Get Mystery Box with random crypto!

Ethiopian Trading Businesses Corporation (ETBC)

የቴሌግራም ቻናል አርማ etbcinfo — Ethiopian Trading Businesses Corporation (ETBC) E
የቴሌግራም ቻናል አርማ etbcinfo — Ethiopian Trading Businesses Corporation (ETBC)
የሰርጥ አድራሻ: @etbcinfo
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.13K

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 12

2022-10-27 14:47:26
274 views11:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-27 11:19:51
289 views08:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-27 10:45:08 ኮርፖሬሽኑ በ2014 በጀት ዓመት የውስጥ አሠራር ሥርዓት ባላከበሩና የሥነ-ምግባር ጥሰት በፈፀሙ ሠራተኞች ላይ የተለያዩ አስተዳደራዊ እርምጃዎች ወሰደ

የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን በ2014 በጀት ዓመት አሠራርን፣ አገልግሎት አሰጣጥን፣ ሀብት አጠቃቀምንና መልካም አስተዳደርን በተመለከተ ከውስጥና ከውጭ ደንበኞች የቀረቡ 469 ጥቆማዎችን በመቀበል በ247 (73%) አመራርና ሠራተኞች ላይ የማጣራት ሥራዎች በማካሄድ በ54ዎቹ ላይ የተለያዩ አስተዳደራዊ እርምጃዎች እንዲወሰዱ አድርጓል። በሌሎች 12 የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች ላይ ደግሞ በተቋሙ የዲሲፕሊን ኮሚቴ አማካኝነት ጉዳያቸው በመታየት ላይ ይገኛል፡፡

እምነት በማጉደል ስርቆት መፈጸም፣ የሥራ ተግባርና ኃላፊነት በአግባቡና በታማኝት አለመወጣት፣ ቅጥር፣ ዝውውርና ደረጃ ዕድገት ማጓተት፣ የሰዓት መቆጣጠሪያ ላይ አስቀድሞ መፈረም፣ የጥገና አገልግሎት መጓተት፣ ያለ ፍቃድ ከሥራ መቅረት፣ የደንብ ልብስ የጥራትና የሥርጭት አሠራር ክፍተት መኖር፣ ከመመሪያ ውጭ የተለያዩ የዲሲፕሊን ግድፈቶች መፈጸም፣ በሥራ ገበታ አርፍዶ መገኘት፣ ተገቢ ያልሆነ የጥቅማጥቅም ክፍያ መፈጸም፣ በሀሰት የትምህርት ማስረጃ መገልገልና ያለበቂ ምክንያት ሥራን ማዘግየት የሚሉት ከውስጥና ከውጭ ተገልጋዮች የቀረቡ ጥቆማዎች ናቸው፡፡

ከዚህም በተጨማሪ ያለደረሰኝ ግብይት መፈጸምና ሚዛን ማጉደል፣ ሥራ በማጓተት ተገቢ ያልሆነ ጥቅም መጠየቅ፣ የመጠቀሚያ ጊዜያቸው የተቃረቡ ምርቶች ግዥ መፈጸም፣ በሥራ ሰዓት የመሸጫ ሱቆች ከፍቶ አገልግሎት ያለመስጠት፣ ሥራን በአግባቡ ባለመወጣት ምርት ማጉደል፣ የገቢ ሂሳብ ሪፖርት በጥራትና በጊዜ ገቢ አለማድረግ፤ የክፍያ ሰነድ ትክክለኝነት ሳይረጋገጥ ለክፍያ መምራት፣ የተሰበሰበውን ገንዘብ በወቅቱ ገቢ አለማድረግ፣ በአገልግሎት ስታንዳርድ መሠረት አለመምራትና የትርፍ ሰዓት ክፍያ ቁጥጥርና ክትትል ሥርዓት ላይ ክፍተት መኖር በኮርፖሬሽንና በሌሎች አካላት የወጡ መመሪያዎችን ተግባራዊ ባለማድረግ የተፈጸሙ የአሠራር ክፍተቶች ሆነው የቀረቡ ጥቆማዎች ናቸው፡፡

በአጠቃላይ በበጀት ዓመቱ ከደንበኞች የመጣውን ጥቆማ ጨምሮ ተቋሙ ያስቀመጠውን የውስጥ አሠራር ሥርዓት ያላከበሩና የሥነ-ምግባር ጥሰት የፈፀሙ ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ፣ የገንዘብ ቅጣት፣ ከኃላፊነት ቦታ ከማንሳት እስከ የሥራ ስንብት የሚደርሱ እርምጃዎች ተወስደዋል፡፡ በዚህም 8 የቃል ማስጠንቀቂያ፣ 12 የጹሑፍ ማስጠንቀቂያ፣ 17 የደመወዝ/ገንዘብ ቅጣትና የጹሑፍ ማስጠንቀቂያ እንዲሁም 12 የሥራ ስንብት እርምጃ መወሰዱን ከኮርፖሬት ሥነምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
274 views07:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-26 15:22:10
289 views12:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-20 15:50:58
480 views12:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-18 11:59:30
502 views08:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-18 11:59:23 ለዘርፉ ሽያጭና መጋዘን ሠራተኞች በሙያ ሥነምግባር፣በሙያ ደህንነትና በምርት እንክብካቤ ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ

ለአትክልትና ፍራፍሬ ንግድ ሥራ ዘርፍ ሽያጭና መጋዘን ሠራተኞች በሙያዊ የሥነምግባር፣በሙስና ወንጀል ህጎች፣በሠራተኞች ደህንነትና ጤና አጠባበቅ እንዲሁም በምርት አያያዝና እንክብካቤ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ፡፡

በስልጠናው መድረክ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የዘርፉ ሥራ አስፈጻሚ አቶ መህዲ አስፋው ሲሆኑ ለሰልጣኞቹ ባስተላለፉት መልዕክት፣ለደንበኞች የሚሰጡ አገልግሎቶች ሙያዊ ሥነምግባርን በተላበሰ መንገድ መከናወን እንዳለባቸው በተለይ በድርጅቱ የተሰጣቸው የሥራ ኃላፊነት እና ንብረት በታማኝነት፤ በቅንነትና በአገልጋይነት ስሜት መወጣት እንደሚጠበቅባቸው ተናግረዋል፡፡

የዘርፉ ሥራ አስፈጻሚ አክለውም በደንበኞች አገልግሎት አሰጣጥ ሂደት ውስጥ የሚታዩ ህገ ወጥ አሠራሮች ካለፉት ዓመታት አንጻር ሲታዩ የመቀነስ አዝማሚያ ቢያሳዩም ሙያዊ ሥነምግባር በተላበሰ መንገድ ለደንበኞች አገልግሎት አለመስጠት፤ሚዛን ማጉደል፤የመንግስት የሥራ ሰዓት ማባከን፣የምርት ብልሽት በሚፈለገው ደረጃ አለመቀነስና የሥራ ተነሳሽነት ደካማ መሆን አሳሳቢ እየሆኑ የመጡ ችግሮች መሆናቸውን የቅርብ የክትትልና ቁጥጥር ሪፖርቶች (Supervision Report) ያመለክታሉ በማለት ተናግረዋል፡፡

በመጨረሻም የሥራ ዘርፉ በ2015 በጀት ዓመት ያስቀመጣቸውን ዋና የትኩረት አቅጣጫ የደንበኞች አገልግሎት አሰጣጥ ማሻሻል፣ሀብትና ንብረትን በቁጠባ መጠቀም፤የምርት ብልሽትና ብክነትን መቀነስ፣ የሠራተኞችን ምርታማነት ማሳደግና ትርፋማ የመሆን ግቡን ለማሳካት የአቅም ግንባታ መድረኮች አጠናክሮ እንደሚሰራ አቶ መህዲ አስፋው ገልጸዋል፡፡

የዘርፉ 95 ሽያጭና የመጋዘን ሠራተኞች ለሶስት ተከታታይ ቀናት የተሰጠውን የሙያዊ ሥነምግባር፤የሙስና የወንጀል ህጎች፣የሙያ ደህንነትንና የምርት እንክብካቤ ስልጠና በትኩረት ተከታትለው አጠናቀዋል፡፡
486 views08:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-18 09:02:31
“በደማችን ያስከበርናትን ሰንደቅ ዓላማ በላባችን ከፍ እናደርጋታለን”
መልካም የሰንደቅ ዓላማ ቀን!
383 views06:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-13 15:31:01
572 views12:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-13 14:59:56
504 views11:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ