Get Mystery Box with random crypto!

ብራና ሚዲያ BRANA MEDIA

የቴሌግራም ቻናል አርማ brana_book — ብራና ሚዲያ BRANA MEDIA
የቴሌግራም ቻናል አርማ brana_book — ብራና ሚዲያ BRANA MEDIA
የሰርጥ አድራሻ: @brana_book
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 373

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2022-12-12 09:28:27
125 viewsMIKIYAS DANAIL, 06:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-11 20:40:58
155 viewsMIKIYAS DANAIL, 17:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-08 20:22:31
92 viewsMIKIYAS DANAIL, 17:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-08 20:22:28
88 viewsMIKIYAS DANAIL, 17:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-08 12:32:24 https://t.me/+VYtQE4hmpfQMI1DD
141 viewsMIKIYAS DANAIL, 09:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-05 00:00:33
63 viewsMIKIYAS DANAIL, 21:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-05 00:00:25 +++ እስራኤልን የሚያድን አዳኝ +++
መጽሐፍ ቅዱስ "እስራኤልም ወደ እግዚአብሔር ጮኹ እግዚአብሔርም የሚያድናቸው አዳኝ የካሌብን የታናሽ ወንድሙን የቄኔዝን ልጅ ጎቶንያልን አስነሣላቸው።" ይላል። (መሳ: 3:9) መስፍኑ ጎቶንያል እግዚአብሔር ያስነሥሣው አዳኝ የሚያድን መባሉን ትመለከታላችሁን? ማዳን የማነው? የእግዚአብሔር ! መስፍኑ ጎቶንያልን የሚያድን አዳኝ አድርጎ ያስነሣው ማነው? እግዚአብሔር! ጎቶንያል የሚያድን አዳኝ መባሉ የእግዚአብሔርን አዳኝነት ያስተሐቅራልን? በፍጹም! ታድያ ድንግል ማርያምን በጸጋ የተሞላች መድኃኒት ክርስቶስን የወለደች በጀርባዋ ያዘለች ጡቶቿንም ያጠባች በማዳኑም ጉዞ ያልተለየች የደስታ መፍሰሻ ምክንያተ ድኂንም በመሆኗ የምታድን አዳኝ ብንላት ችግሩ ምንድነው? ከጎቶንያል የሚልቅ ጸጋ አልተሰጣትምን? እርሷ መድኃኒት ቤዛ የምታድን መባሏን የምትቃወሙ መጽሐፍ ቅዱስ ሙሴን ቤዛ ጎቶንያልን አዳኝ የሚያድን ሲልስ ምን ትሉ ይሆን? ስህተት ነውን?

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ደቀመዝሙሩ ጢሞቴዎስን "ለራስህና ለትምህርትህ ተጠንቀቅ በእነዚህም ጽና ይህን ብታደርግ ራስህንም የሚሰሙህንም ታድናለህ።" በማለት ይመክረዋል:: (1ጢሞ 4:16) ጢሞቴዎስ ታድናለህ ሲባል ማንን ነው የሚያድነው? ሰዎችን አይደለምን? እንዴት ነው የሚያድነው? በእምነት የሚያጸና በምግባር የሚያቀና መልካም አኗኗርን እንድንኖር የሚያደርግ ለመንግሥተ ሰማያት የሚያበቃ ትምህርት በማስተማር አይደለምን? ሰዎችን ወደ መድኃኒት ክርስቶስ በትምህርትም በኑሮም የሚመሩ አዳኞች የሚያድኑ ታድናላችሁ አድኑ ተባሉ::

ሐዋርያትን ጌታችን ወደ ዓለም ሲልካቸው በሰጣቸው የማዳን ጸጋ ሰዎችን ከርኩሳን መናፍስት ከእኩያን አጋንንት እንዲታደጉ እንዲያድኑ በማዘዝ ነው "ሂዱ አጋንንትን አውጡ ሕሙማንን ፈውሱ(አድኑ)።" እንዲል:: (ማቴ 10:8) በዚህ ሐዋርያዊ ተልእኳቸው በደዌ ሥጋ በአጋንንት እስራት የተያዙትን በተአምራት በደዌ ነፍስ በኃጢአት የተያዙትን በትምህርት አድነዋል:: እንደ እነርሱ ያሉ የእነርሱን ፍኖት የተከተሉ እውነተኞች ቀሳውስትም በጸሎታቸው የተቀደሰውን ቅብአት እየቀቡ ስመ እግዚአብሔርን እየጠሩ በደዌ ሥጋ በደዌ ነፍስ(በኃጢአት) የተያዙትን እንዲያድኑ ታዘዋል በዚህም የሚያድኑ ተብለዋል። ( ያዕ 5:14-15)

++እግዚአብሔር ሕይወትን ለማዳን ከናንተ በፊት ሰድዶኛል +++ ቅደስ ዮሴፍ
(ዘፍ 45:5))

ዮሴፍ የንጽሕና ምሳሌ ነው:: የጴጥፋራ ሚስት ለኃጢአት ብትጋብዘው እምቢ ብሏታልና:: (ዘፍ 39:7-17)

ዮሴፍ ይቅርታ የማድረግ ምሳሌ ነው በከንቱ የጠሉትን ለእስማኤላውያን በሃያ ብር የሸጡትን በጉድግጓድ የጣሉትን ወንድሞቹን ሊበቀል እየቻለ ይቅርታ አድርጎላቸዋልና:: (ዘፍ 45:1)

ዮሴፍ የበረከት ምክንያት ነው "እግዚአብሔር የጴጥፋራን ቤት ውስጡንም ውጭውንም ስለ ዮሴፍ ባረከው የእግዚአብሔርም በረከት በውጭም በግቢም ባለው ሁሉ ላይ ሆነ።" እንዲል (ዘፍ 39:5) በዚህም " የጻድቅ መታሰቢያ ለበረከት ነው።"፤ "በረከት በጻድቅ ራስ ላይ ነው" ፤ "በጻድቃን በረከት ከተማ ከፍ ከፍ ትላለች" የሚሉትም ቃላት እውነተኞች መሆናቸውን አወቅን:: (ምሳ 10:6፣10:7፣ 11:11) ዮሴፍ ከተደረገበት ነገር አንዱ በክፋት አንዳች ክፉ ሳይገኝበት በገዛ ወንድሞቹ በከንቱ መጠላቱ ከዚያም ባለፈ መጀመርያ ለእስማኤላውያን ነጋዴዎች ኋላም ለግብፃውያን መሸጡ ነው:: ዮሴፍ ወንድሞቹ ከሸጡት በኋላ ብዙ ፈተናዎችን አልፎ እግዚአብሔር ረድቶት ምሥጢርን ገልጦለት በግብጽ ቤተ መንግሥት ታላቅ ለመባል በቃ:: ዓለም በሙሉ እህል ፍለጋ ከረጢቱን ይዞ ወደ እርሱ ተመመ:: ወንድሞቹም መጡ በክፋት ሳይጠላቸው ሊበቀላቸው እየቻለ ሳይበቀላቸውም "እኔን በመሸጣችሁ አትዘኑ እግዚአብሔር ሕይወትን ለማዳን ከናንተ በፊት ሰድዶኛልና።" አላቸው ይላል መጽሐፍ ቅዱስ:: (ዘፍ 45:5) "እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ድንቅ ነው" እንዲልም እግዚአብሔር ማዳን እየተቻለው ፈቃዱን የፈጸሙ ቅዱሳኑን ምክንያት አድርጎ ማዳኑን እንደሚፈጽም ከዚህ ታሪክ እንማራለን:: (መዝ 67:35) ዮሴፍ "ሕይወትን ለማዳን ተላክሁ።" እንዳለ አትሰሙምን ? ዮሴፍ እኮ የእግዚአብሔር ሕይወትን ለማዳንም የላከው እግዚአብሔር ነው:: እነሆ ከዮሴፍ የምትበልጥ ከዚህ አለች እርሷ የዮሴፍን የአብርሃምን ፈጣሪ ክርስቶስን የወለደች ናትና:: (ሉቃ 1:28) የዮሴፍን ፈጣሪ ክርስቶስን የወለደች ብርሃን የወጣባት ምሥራቅ ናትና:: (ኢሳ 9:2 :6 ዮሐ 4:12-15) በረከትን የሚያድል የበረከት አባት ክርስቶስን ወልዳለችና። (ሉቃ 2:1-15) "ዮሴፍ ሕይወትን አዳነ" ብሎ መጽሐፍ ከነገረን እመቤታችን በተሰጣት ጸጋ ሕይወታችንን ከመተተኞችና ከክፉዎች ታድናለች ብንል ችግሩ ምንድነው?

ሰዎቹ ተሸክመውት ያለውን መጽሐፍ አያስተውሉትም እንጂ ቅዱሳን ሐዋርያት "እንዲሁ ጌታ እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ ለማዳን ትሆን ዘንድ ለአሕዛብ ብርሃን አድርጌሃለው ብሎ አዞናል።" ብለው የተልእክኳቸው ዓላማ ምን እንደሆነ እንደተናገሩ ይመሠክርላቸዋል። (የሐዋ 13:47) ሐዋርያት ለምን ወደ ዓለም ተላኩ? ሰዎችን የክርስቶስን ቃል አስተምረው መክረውና ገሥጸው በትምህርታቸው ለክብር ለማብቃት ነው:: በዚህም "ለማዳን የተላኩ" "ብርሃናት" ተባሉ። (ማቴ 10:1-16) ሐዋርያት ለማዳን ተልከናል ሲሉ ራሳቸውን ከክርስቶስ ጋር እያፎካከሩ ነውን ? አይደለም !! ቅዱሳን እንዲሁም እመቤታችን "መድኃኒት ቤዛ የሚያድኑ ለማዳን የተላኩ " ለምን እንደተባሉ መርምሮ በቀና አእምሮ መረዳት መልካም ነው ::

የእናቱ የእመቤታችን አማላጅነት የልጇ ቸርነት አይለየን !!

ቢትወደድ ወርቁ
ኅዳር 23 ቀን 2015 ዓ.ም
54 viewsMIKIYAS DANAIL, 21:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-05 00:00:24 +++ እርሷ መድኃኒታችሁ ናትና!!" +++

(በትዕግሥት ሆነው ያንብቡት፣ ለሌላውም በማጋራት ሃይማኖታዊ ግዴታዎን ይወጡ)

ከጻድቁ አቡነ ተክለሃማኖት በረከት ያሳትፈን!!

ላለመማርና ላለማወቅ አእምሯቸውን አሳልፈው የሰጡ ኦርቶዶክሳዊነትንና ኦርቶዶክሳውያንን አምርረው የጠሉ ሰዎች "ድንግል ማርያም ምክንያተ ድኂን እንጂ መድኃኒት አትባልም" ሲሉ ለይቶላቸው ጸረ ማርያም የሆኑቱ ደግሞ ጥቅሶችን ከዓውድና ከተነገሩበት ዓላማ ውጭ በመጥቀስ "ማርያምን መድኃኒት ቤዛ አድኝን" አትበሏት ብለው በአፍም በመጽሐፍም ይናገራሉ:: ኦርቶዶክሳውያን ድንግል ማርያምን "መድኃኒት፣ ቤዛ" ብለን ስንጠራት በውስጥም በአፋ ያሉ ብዙዎች ባልተረዱት ባላወቁት ባልመረመሩት ነገር እርሷን ከልጇ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ያተካከልናት በእርሱ የማዳን ዙፋን ያስቀመጥናት አድርገው ያስባሉ ይናገራሉም:: ከዚያም አልፈው በክርስቶስ የማዳን ሥራ ላይ የተንሸዋረረ እውቀትና እምነት እንዳለን አድርገው በሌሎች ዘንድ ያጠለሹናል:: ኦርቶዶክሳውያን ያዳነን ማን እንደሆነ ከምን እንዳዳነን ለምን እንዳዳነንና በማዳኑም ሥራ ውስጥ ማዳኑ የተፈጸመለት የሰው ልጅ ሱታፌና ድርሻ ምን መሆን እንደሚገባው ቤተክርስቲያን ታስተምረናለች:: ድንግል ማርያምና ቅዱሳኑን በመንቀፍና በመጥላት ስለ እነርሱም ላለመናገር ዳተኛ በመሆን ለክርስቶስ ያለኝን "ፍቅር" እገልጻለሁ ብሎ መድከም ምንኛ አለመታደል ነው ? ዋናዎቹ ተቃዋሚዎች የ"ፓስተሮቻቸውን የ"መጋቤዎቻቸውን" የ"ነቢያቶቻቸውን" የ"ያድናሉ" መልእክት በፖስተር በብሮሸርና በትላልቅ " ባነሮች" እየለጠፋ ወደ የመስብሰቢያ አዳራሾቻቸው ሰዎችን ይጋብዛሉ : በየጉባኤዎቻቸውም የሚያምኑበትን የራሳቸውን ትምህርት ከማስተማር ይልቅ ኦርቶዶክሳዊነትን እያጨለሙና እያጠለሹ የሌለ ስም እየሰጡ ይሰብካሉ :: ኢየሱስ ክርስቶስ ከምንና ለምን አዳነን? እርሱ ካዳነን ከእኛ ምን ይጠበቃል? የሚሉትን ሀሳቦች ማየቱ እጅግ ሰፊ በመሆኑ ለጊዜው አቆይተነው ወደ ነጥባችን እንመለስ :-

+++ ድንግል ማርያም መድኃኒት አትባልምን ? +++

መልሱ ግልጽ ነው::መድኃኒት ትባላለች:: እርሷ መድኃኒት ማለታችን ግን ከክርስቶስ ጋር አስተካከልናት ማለት አይደለም ሊሆንም አይችልም::በመጽሐፍ ቅዱስ ክርስቶስ ብርሃን ተብሏል ቅዱሳንም ብርሃን ተብለዋል:: (ማቴ 5:14 ዮሐ 5:38፣ 8:12) እናስተውል እርሱን ብርሃን ስንለውና እነርሱን ብርሃናት ስንላቸው አንድ አይደለም:: እርሱን ብርሃን ስንለው ቃሉ እንደ አምላክነቱ ይረቃል ይመጥቃል ይረቃልም:: እነርሱን ብርሃናት ስንላቸውም እንደ ማዕረጋቸው እንደ ቅድስና ደረጃቸው ነው። (ማቴ 13: 8 1ቆሮ 15:41) ያ ባይሆን ቅዱስ መጽሐፍ ክርስቶስንም ብርሃን አገልጋዮቹንም ብርሃን በማለቱ እርሱንና ቅዱሳኑን አፎካከረ ያሰኝ ነበር:: ወዳጆቹን ብርሃናት ማለት የእርሱን ብርሃንነት መካድ አይደለም:: እርሱ እንደውም የብርሃናት (የቅዱሳን) አባት ተብሏል:: (ያዕ 1:17) ይህን እንደ መነሻ ካልን እርሷ መድኃኒት መባል እንደሚገባት መጽሐፍ ቅዱስን መሠረት አድርገን በንጽጽር እንመልከት::

+++ ቤዛ እስራኤል ቤዛዊተ ዓለም +++

በብሉይ ኪዳን እስራኤል ዘሥጋን ከግብጽ ባርነት ነጻ ያወጣ በጸናች እጅ በተዘረጋችም ክንድ ለሕዝቡ ቤዛ የሆነ ጠላቶቻቸውን የጣለ እርሱ እግዚአብሔር ነው::እግዚአብሔር ሕዝቡን ከባርነት ነፃ ሲያወጣ ነፃ ካወጣቸውም በኋላ የነፃነት ጉዞ ሲያደርጉ መላእክት ቀን በደመና ሌሊት በብርሃን እንደሚመራቸው ተነግሯቸው ነበር:: (ዘጸ 14:19 ዘጸ 23:20) በዚህ ነጻ የመውጣት ጉዞ ውስጥ ታላቅ ሚናና ድርሻ የነበረው ሰው መስፍኑ ሊቀ ነቢያት ሙሴ ነበር :: ሕዝቡን ይመራና ያስተዳድር ስለእነርሱም ራሱን አሳልፎ ሰጥቶ ነበር:: (ዘጸ 32:32) በዚህም ምክንያት የእግዚአብሔር የሆኑት እስራኤላውያን "የሙሴ ሕዝብ" ሲባሉ ሙሴም በፈጣሪው "የሕዝቡ ነፃ አውጪ" ተብሏል:: (ዘጸ 32:7-8) እስራኤል እግዚአብሔርን ባሳዘኑት ጊዜ ሙሴ ስለ እነርሱ በእግዚአብሔር ፊት ባይቆም ኖሮ ያጠፋቸው ነበር:: (መዝ 105:23) ከዚህ ሁሉ የተነሳ እግዚአብሔር ሙሴን ምክንያት አድርጎ ሕዝቡን ከባርነት ነጻ ስላወጣቸው ሙሴ "የእስራኤል ነፃ አውጪና ቤዛ" ተብሏል:: (ዘጸ 32:7-8፣ የሐዋ 7:35) ይህንም መጽሐፍ ሲመሠክር " ይህ ሰው (ሙሴ) በግብጽ ምድርና በኤርትራ ባሕር በምድረ በዳም አርባ ዓመት ድንቅና ምልክት እያደረገ አወጣቸው" ብሏል :: (የሐዋ 7:36)

እስቲ ጥያቄ እናንሣ እስራኤልን ነፃ ያወጣ ማነው? ሙሴ እንዴት ነፃ አውጪ ተባለ? የእስራኤል ቤዛ ማነው? ሙሴ እንዴት የእስራኤል ቤዛ ተባለ? እስራኤል የማን ሕዝብ ናቸው? የእግዚአብሔር የሆኑት ሕዝቡ እንዴት የሙሴ ሕዝብ ተባሉ? ሙሴ በሕዝቡ መካከል ድንቅና ምልክት ካደረገ "ወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያም ድንቅና ምልክቶችን አድርጋለች።" ተብሎ ሲነገር "ይህማ አይሆንም!" ብሎ ሽንጥ ገትሮ መከራከርን ምን አመጣው? (ማር 16:17 ዮሐ 14:15 ::) በሐዲስ ኪዳን ግብጽ የሲኦል እስራኤላውያን የምእመናነ ሐዲስ ጉዟቸው የጉዟችን የገጠሟቸው ፈተናዎች የፈተናዎቻችን ምሳሌዎች እንደሆኑ ተነግሮናል:: (1ቆሮ 10:1-5) በሙሴ ምስፍና እግዚአብሔር ሕዝቡን ከግብጽ ባርነት ነፃ እንዳወጣ ከእርሷ ከድንግል ማርያም በነሳው (በተዋሐደው) ሥጋ እኛን ከሰይጣን አገዛዝ ከሲኦል ባርነት ነፃ አውጥቶናል:: (ዕብ 2:14-16 1ጴጥ 3:19 ዮሐ 1:14-15) በሙሴ ተልእኮ እስራኤል ከግብጽ ወጡ ከድንግል በነሳው ሥጋ ዓለም ከሲኦል ነፃ ወጣ:: በሙሴ ተልእኮ ፈርኦን ተሸነፈ ከድንግል በተዋሐደው ሥጋ በፈጸመው የማዳን ሥራ ዲያብሎስ አፈረ በመስቀሉም ተጠረቀ:: (ቆላ 2:14-16) እስራኤል ከሥጋ ባርነት ከፈርኦን አገዛዝ ነፃ ከወጡበት መንገድ ዓለም ከነፍስ ባርነት ከሰይጣን አገዛዝ የዳነበት መንገድ ይበልጣል :: በእርሱ ምክንያት በተፈጸመው እስራኤልን ነጻ የማውጣት ጉዞ ሙሴ ቤዛ ነጻ አውጪ ከተባለ በድንግል ማርያም በተፈጸመው የማዳን ሥራ ቤዛዊተ ዓለም ብትባል ምን ያንስባታል? እራሷ " ብርቱ የሆነ እርሱ በእኔ ታላቅ ሥራ ( ማዳኑን ) አድርጓልና።" እንዳለች (ሉቃ 1:49-50)

+++ እርሷ መድኃኒታችሁ ናት +++

በተአምረ ማርያም መቅድም ከሠፈሩ እመቤታችንን እንድንወዳት ከሚያስገነዝቡን ኃይለ ቃላት አንዱ "ውደዷት እርሷ መድኃኒታችሁ ናት" ይላል:: እንግዲህ ይህን አንብበው ነው ሰዎቹ ለምን እንዲህ ትላላችሁ ብለው እንደ ጥህሎ ሊውጡን እንደ እንቀት ሊጠጡን የሚነሥሡብን ሳይመረምሩና ሳይገነዘቡም የሚተቹን :: እነዚህ ክፍሎች እርሷን እንዴት መድኃኒት ትሏታላችሁ? ብለውም ጉንጭ አልፋ መከራከርያ ያነሣሉ:: እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ መድኃኒት አዳኝ ነው:: ማዳን የባሕርይው የሆነ እርሱ የወደዳቸውን በፍጹም ልባቸው ያመለኩት ወዳጆቹን ምክንያት አድርጎ በልዩ ልዩ መንገድ ማዳኑን ስለገለጠባቸው መድኃኒት አዳኝ እንዲባሉ ፈቀደ ያድኑም ዘንድ የማዳኑን ጥበብ ገለጠላቸው ኃይሉንም አስታጠቃቸው መንገዳቸውንም አቃና:: እስቲ የሚከተሉትን ለግንዛቤ እንመልከት
42 viewsMIKIYAS DANAIL, 21:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-05 00:00:22
47 viewsMIKIYAS DANAIL, 21:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-04 23:43:25

54 viewsMIKIYAS DANAIL, 20:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ