Get Mystery Box with random crypto!

Ethiopian Trading Businesses Corporation (ETBC)

የቴሌግራም ቻናል አርማ etbcinfo — Ethiopian Trading Businesses Corporation (ETBC) E
የቴሌግራም ቻናል አርማ etbcinfo — Ethiopian Trading Businesses Corporation (ETBC)
የሰርጥ አድራሻ: @etbcinfo
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.13K

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 13

2022-10-10 14:04:55
190 views11:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-07 09:41:36
158 views06:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-06 10:34:40
210 views07:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-05 14:43:24 መስከረም 24፣ 2015

ከሲሚንቶ ግብይት መመሪያ ውጪ ሲዘዋወር ነበር የተባለ ከ22,000 ኩንታል በላይ ሲሚንቶ ተይዞ እርምጃ መወሰዱ ተነገረ፡፡

ይህንን ያለው የአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ቢሮ ነው፡፡

የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር የሲሚንቶ ዋጋ እጥረትን ለመቆጣጠር የሲሚንቶ ግብይት መመሪያ ማውጣቱ የሚታወስ ነው፡፡

የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮም ለከተማው የተመደበው ሲሚንቶ ከተቀመጠው አሰራር ውጪ ገበያ ላይ እንዳይውል ከኦሮሚያ ልዩ ዞን እና ከኦሮሚያ ንግድ ቢሮ ጋር በትብብር ቁጥጥር እያደረገ መሆኑን ተናግሯል፡፡
የከተማው የንግድ ቢሮ ሀላፊ አቶ አደም ኑሪ እንደተናገሩት በተሰራው የቁጥጥር ስራ 22,293 ኩንታል ሲሚንቶ ከመመሪያው ውጪ ሲዘዋወር ተይዟል፡፡

ቢሮው በመግቢያ በሮች ከሚያደርገው ቁጥጥር በተጨማሪ በከተማው ውስጥ በሚገኙ የንግድ ቤቶች፣ የተጀመሩ የግንባታ ስራዎች እንዲሁም የሲሚንቶ ማከማቻ ስፍራዎቹ ባደረገው ፍተሻ መያዙ ተነግሯል፡፡

ከተያዘው ውስጥ 15,179 ኩንታል ተወርሶ በኢ.ግ.ል.ድ እና በንግድ ስራዎች ኮርፖሬሽን በኩል ለገበያ ቀርቦ መሸጡን ሀላፊው ተናግረዋል፡፡

2,266 ኩንታሉ ደግሞ ተጣርቶ ህጋዊነቱን የሚያረጋግጥ መረጃ በመቅረቡ ተለቋል ቀሪው መንግስት በተመነው ዋጋ እንዲሸጥ ሆኗል ብለዋል፡፡

የሲሚንቶ ምርትን በቀጥታ ከፋብሪካዎች ገዝተው እንዲጠቀሙ በመመሪያው የተፈቀደላቸው ተቋማት የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን፣ የውሃ ፍሳሽ ባለስልጣን፣ የሜጋ ግንባታ ፕሮጀክት ጽ.ቤት የመንገድና ባለስልጣን እና የዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ ናቸው ተብሏል፡፡

ከዚህ ውጪ በአዲስ አበባ ላለው የሲሚንቶ ፍላጎት ከፋብሪካዎች በመረከብ በችርቻሮና በጅምላ የሚያቀረቡት የኢንዱስትሪ ግብአቶች ልማት ድርጅት (ኢግልድ) እና የንግድ ስራዎች ኮርፖሬሽን ብቻ ናቸው ብሏል ቢሮው በመግለጫው፡፡

ቴዎድሮስ ወርቁ

(ሸገር ኤፍኤም 102.1 ራዲዮ)
239 views11:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-30 10:04:27
234 views07:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-29 15:41:05
157 views12:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-24 10:19:59
77 views07:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-23 15:50:14
ኮርፖሬሽኑ 326 ሚሊየን 272 ሺህ 12 ብር ትርፍ ከታክስ በፊት አስመዘገበ

የኢትዮጵያ ንግድ ስራዎች ኮርፖሬሽን በ2014 በጀት ዓመት 326 ሚሊየን 272 ሺህ 12 ብር ትርፍ ከታክስ በፊት እንዳስመዘገበ ተገለጸ፡፡ አመራሩና ሰራተኛው ባሳዩት ከፍተኛ አፈጻጸም ትርፋማ መሆን እንደተቻለና የተመዘገበው ትርፍ ካለፉት ዓመታት የበለጠ መሆኑን የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አቻ ደምሴ ገልጸዋል፡፡ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አያይዘውም በተገኘው አመርቂ ውጤት ለኮርፖሬሽኑ አመራርና ሰራተኞች የሶስት ወራት ደመዎዝ ጉርሻ እና የሶስት እርከን ደመወዝ ጭማሪ በማትጊያነት እንዲሰጥ በስራ አመራር ቦርዱ መወሰኑን አረጋግጠው ለኮርፖሬሽኑ ሰራተኞች የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡

ኮርፖሬሽኑ የ2015 በጀት ዓመት የእቅድ ትውውቅ ቀጣይ መድረክ መስከረም 12/ 2014 ዓ.ም አካሂዷል፡፡ በዚህ መድረክ የ2014 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት፣ በ2014 በጀት ዓመት በኮርፖሬሽኑ እቅድ አፈጻጸም የነበሩ ክፍተቶች እንዲሁም የሰራተኛ ማህበር ሪፖርት ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተካሂዶባቸዋል፡፡ ከሰኣት በኋላ በነበረው መርኃ ግብር የ2015 በጀት ዓመት እቅድ ቀርቦ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
178 views12:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-22 14:13:51
221 views11:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-20 15:43:35
የ2015 በጀት ዓመት የእቅድ ትውውቅ መድረክ ተካሄደ

የኢትዮጵያ ንግድ ስራዎች ኮርፖሬሽን የ2015 በጀት ዓመት የእቅድ ትውውቅ መድረክ ከአራቱም ዘርፎች የተውጣጡ ሥራ አስፈጻሚዎች፣ አመራሮችና ሰራተኞች በተገኙበት መስከረም 9/ 2015 ዓ.ም በኢትዮጵያ ሆቴል ቁ.2 ተካሄደ፡፡

የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አቻ ደምሴ በመድረኩ መክፈቻ ላይ ባስተላለፉት መልእክት መድረኩ ትልቅ ትኩረት የተሰጠው መሆኑን በመጥቀስ የዓመቱን እቅድ በውጤታማነት ለማከናወን የሚያስችል አቅም ለመፍጠር መድረኩ መዘጋጀቱን ገልጸዋል፡፡ ከሰራተኞችም ጠቃሚ ግብአት እንደሚጠበቅም አያይዘው ጠቁመዋል፡፡ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አክለውም ኮርፖሬሽኑ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ትርፋማ በመሆኑ ለአጠቃላይ ሰራተኞች የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡ በየደረጃው ያሉ ሰራተኞችና አመራሮች ያደረጉት ጥረት ኮርፖሬሽኑን ትርፋማ እንዳደረገ ጠቁመዋል፡፡

በመድረኩ የኮርፖሬሽኑ የ2014 በጀት ዓመት ሪፖርት፣ በ2014 በጀት ዓመት በኮርፖሬሽኑ እቅድ አፈጻጸም የነበሩ ክፍተቶች እንዲሁም የሰራተኛ ማህበር ሪፖርት ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተካሂዶባቸዋል፡፡ ከሰኣት በኋላ በነበረው መርኃ ግብር የ2015 በጀት ዓመት እቅድ ቀርቦ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ በዋና መ/ቤትና በዘርፍ ደረጃ ከጀማሪ እስከ መካከለኛ ደረጃ ያሉ 400 ሰራተኞች በመድረኩ የተሳተፉ ሲሆን ከጥቂት ቀናት በኋላም ሌሎች 400 ሰራተኞችን ያካተተ ተመሳሳይ መድረክ እንደሚኖር ከወጣው መርሃ ግብር ለማወቅ ተችሏል፡፡ በቀጣይም የውይይት መድረኩ በሁሉም የክልል ግብይት ማዕከላት ተካሂዶ የማጠቃለያ መድረክ እንደሚኖር ተመላክቷል፡፡

የውይይት መድረኩን መጠናቀቅ ተከትሎ የመድረኩን ተሳታፊዎች በሙሉ ያካተተ የእራት ግብዣ ሥነ-ስርዓት ተካሂዷል፡፡
314 views12:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ