Get Mystery Box with random crypto!

ብራና ሚዲያ BRANA MEDIA

የቴሌግራም ቻናል አርማ brana_book — ብራና ሚዲያ BRANA MEDIA
የቴሌግራም ቻናል አርማ brana_book — ብራና ሚዲያ BRANA MEDIA
የሰርጥ አድራሻ: @brana_book
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 373

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2023-01-16 18:12:02
172 viewsMIKIYAS DANAIL, 15:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-16 18:11:55
148 viewsMIKIYAS DANAIL, 15:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-16 18:11:51
132 viewsMIKIYAS DANAIL, 15:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-16 18:11:46
156 viewsMIKIYAS DANAIL, 15:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-16 10:28:20
22 viewsMIKIYAS DANAIL, 07:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-09 14:01:04
165 viewsMIKIYAS DANAIL, 11:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-09 14:00:55 *ሊቀ ዲያቆናት ቅዱስ እስጢፋኖስ
•••••••••••••••••••••••••••••••••
“ የጻድቃንን ሞት እኔ ልሙት፥ ፍጻሜዬም እንደ እርሱ ፍጻሜ ትሁን።”
ዘኍልቁ 23፥10
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
የስሙ ትርጉም - በግሪክ ቋንቋ አክሊል ማለት ነው፡፡ በግብሩ የቀን ሃሩር የሌሊት ቁር የማይለውጠው፣ መብራት ማለት ነው፡፡

አባቱ ስምኦን፣ እናቱ ሃና ይባላሉ፡፡

የተወለደው - ጥር 1 ቀን በእስራኤል ሃገር ውስጥ በብፅዓት /በስለት/ ነው፡፡ ልዩ ስሟ ሐኖስ በተባለ ቦት ተወለደ ከመጥምቁ ዮሐንስ እግር ሥር በመሆን ተምሯል፡፡

ጥቅምት 17 ቀን ሐዋርያት ሊቀ-ዲያቆናት አድርገው ሾሙት፡፡

ወንጌልን በማስተማሩ አይሁድ በጠላልትነት ተነስተውበት ጥር 1 ቀን በ34 ዓ.ም. በድንጋይ ተወግሮ በስማዕትነት አረፈ፡፡ በዚህም ቀዳሚ-ሰማዕት ተሰኘ፡፡

"ሰማዕታት የዚህችን ዓለም ጣዕም በእውነት ናቁ ፤ ደማቸውን ስለ እግዚአብሔር አፈሰሱ ፤ ስለ መንግስተ ሰማያት መራራ ሞትን ታገሱ"

ውዳሴ ማርያም ዘሐሙስ ቁ.6

ቅዱስ እስጢፋኖስ ጸጋንና ኃይልን ተሞልቶ በሕዝቡ መካከል ድንቅንና ታላቅ ምልክትን ያደርግ ነበር፡፡ ከግሪክ አገር የመጡ አይሁድ በተከራከሩት ጊዜ በመንፈስና በጥበብ መለሰላቸው፡፡ አይሁድም ዳኞች በተሰየሙበት ሸንጎ ፊት አቅርበው በሐሰት ከሰሱት፤ ሸንጎውም በድንጋይ እንዲወገር ፈረደበት፡፡ እስጢፋኖስ ግን በታላቅ ኃይልና በብዙ መረዳት ከአባቶቻቸው ታሪክ ተነሥቶ የዓለም መድኃኒት የሆነውን ክርስቶስን ሰበከላቸው፡፡ ጥላውን ከአካሉ ጋር እያጋጠመ ወደ ፍጹማን ጥበብ በጽድቅ ቃል መራቸው፡፡ አይሁድ በጣም ተቆጡ፤ ሁሉም በአንድነት ሆነው በድንጋይ ወገሩት፡፡ ቅዱስ እስጢፋኖስ ሰውነቱ ቆስሎና ዝሎ ዓይኖቹን ወደ ሰማይ ባነሣ ጊዜ የልዑልን ክብር ተመለከተ፡፡ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአባቱ ቀኝ ቆሞ አየ፡፡ የሐዋ.ሥራ 7÷55፡፡

ቅዱስ አሰስጢፋኖስ “እነሆ ሰማያት ተከፍተው የሰው ልጅ (ኢየሱስ ክርስቶስ) በአባቱ ቀኝ ቆሞ አያለሁ” አላቸው፡፡ አይሁድ ግን ልበ-ደንዳኖች (የማይራራ ጨካኝ ልብ ያላቸው) ስለሆኑ እስጢፋኖስን ከከተማ ወደ ውጭ አውጥተው ደበደቡት፡፡ ቅዱስ እስጢፋኖስ ሰውነቱ ደከመ፤ ነፍሱ ከሥጋው ልትለይ በደረሰች ጊዜ በሞት ጣር ሆኖ “ጌታ ኢየሱስ ሆይ ይህን ኃጢአት አትቁጠርባቸው፤ ነፍሴን ተቀበል” ብሎ ጸለየ፡፡ ነፍሱንም ለታመነው ፈጣሪ አደራ ሰጥቶ ጥር 1 ቀን በ34 ዓ.ም በሰማዕትነት ዐረፈ፡፡

ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በተአምኆ ቅዱሳን መጽሐፉ ላይ ስለ ቅድስ እስጢፋኖስ እንዲ ብሎ ተቀኝቷል፦

“ሰላም ለእስጢፋኖስ በኲረ ሰማዕታት
ሊቀ ዲያቆናት ዐምደ ሃይማኖት
ቅድስተ ሥላሴ ዘርእየ በዐይኑ
ወልዱ ለአብ እንዘ ይነብር በየማኑ
ተቃውሞቶ መዋግድ ዘስእኑ
ነባቤ ጥበብ በልሳኑ
ጽጉያተ ወጽዱላተ አቅማኀ ቃሉ
ማዕከለ አይሁድ በውስተ ዐውድ ዘኮነ ሰማዕተ ወልድ”፡፡

(የሰማዕታት መዠመሪያ የዲያቆናት አለቃ፣ የሃይማኖት ምሰሶ፤ የተለየች ሦስትነትን በዐይኑ ያየ፤ የአብ የባሕርይ ልጁ በቀኙ ተቀምጦ ያየ፤ መከራከሩን ሸፋጮች አይሁድ ያልቻሉ በአንደበቱ ጥበብን የሚናገር የቃሉ ፍሬዎችም ብርሃናውያትና ያበቡለት፤ በአይሁድ መኻከል በዐደባባይ ውስጥ የወልድ ምስክርን ኾኖ ለተገኘ ለእስጢፋኖስ ሰላምታ ይገባል) በማለት አወድሶታል።

የሰማዕትነት ሕይወትን በመጀመሩ ስለ ክርስቶስ ፍቅር መራራ ሞትን በመታገሡ ቀዳሜ ሰማዕት ተብሏል፤ የቤተክርስቲያን የመጀመሪያው ሰማዕት ነውና፡፡

“በድንጋይ ተወግረው ሞቱ፥ ተፈተኑ፥ በመጋዝ ተሰነጠቁ፥ በሰይፍ ተገድለው ሞቱ፥ ሁሉን እያጡ መከራን እየተቀበሉ እየተጨነቁ የበግና የፍየል ሌጦ ለብሰው ዞሩ፤”
ዕብራውያን 11፥37

ለእግዚአብሔር ክብር ይሁን!!!
እኛንም በሰማዕቱ ጸሎት ይማረን !!!
አምላክ ከበዓሉ ረድኤት በረከት ያሳትፈን
አሜን!
ተጻፈ:- ጥር 1/2015 ዓ/ም

መ/ር ሚኪያስ ዳንኤል
~•••••••~•••••••~•••••~
“ስለ ሕይወት ቃል ከመጀመሪያው የነበረውንና የሰማነውን በዓይኖቻችንም ያየነውን የተመለከትነውንም እጆቻችንም የዳሰሱትን እናወራለን፤” ፩ኛ ዮሐንስ ፩፥፩!
••••••••••••••••••
የፌስቡክ ፔጃችንን ይቀላቀሉ ፤ ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like, እና Share ያድርጉ :-
~•••••••~•••••••~•••••~
የፌስቡክ ገጽ :- https://www.facebook.com/mikiyas.danail
https://www.facebook.com/profile.php?id=100063973695479
https://www.facebook.com/mikiyas24/
የቴሌግራም ቻናል
: https://t.me/brana_Book
137 viewsMIKIYAS DANAIL, 11:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-09 13:58:37
133 viewsMIKIYAS DANAIL, 10:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-07 06:00:33
45 viewsMIKIYAS DANAIL, 03:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-07 00:30:04 *የክርስቶስ የልደት ቀን የመላው የሰው ዘር የልደት ቀን ነው - the nativity of Christ is the birthday of the whole human race*
°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°
"ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና"
ሉቃስ ፪፥፲፩
ለወልደ እግዚአብሔር ሁለት ልደታት እንዳሉት እናምን ዘንድ ይገባናል ፤ አንዱ ከዘመን ሁሉ አስቀድሞ ከእግዚአብሔር አብ የተወለደው ልደት ነው። ሁለተኛው ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም የተወለደው ልደት ነው ። (ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሳርያ)
"ህፃን ተወለደልን ፣ ወንድ ልጅም ተሰጠን፣ ስሙም ድንቅ መካር ፣ ኃያል አምላክ የሠላም አለቃ የዘላለም አባት ተብሎ ይጠራል።"
ኢሳ ፱÷፮
የጌታችን ልደት የእኛም የክርስቲያኖች ዅሉ ልደት ነው፡፡ ከሦስቱ የቀጰዶቅያ አባቶች (The three Cappadocian Fathers) አንዱ፣ ታላቁ የቤተ ክርስቲያን አባት ሊቁ ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ ይህን ምሥጢር ሲገልጥ ‹‹The nativity of Christ is the birthday of the whole human race – የክርስቶስ ልደት የመላው ሰው የልደት ቀን ነው›› ሲል መስክሯል (Hyman of praise to the mother of God)፡፡
ዓለምን የፈጠረ የሁሉ ማረፊያ ጌታ ፥ ቤት እንደሌለው በጎል (በረት) ተወለደ ።
አረጋዊ መንፈሳዊ
"ዘይስዕሎሙ ለህፃናት ኀደረ ወተገምረ ውስተ ማህፀነ ድንግል። - ህፃናትን በማህፀን የሚፈጥር ጌታ በድንግል ማህፀን አደረ ተወሰነ።" ቅዱስ ያሬድ
ሊቃውንት እንዳስተማሩን እግዚአብሔር አምላክ ዓለምን ከፈጠረበት ጥበቡ ይልቅ ዓለምን ያዳነበት ጥበቡ ይበልጣል፡፡
ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተወለደበት እና ዓለምን ያዳነበት ምሥጢር ከምሥጢራት ዅሉ በላይ ነው፡፡ ይህን ምሥጢር ከማድነቅ ሌላ ሊናገሩት አይቻልም፡፡ ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅም በመገረም ይህን ጥበብ እንዲህ ሲል ይገልጸዋል፤ ‹‹ምን እላለሁ? ምንስ እናገራለሁ? ከዘመን አስቀድሞ የነበረው እርሱ ሕፃን ኾኗልና፡፡ እኔ ፈጽሜ አደንቃለሁ፡፡ ከሰማየ ሰማያት በላይ የሚኾን፣ በዘለዓለማዊ ዙፋን የሚኖር እርሱ በበረት ተጣለ፡፡ ከሥጋዌ አስቀድሞ አይዳሰስ የነበረ አንዱ እርሱ በምድራውያን እጅ ተዳሰሰ፡፡ ኀጢአትን የሚያስተሰርይ እርሱን በጨርቅ ጠቀለሉት፡፡ ይህን ወዷልና፤›› (ሃይማኖተ አበው ዘዮሐንስ አፈ ወርቅ፣ ፷፮፥፲፯)፡፡
የተወለደው ወልደ አብ ወልደ ማርያም፤ የወለደችው ደግሞ ወላዲተ አምላክ። የተወለደው አምላክ ወሰብእ ፤ የወለደችው ፥ ድንግል ወእም ትባላለችና።
"ድንግል ትጸንሳለች ወንድ ልጅም ትወልዳለች፤ አማኑኤልም ብላ ትጠራዋለች።" ኢሳ ፯÷፲፬
ለአምስት ሺሕ አምስት መቶ ዘመን በዓለም ላይ ሠልጥኖ የነበረውን ጨለማ ያስወግድ ዘንድ እግዚአብሔር አምላክ ሰው ኾነ፡፡ ከቅድስት ድንግል ማርያም የተወለደው አማናዊው ብርሃን ፀሐየ ጽድቅ ክርስቶስ በሥጋ ተገለጠ፡፡ ‹‹ብርሃን ዘበአማን ዘያበርህ ለኵሉ ሰብእ ለእለ ይነብሩ ውስተ ዓለም፤ በጨለማ ውስጥ ለሚኖር ሕዝብ ታላቅ ብርሃን ወጣላቸው›› እንዳለ ቅዱስ ኤፍሬም በውዳሴው (ኢሳ. ፱፥፪)፡፡
"በቅዱሳን ላይ የሚያድር እግዚአብሔር እኛን ለማዳን ልዩ ከሆነች ድንግል ሰው ሆኖአልና ኑ ይህን ድንቅ እዩ" ውዳሴ ማርያም ዘረቡዕ
እንኳን ለጌታችን ለመድሃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን ።
መልካም የልደት በዓል !!!
አምላክ ከበዓሉ ረድኤት በረከት ያሳትፈን አሜን!
ተጻፈ:- ታኀሣሥ/28/2015 ዓ/ም
ዋዜማ
መ/ር ሚኪያስ ዳንኤል
~•••••••~•••••••~•••••~
“ስለ ሕይወት ቃል ከመጀመሪያው የነበረውንና የሰማነውን በዓይኖቻችንም ያየነውን የተመለከትነውንም እጆቻችንም የዳሰሱትን እናወራለን፤” ፩ኛ ዮሐንስ ፩፥፩!
••••••••••••••••••
የፌስቡክ ፔጃችንን ይቀላቀሉ ፤ ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like, እና Share ያድርጉ :-
~•••••••~•••••••~•••••~
የፌስቡክ ገጽ :- https://www.facebook.com/mikiyas.danail
https://www.facebook.com/profile.php?id=100063973695479
https://www.facebook.com/mikiyas24/
የቴሌግራም ቻናል
: https://t.me/brana_Book
63 viewsMIKIYAS DANAIL, 21:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ