Get Mystery Box with random crypto!

ብራና ሚዲያ BRANA MEDIA

የቴሌግራም ቻናል አርማ brana_book — ብራና ሚዲያ BRANA MEDIA
የቴሌግራም ቻናል አርማ brana_book — ብራና ሚዲያ BRANA MEDIA
የሰርጥ አድራሻ: @brana_book
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 373

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2023-01-07 00:30:04
57 viewsMIKIYAS DANAIL, 21:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-28 09:30:39
210 viewsMIKIYAS DANAIL, 06:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-28 09:30:13
196 viewsMIKIYAS DANAIL, 06:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-27 22:56:11 #ቅዱሳን_መላእክት እና #አገልግሎታቸው!
•ሀ, ይረዳሉ:~
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
“የፋርስ መንግሥት አለቃ ግን ሀያ አንድ ቀን ተቋቋመኝ፤ እነሆም፥ ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ፤ እኔም ከፋርስ ነገሥታት ጋር በዚያ ተውሁት። ዳንኤል 10፥13

•ለ, ያድናሉ:~
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
“የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፥ ያድናቸውማል።” መዝሙር 33፥7

“ከክፉ ነገር ሁሉ ያዳነኝ መልአክ፥ እርሱ እነዚህን ብላቴኖች ይባርክ፤ ስሜም የአባቶቼ የአብርሃምና የይስሐቅም ስም በእነርሱ ይጠራ፤ በምድርም መካከል ይብዙ።”
ዘፍጥረት 48፥16

•ሐ, ይጠብቃሉ:~
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
“በመንገድ ይጠብቅህ ዘንድ ወዳዘጋጀሁትም ስፍራ ያገባህ ዘንድ፥ እነሆ፥ እኔ መልአክን በፊትህ እሰድዳለሁ።”
ዘጸአት 23፥20

"በመንገድህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላእክቱን ስለ አንተ ያዝዛቸዋልና፤ እግርህም በድንጋይ እንዳትሰናከል በእጆቻቸው ያነሡሃል። መዝሙር 90፥11

•መ, ጾም፣ ፀሎት፣ ምጽዋት ያሳርጋሉ!:~
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
እርሱም ከቤተ ሰዎቹ ሁሉ ጋር እግዚአብሔርን የሚያመልክና የሚፈራ ለሕዝብም እጅግ ምጽዋት የሚያደርግ ወደ እግዚአብሔርም ሁልጊዜ የሚጸልይ ነበረ። ከቀኑም ዘጠኝ ሰዓት ያህል፦ ቆርኔሌዎስ ሆይ የሚለው የእግዚአብሔር መልአክ ወደ እርሱ ሲገባ በራእይ በግልጥ አየው። እርሱም ትኵር ብሎ ሲመለከተው ደንግጦ፦ ጌታ ሆይ፥ ምንድር ነው? አለ። መልአኩም አለው፦ ጸሎትህና ምጽዋትህ በእግዚአብሔር ፊት ለመታሰቢያ እንዲሆን አረገ። ሐዋርያት 10÷1-4

•ሠ, ይባርካሉ:~
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
“ከክፉ ነገር ሁሉ ያዳነኝ መልአክ፥ እርሱ እነዚህን ብላቴኖች ይባርክ፤ ስሜም የአባቶቼ የአብርሃምና የይስሐቅም ስም በእነርሱ ይጠራ፤ በምድርም መካከል ይብዙ።”
ዘፍጥረት48÷16

•ረ, ያጽናናሉ:~
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
“ነገር ግን በእውነት ጽሑፍ የተጻፈውን እነግርሃለሁ፤ በዚህም ነገር ከአለቃችሁ ከሚካኤል በቀር ማንም የሚያጸናኝ የለም።”
ዳንኤል 10፥21

“የመላእክት አለቃ ሚካኤል ግን ከዲያብሎስ ጋር በተከራከረ ጊዜ ስለ ሙሴ ሥጋ ሲነጋገር፦ ጌታ ይገሥጽህ አለው እንጂ የስድብን ፍርድ ሊናገረው አልደፈረም።” ይሁዳ 1፥9

•ሰ, ያማልዳሉ
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
“በዚያም ዘመን ስለ ሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ አለቃ ሚካኤል ይነሣል፤" ዳንኤል 12፥1

“የእግዚአብሔርም መልአክ መልሶ፦ አቤቱ፥ የሠራዊት ጌታ ሆይ፥ እነዚህ ሰባ ዓመት የተቈጣሃቸውን ኢየሩሳሌምንና የይሁዳን ከተሞች የማትምራቸው እስከ መቼ ነው? አለ።” ዘካርያስ 1፥12

★★★
“ጌታ ራሱ በትእዛዝ በመላእክትም አለቃ ድምፅ በእግዚአብሔርም መለከት ከሰማይ ይወርዳልና፥ በክርስቶስም የሞቱ አስቀድመው ይነሣሉ፤” 1ኛ ተሰሎንቄ 4፥16
★★★
ከሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ረድኤት በረከት ይክፈለን፣
ጸሎት፣ ምልጃው፣ ጠብቆቱ አይለየን አሜን!

ተጻፈ:- ታኀሣሥ/18/2015 ዓ/ም
ዋዜማ
መ/ር ሚኪያስ ዳንኤል
~•••••••~•••••••~•••••~
“ስለ ሕይወት ቃል ከመጀመሪያው የነበረውንና የሰማነውን በዓይኖቻችንም ያየነውን የተመለከትነውንም እጆቻችንም የዳሰሱትን እናወራለን፤” ፩ኛ ዮሐንስ ፩፥፩!
••••••••••••••••••
የፌስቡክ ፔጃችንን ይቀላቀሉ ፤ ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like, እና Share ያድርጉ :-
~•••••••~•••••••~•••••~
የፌስቡክ ገጽ :- https://www.facebook.com/mikiyas.danail

https://www.facebook.com/profile.php?id=100063973695479

https://www.facebook.com/mikiyas24/

የቴሌግራም ቻናል
: https://t.me/brana_Book
181 viewsMIKIYAS DANAIL, 19:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-27 22:55:08
178 viewsMIKIYAS DANAIL, 19:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-24 21:39:10
305 viewsMIKIYAS DANAIL, 18:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-16 20:10:35 https://t.me/brana_Book
64 viewsMIKIYAS DANAIL, edited  17:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-12 09:36:06 ስማኝ ልጄ!!!

1. ጠንካራ ሰው ሁን ማለት አትውደቅ ማለት አይደለም ወድቀህ መነሳትንም ልመድ ማለት እንጂ!!!!

2. ዝም በል ማለት አትናገር ማለት አይደለም ሌሎችን ለመስማት ጆሮ ስጥ ማለት እንጂ!!!!

3. ሆዳም አትሁን ማለት አትብላ ማለት አይደለም በሰው ሀቅ አትለፍ ማለት እንጂ!!!!

4. አትቆጣ ማለት ስሜት አይኑርህ ማለት አይደለም ከቁጣ ቶሎ ተመለስ ማለት እንጂ!!!!

5. ይቅርታ አድርግ ማለት አልተጎዳህም ማለት አይደለም በሆድህ ቂም መያዝ ሌላ ጉዳት ስለሆነ እንጂ!!!!

6. ጠላትህን ውደድ ማለት ጠላት ጥሩ ነው ማለት አይደለም ከጥላቻ ይልቅ ፍቅር ስለሚያሸንፍ እንጂ!!!

7. ደስተኛ ሁን ማለት ሁሉ ይኑርህ ማለት አይደለም ባለህ ነገር ደስ ይበልህ ማለት እንጂ!!!!

8. ስራህን ውደድ ማለት የምትሰራው ስራ ጥሩ ነው ማለት አይደለም ነገ ጥሩ ስራ እንዲኖርህ ዛሬ የምትሰራውን ስራ ውደድ ማለት እንጂ!!!!

9. ወረኛ አትሁን ማለት አታውራ ማለት አይደለም ምንም ስለማታውቀው ነገር አታውራ ማለት እንጂ!!!!

10. ትሞታለህ ማለት አትስራ ማለት አይደለም ምንም ቁም ነገር ሳትሰራ አትሙት ማለት እንጂ!!!!

11. ብቸኛ አትሁን ማለት ሮጠህ ትዳር ያዝ ማለት አይደለም ልብህን ግዜህን ያለህን ሁሉ አሳልፈ ለመስጠት ዝግጁ ሁን ማለት እንጂ!!!!

12. እውነተኛ ሁን ማለት ሰዎች ባሉበት ብቻ እውነትተናገር ማለት አይደለም ለራስህም የእውነት ኑሮ ኑር ማለት ማለት እንጂ!!!!

13. አትጣላ ማለት ከሰው ጋር አትኑር ማለት አይደለም ቂም ይዘህ አትቆይ ማለት እንጂ!!!!

14. ኩራተኛ አትሁን ማለት አትዘንጥ ማለት አይደለም ሌሎችን አትናቅ ማለት እንጂ!!!

15. ቆንጆ ነህ ማለት ከሌሎች የተሻልክህ ነህ ማለት አይደለም አምሮብሃል ማለት እንጂ!!!!

16. አዋቂ ሁን ማለት እንደገና ት/ቤት ሂድ ማለት አይደለም ብልህ ሁን ማለት እንጂ!!!
169 viewsMIKIYAS DANAIL, 06:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-12 09:36:05
127 viewsMIKIYAS DANAIL, 06:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-12 09:28:31 ~•የማትፈርሺ መቅደስ ነሽ•~

````````````````````
እግዚአብሔር ያደረባት አማናዊት ቤተ-መቅደስ
#መቅደሲቱ ወደ መቅደስ ገባች፤
#ቅድስቲቱ ወደ ቅድስት ገባች፤
#ክብርቲቱ ወደ ክብርት ቤቷ ገባች፤
#ልዩ_የሆነችው ወደ ልዩ ሥፍራ ገባች፤
#ቅድስተ_ቅዱሳኗ ወደ ቅድስተ ቅዱሳን ገባች፤
#ንጽሕተ_ንጹሐኗ ወደ ንጽሕ አዳራሽ ገባች፤
#ቤተ_መቅደሷ ወደ ቤተ መቅደስ ገባች፡፡ ሊቃውንትም ‹‹መቅደስ ዘኢትትነሠት-የማትፈርሺ መቅደስ ነሽ››

“ልዑል ማደሪያውን ቀደሰ።”
መዝሙር 45፥4
“ኦ ድንግል አኮ በተላህዮ ዘልሕቂ ከመ አዋልደ ዕብራውያን እለ ያገዝፋ ክሣዶን አላ በቅድስና ወበንጽሕ ውስተ ቤተ መቅደስ ነበርኪ…” (ድንግል ሆይ አንገታቸውን እንደሚያገዝፉ እንደ ዕብራውያን ሴቶች ልጆች በዋዛ ያደግሽ አይደለም፤ በንጽሕና በቅድስና በቤተ መቅደስ ኖርሽ እንጂ፤ ድንግል ሆይ ምድራዊ ኅብስትን የተመገብሽ አይደለም፤ ከሰማየ ሰማያት የበሰለ ሰማያዊ ኅብስትን ነው እንጂ፤ ድንግል ሆይ ምድራዊ መጠጥን የጠጣሽ አይደለም፤ ከሰማየ ሰማያት የተቀዳ ሰማያዊ መጠጥን ነው እንጂ፤ ድንግል ሆይ ከአንቺ አስቀድሞ ከአንቺም በኋላ እንዳሉ ሴቶች መተዳደፍን የምታውቂ አይደለም፤ በንጽሕና በቅድስና ያጌጥሽ ነሽ እንጂ፤ ድንግል ሆይ የሚያታልሉ ጐልማሶች ያረጋጉሽ አይደለም የሰማይ መላእክት ጐበኙሽ እንጂ እንደተነገረ ካህናትና የካህናት አለቆች አመሰገኑሽ እንጂ)
[ሊቁ አባ ሕርያቆስ በቅዳሴ ማርያም]

የሰው ዘር እግዚአብሔር በጸጋ የሚያድርበት መቅደስ ይባላል፤ “የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እንደ ሆናችሁ የእግዚአብሔርም መንፈስ እንዲኖርባችሁ አታውቁምን?” 1ኛ ቆሮንቶስ 3፥16 እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ደግም፤ እግዚአብሔር ያደረባት አማናዊት ቤተ-መቅደስ ትባላለች።

"እግዚአብሔር ጽዮንን መርጦአታልና፥ ማደሪያውም ትሆነው ዘንድ ወድዶአታልና፥ እንዲህ ብሎ፦ ይህች ለዘላለም ማረፊያዬ ናት፤ መርጫታለሁና በዚህች አድራለሁ። መዝ 131÷13

“እኛ የሕያው እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ነንና”
2ኛ ቆሮ 6÷16

ከወላዲተ አምላክ ረድኤት በረከት ይክፈለን፣
ፍቅሯን በልባችን፣ ጣዕሟን በአንደበታችን ያሳድርብን፤
ጸሎት ምልጃዋ አይለየን አሜን!

ተጻፈ:- ታኀሳስ/02/2015 ዓ/ም
መ/ር ሚኪያስ ዳንኤል
~•••••••~•••••••~•••••~
“ስለ ሕይወት ቃል ከመጀመሪያው የነበረውንና የሰማነውን በዓይኖቻችንም ያየነውን የተመለከትነውንም እጆቻችንም የዳሰሱትን እናወራለን፤”
፩ኛ ዮሐንስ ፩፥፩!
••••••••••••••••••
የፌስቡክ ፔጃችንን ይቀላቀሉ ፤ ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like, እና Share ያድርጉ :-
~•••••••~•••••••~•••••~
የፌስቡክ ገጽ :- https://www.facebook.com/mikiyas.danail

https://www.facebook.com/profile.php?id=100063973695479

https://www.facebook.com/mikiyas24/

የቴሌግራም ቻናል : https://t.me/brana_Book
121 viewsMIKIYAS DANAIL, 06:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ