንጀል የእስርና የገንዘብ ቅጣት ተወሰነበት፡፡
የኮርፖሬት የውስጥ ኦዲት ዳይሬክቶሬት ባደረገው ጥልቅ የሰነድ ምርመራ ግለሰቡ ከተረከበው የመንግስት የእህል ምርት ውስጥ ከ2.8 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያለው ምርት በህገ ወጥ መንገድ ከመጋዘን አውጥቶ በመሸጥ ከባድ የእምነት ማጉደል ወንጀል መፈጸሙ በማስረጃ ይረጋግጣል፡፡ ይህን የኦዲት ግኝት መሠረት በማድረግ የኮርፖሬት የህግ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት አስፈላጊውን ማጣራት ካደረገ በ|ላ ክስ ለመመስረት የሚያስፈልጉት መሠረታዊ ጭብጦችን በማዘጋጀት ወንጀሉ እንዲመረመርና ክስ እንዲመሰረት በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ፖሊስ ኮሚሽን ለሰሜን ሸዋ ዞን ፖሊሰ የሙስና ወንጀሎች ምርመራ ክፍል ጥያቄ ያቀርባል፡፡
የምርመራ ጥያቄው የቀረበለት የሰሜን ሸዋ ፖሊስ የሙስና ወንጀሎች ምርመራ ክፍል በተሰጠው ስልጣንና ኃላፊነት መሠረት አቶ ሙሉጌታ ጃሌ የፈጸሙት የእምነት ማጉደል የሙስና ወንጀልን በጥልቀት በመመርመር ተጠርጣሪውን ተከታትሎ በመያዝ ለህግ ያቀርባል፡፡
የክስ መዝገቡም በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ፍትህ ቢሮ የደብረብርሃን ምድብ ማስተባበሪያ ተልኮ አቃቤ ህግም ክስ አቀርቦ ሲከራከር ቆይቶ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት በዕለቱ በዋለው ችሎት በጉዳዩ ላይ ግራና ቀኙን ካከራከረ በኃላ ተከሳሽ የቀረበበትን ክስ ማስተባበል ባለመቻሉና በከሳሽ በኩል የቀረቡት የሰነድ ማስረጃዎች ግለሰቡ ከፍተኛ የእምነት ማጉደል የሙስና ወንጀል መፈጸሙ ስለታመነ ተከሳሹን ያርማል ሌሎችንም ያስጠነቅቃል ብሎ ባመነበት ተከሳሽ ከኮርፖሬሽኑ እምነት በማጉደል የዘረፈውን ብር 2.890,031 (ሁለት ሚሊዮን ስምንት መቶ ዘጠና ሺህ ሰላሳ አንድ ብር) ከወጪና ኪሳራ ተሰልቶ እንዲከፍል፣በሁለት ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣትና በ9 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ፍርድ ቤቱ ወስኗል፡፡
ማጠቃለያ
በአጠቃላይ ከዚህ ግለሰብ ከባድ የእምነት ማጉደል የሙስና ወንጀል ድርጊት፣የክስ ሂደትና የፍርድ ውሳኔ መገንዘብ የሚቻለው ማንኛውም ግለሰብ የማጭበርበር የሙስና ወንጀል በመፈጸም የመንግስትና የሕዝብ ሀብትን ወስዶ ለጊዜው ከህግ ተሰውሮ ቢቆይም ወቅቱን ጠብቆ ከህግ ተጠያቂነት ማምለጥ እንደማይቻል የጥንቃቄ መልዕክት ለማስተላለፍ ነው፡፡ ስለዚህ በሚከተሉት የጥቆማ መስጫ መንገዶች ጥቆማ፣ቅሬታና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ማቅረብ የምትችሉ መሆኑን በቅድሚያ እናሳውቃለን፡፡
በመደበኛ ስልክ፡-011 416 88 94 በተንቀሳቃሽ ስልክ፡-09 11 96 65 09, 09 11 65 96 96 - ፖ.ሳ.ቁ፡-3321
የኮርፖሬት ሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት
188 views06:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ