Get Mystery Box with random crypto!

አንሙት አብርሃም

የቴሌግራም ቻናል አርማ animutabraham — አንሙት አብርሃም
የቴሌግራም ቻናል አርማ animutabraham — አንሙት አብርሃም
የሰርጥ አድራሻ: @animutabraham
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.51K

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2023-03-16 20:30:29 በአዲስ አበባ የሚገኙ #የባጃጅ ሹፌሮች የተነጠቋቸው መብቶች ምንድን ናቸው?

ከየካቲት 30/2015 ጀምሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባለሦስት እና አራት እግር (ባጃጅ) አነስተኛ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ተሽከርካሪዎች ላይ እገዳ ማስቀመጡ ቀጣዮቹን መብቶች ስለመጣሱ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮምሽን አሳስቧል።

*መንግሥት ሰዎች ሥራቸውን እና የመረጡትን መተዳደሪያ ያለአግባብ እንዳያጡ ማድረግን ጨምሮ የመረጡትን እና የተቀበሉትን ሥራ እንዲሠሩ የማስቻል ኃላፊነት አለበት።

*በኢትዮጵያ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 41(1) መሠረት “ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በሀገሪቱ ውስጥ በማንኛውም የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የመሰማራት እና ለመተዳደሪያው የመረጠውን ሥራ የመሥራት መብት አለው

* በህገመንግስቱ አንቀጽ 41 በንዑስ-አንቀጽ 2 እንደተመለከተው መተዳደሪያውን፣ ሥራውን እና ሙያውን የመምረጥ መብት አለው። ይህ መተዳደሪያን የመምረጥ/በመረጡት ሥራ የመሰማራት መብት (the right to choose one’s livelihood/work) ኢትዮጵያ ባጸደቀቻቸው የተለያዩ ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ሰነዶችም የተረጋገጠ መብት ነው፡፡

* የሕገ-መንግሥቱ አንቀጽ 41(6) እንደሚደነግገው መንግሥት ለሥራ አጦች እና ለችግረኞች ሥራ ለመፍጠር የሚያስችል ፖሊሲ የመከተል፤ በሚያካሂደው የሥራ ዘርፍ ውስጥ የሥራ ዕድል ለመፍጠር የሥራ ፕሮግራሞችን የማውጣት እና ፕሮጀክቶችን የመቅረጽ ግዴታ አለበት።

*የዚሁ አንቀጽ ንዑስ-አንቀጽ 7 ደግሞ መንግሥት ዜጎች ጠቃሚ ሥራ የማግኘት ዕድላቸው እየሰፋ እንዲሄድ ለማድረግ አስፈላጊ እርምጃዎችን መውሰድ እንዳለበት ይደነግጋል።

* ሕገ-መንግሥቱ በምዕራፍ አስር ከተካተቱት የብሔራዊ ፖሊሲ መርሆችና ዓላማዎች መካከል ስለኢኮኖሚ ነክ ዓላማዎች በሚደነግገው በአንቀጽ 89(2) ላይ መንግሥት የኢትዮጵያውያንን የኢኮኖሚ ሁኔታዎች ለማሻሻል እኩል ዕድል እንዲኖራቸው ለማድረግ ሁኔታዎች የማመቻቸት ግዴታ እንዳለበት ይገልጻል። የዚሁ አንቀጽ ንዑስ-አንቀጽ 8 ደግሞ መንግሥት የሠራተኛውን ሕዝብ ጤንነት፣ ደኅንነት እና የኑሮ ደረጃ ለመጠበቅ መጣር እንዳለበት ይገልጻል።

Ethiopian Human Rights Commission
299 views17:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-16 08:32:34
444 views05:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-16 08:32:29 አስተዳደራዊ ድክመት የፈጠረው  የንግግር ለከት ማጣት ሀገርን የከፋ ቀውስ ውስጥ ይከታል !

       በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከእናት፣ መኢአድ እና ኢሕአፓ ፓርቲዎች የተሰጠ መግለጫ
ከቦታ ቦታ የመንቀሳቀስ አልፎም በመረጡት ቦታ የመኖር የሠው ልጅ ማንም ሊሠጠው እና ሊነሣው የማይችል የተፈጥሮ ሥጦታ   ከመሆኑም በተጨማሪ  በሕገ መንግሥቱ ለዜጎች የተሰጣቸው መብት እንጂ አንዳንድ ባለስልጣናት ደስ ሲላቸው የሚቸሩት ካልፈለጉ ደግሞ የሚነፍጉት ጉዳይ አይደለም።
ከአማራ ክልል ወደ አዲስ አበባ በሚጓዙ መንገደኞች ላይ ህፃናትን , ታማሚዎችን , እናቶቻችን, አቅመ ደካማ የሆኑ አባቶችን ,  የሃማኖት አባቶችን  ጨምሮ በተለያዩ ጊዜያት ሰበባ ሰበብ እየተፈለገ ሲፈጸም የነበረው ድብደባ   ማዋከብ፣ እንግልትና ማጉላላት, መሠወር  ከነገ ዛሬ መሻሻል ይታይበታል ተብሎ ተስፋ ሲደረግ ይባስ ብሎ “ከአንዳንድ ክልሎች ወደ አዲስ አበባ የሚደረገው ከፍተኛ ፍልሰት መንግሥትን በመጣል በኃይል ስልጣን ለመቆጣጠር ያለመ ነው” በሚል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አበቤ በቀን 05/07/2015 ዓ.ም ለምክር ቤት ባቀረቡት ሪፖርት ላይ የገለጹበት መንገድ ያለፈውን ስህተት ከማረም ይልቅ የዜጎችን ከቦታ ቦታ የመንቀሳቀስ መብት የሚነፍግ ከመሆኑም በላይ አንዱ በዓንዱ ጥርጣሬን ፈጥሮ እንዲነሣ በማድረግ የቀጠለውን ማንነትን መሠረት ያደረገ  የዘር ምንጠራ  በከፍተኛ ሴራና ፍረጃ ለበለጠው  ፍጅት የሚያመቻችና ዜጎችን ማግለልና የማሸማቀቅ አካል በመሆኑ ግልፅ ሰዓብዊ መብት ጥሰት ነው።
በሌላ በኩል ትናንት የሃማኖት መሪን በጠራራ ፀሃይ የደንብ ልብሥ የለበሡ የሥርዓቱ ህግ -አሥከባሪ መሠል ፖሊሦች  በጥፊ ሲመቱ፣ ሕጻናትንና ሴቶችን ሲያዋክቡና በማንነታቸው ሲያሸማቅቁ፣ ሲገድሉና ሲዘርፉ ለኖሩ ኃይሎች ሽፋን የመስጠትና ጥብቅና የመቆም አካል አድርገን እንወስደዋለን።
የክሩን ጫፍ ከተከተልነው ደግሞ እኩይ ድርጊቱ በኦሮሚያ ብልጽግና በንግግርም በተግባርም በተጠናና መዋቅራዊ በሆነ ኹኔታ እንደሚፈጸም መሠረታዊ  ማረጋገጫና በቀጣይም ሰቆቃና ማወከቡ ቢብስ እንጂ እንደማይረግብ ጉልህ ማሳያ ነው።

ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ አዲስ አበባ እንዳይገቡ የሚከለከሉ ዜጎቻችን ጉዳይ የሌላ ሀገር ድንበር አቋርጠው በሕገወጥ መንገድ ለመግባት የሚሞክሩ መንገደኞች እንጂ ከሀገራቸው አንድ ክፍል አባቶቻቸው ወደ አቀኑላቸው ዋና ከተማቸው የሚደረግ ሕጋዊ እንቅስቃሴ አይመስልም።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከዓለም በድፕሎማቲክ ከተማነት በመጀመሪያዎቹ ረድፍ የምትጠቀስ፣ በሰላሟ የሚቀናባትን ከተማ በምዝበራና ወረራ እንድትጠቀስ፣ ነዋሪዎቿን በኑሮ ውድነት የምትጠብስ፣ ሌብነትና ሙሥና  ሕጋዊ ሆኖ እግር አውጥቶ የሚሄድባት፣ የአፍሪካና የመላ ጥቁር ሕዝብ ድልና ኩራት የሆነው አድዋ በባለቤቱ ሕዝብ የማይከበርባት፣ ጤፍ ብርቁ፣ ሲሚንቶ ብርቁ፣ ስኳር ብርቁ፣ የምሥኪን ዜጎቿን ጎጆ በግብታዊነትና ዘረኝነት በወለደው የጥላቻ ቋሚ  ስካር የምታፈርስ ወደ ማድረግ አዘቅት መምራቱ ሳያንስ የንግግር ለከት ማጣቱና በጽንፈኛ ኃይሎች የተጻፈን ስክሪፕት(Script) በመንግሥት መዋቅር፣ በተከበረ ምክር ቤት ፊት አምጥቶ ማነበነብ እጅጉን ያሥቆጫል ያሣዝናልም ።
ምን አልባት ከዚህ ጀርባ ተስፋ መቁረጥ፣ በኢትዮጵያ ፍርስራሽ ላይ ቁርጥራጭ ሀገር የመገንባት ቅዠት፣ ከተማዋን ጥቅም አልባ የማድረግ ቀጣይ ፕሮጀክት፣ አፋርን , ሡማሌን ፣ አማራንና ትግራይን ከአዲስ አበባ የመነጠል፣ ለጥፋቱና ለአጥፊዎች ሽፋን የመስጠት አካሄድ ይመስለናል።
በሌላው ዓለም ቢሆን እንዲህ ያሉ እጅግ መርዘኛና ፍጅት ቀስቃሽ(genocidial motivetor speach)  ንግግሮችና ተናጋሪዎች ተገቢው እርምት በቶሎ በተሰጣቸው ነበር።
በእኛ ሀገር ኹኔታ ሕጋዊነት ሳይሆን ሕገ ወጥነት፣ “የእኛ” ሳይሆን “ለእኔ ብቻ” ባዮች፣ ተጠያቂነት ሳይሆን የተረኝነት መንፈሥ  የሰፈነበት አሠራር  በመሆኑ ለዚህ አልታደለንምና የኢትዮጵያ ሕዝብ በአንድነት ህግ ንና ሥርዓት ሠፍነኖ  አጥፊዎች የፍትህ ደጃፍን እንዲያዮ  ሁሉም በህግ ፊት እኩል መሆኑንም አውቀው የአገሪቱ ሠላም, አንድነት እና ሉዓላዊነት ማሥከበር የሁላችንም ግዴታ ሥለሆነ ጥሪያችን  እናቀርባለን።
ፈጣሪ ሀገራችን ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ይጠብቅ
ኢሕአፓ፣ እናት ፓርቲ፣ መኢአድ
መጋቢት 6 ቀን 2015 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
431 views05:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-16 08:32:22
389 views05:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-14 21:09:34 የኢትዮጵያ አዙሪት እና የአማራ ፍዘት!?
(አንሙት አ.)

አስተማሪዬ ሀብታሙ አለባቸው "ታላቁ ተቃርኖ" ባለው መፅሐፉ፥ አፄ ኃይለሥላሴ፡ ኤርትራን ከቅኝ ግዛት ነፃነት በኋላ ወደኢትዮጵያ ለማካተት መሥራታቸው፡ በአፄ ምኒልክ ዘመን የተጠቃለለውን የstate formation ሒደት ወደኋላ የመመለስ እርምጃ እንደነበር ያወጋል።

ደርግ ያንን state ለማስከበር "በአቢዮታዊት እና አንዲት ኢትዮጵያ" ሲምልና ሲታክት ከርሞ አሸለበ። በወያነ/ኢሕአዴግ ደግሞ የኢትዮጵያ state formation ጉዳይን እንደገና በማንሳት፤ ኤርትራ መልሳ የተሸኘችባት እና በውስጧ ደግሞ የራስ-በቅ ግዛተ-መንግስቶች አገር ለማድረግ ደከመ። "አዲስቷ ኢትዮጵያ" እያለ ሲያንቆለጳጵሳት ከርሞ ከመንበሩ ዘወር አለ።

በዚህ የኢትዮጵያ state formation ጉዳይ፡ ከዜሮ የመጀመር ልማድ ስለተጣባን፥ አሁን እድል አግኝተናል የሚሉት የኦሮሞ ልሒቃንም የፈረደበትን የኢትዮጵያን state formation መልሰው አንስተው እያመነዠጉት ነው። ወደኋላ 150 ዓመት መልሰን እንሥራው ብለው ተነስተዋል። (500 ቢያደርጉት ምን ፈርተው ይሆን!? )

የአሁኖቹ የሚለየው በstate formation ላይ የያዙት አላማ ከኢትዮጵያ ይልቅ በኦሮሚያ state formation ላይ ትኩረት ማድረጉ ነው። ሌሎችን ኢትዮጵያውያን እና የአገር-ግዛቶቻቸውን ከኦሮሞ የግዛት ፍላጎት የሚተርፉ ጥቅም አልባ የማድረግ ቡድናዊ ፍላጎት መሸከሙ ልዩ ነው።
እንደቀደሙት መንግስታት፡ ወደኢትዮጵያ በሚካተቱ እና ከኢትዮጵያ በሚቀነሱ ግዛቶች ላይ ሳይሆን ወደኦሮሚያ በሚጠቃለሉ ግዛቶች ላይ የሚሠራ ነው።

ከኢትዮጵያ አጎራባች የሆኑ አገራት ለምሳሌ ጅቡቲ፣ ደቡብ ሱዳን ፣ እና ሌሎችም ከኢትዮጵያ አንፃር ሳይሆን ለኦሮሚያ በሚኖራቸው ፋይዳና ተጎራባችነት እየተሠሉ እና እየተሠላላቸው መሆኑ በክፍለዘመኑ የተለየ ገጠመኝ ነው።

ኢትዮጵያ የstate formation ይሁን nation formation ወይም ለፖለቲካ እንደሚነገድበት ለMultination building ያልታደለች፡ ውስጧንና ዙሪያዋን መሬት ስትቀድ እና ስትሰፋ ቀጥላለች።
የሔዱ የመጡት ሁሉ ከአዲስ የstate formation አላማ ስለሚነሱ ፡ የNation/MultiNation ግንባታ ጉዳይ ሳይጀመር የሚጨነግፍ እንግዳ ነገር ሆኗል።

ረጅም የመንግስትነት ታሪክ ተሸክማ ፣ በቅኝ ገዢዎች ፈቃድ ሳይሆን በነገስታቶቿ አቅም፣ በአቢዮት እና ዝግመት ፡ግዛተ-መንግስቷን የመሠረተች ጥንታዊት አገ፡ ከትናንት አገር ጀመሪዎች በባሰ የውድቀት አዙሪት የምትወዛወዝ አሳዛኝ አገር ሆናለች።

ጉልበት ደግሞ የእቅዱ ማስፈፀሚያ ነውና የዜጎቿ ስቃይና ደም መፍሰስ ሁሌም እንደቀጠለ ነው።

አማራ፥ ለዘመናት በተለያዩ አካላት ፍላጎቶች የሙከራ ውጣ ውረድ ከመድማትና ከመቀጣት ወጥቶ ስለራሱም ስለኢትዮጵያም ለማሰብ የዘገዬ የቤት ሥራ ላይ ነው።

በኢምፔሪያል ኢትዮጵያ እንደነበረው ዘመን ያለ ሳይሆን፣ ከአማራዊ ፍላጎት የሚነሳ፡ የአማራ እና የኢትዮጵያ state formation እና Nation building አላማችንን በግልፅ ልንመክርበትና ልናሠምር ይገባል።
አስቸኳይነቱ ለትናንት ነው
242 views18:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-14 11:02:19
በትምህርት ቤት መገኘት ሲገባቸው በአገራቸው ተፈናቃይ ያደረጋቸው ጠላት ነው !!
ጠላታቸውም የኦሮሞ ብልፅግናን የሚመራው ዘረኛ አስተሳሰብ እና ፋሽስታዊ ቡድን ነው!!

#EthnicCleansing
#AmharaMassacre
#AmharaIDP
#ጠላታችን_በክንዳችን!
#ድል_ለአማራ!!
404 views08:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-14 10:28:40
"ኢትዮዽያ ዝም አለችን ፤ ሀገራች ከዳችን"
- - -
አቶ ንጉስ ማለደ ከ ነቀምት ዋዩ ጡቃ ወረዳ ቦኒያ ሞሎ ቀበሌ ተፈናቅለዉ ደብረብርሃን መጠለያ ዉስጥ ይገኛሉ ። እኔም ያሉበትን ሁኔታ እያየሁ ልቤ ተሰብሮ ማዉራት ጀመርኩ ።

የደረሰባቸዉን የግፍ ግፍ ነገሩኝ ። በወሪያቸዉ መሃል “ኢትዮዽያ ዝም አለችን ፤ ሀገራች ከዳችን ። አማራ ሀገሩ የት ነዉ ? ወላሂ ተስፋ ቆርጫለሁ ። ” አሉኝ ።
እሳቸዉን እያየሁ እንባ ከማቅረር ዉጪ አማራጭ የለኝም ።

ይሄ ሁሉ ግፍ ሲዘንብባቸዉ ምንም ማድረግ አልቻልንም ። ባንታደጋቸዉ እንኳን በአግባቡ ድምፅ አልሆንናቸዉ ። ለዚሁ ሁሉ ጭፍጨፋ ተጠያቂዉ የጠሚዶ ዐብይ የሚመሩት መንግስት እና የኦሮሚያ ክልል ነዉ። እኛስ ነገ ትዉልድ ሲጠይቀን ምን ብለን እንመልስ ይሆን ?

በመጨረሻም አቶ ንጉስ የጠየቁኝን ጥያቄ መልሼ ለራሴ ጠየቅኹት “ አማራ ሀገሩ የት ነዉ ? ”

Nathanael Ketema
404 viewsedited  07:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-13 11:26:36
461 views08:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-13 11:26:29 አማራውን በቋሚ የቀውስ አዙሪት የማድቀቅ ሴራ ሊቆም ይገባል!!!

በአገራችን ተንሰራፍቶ የኖረውን አፓርታይዳዊ የህወሃት የበላይነት ለማስወገድ የአማራ ህዝብ የደም መስዕዋትነትን ከፍሏል፡፡ይህ የደም መስዕዋትነት በአማራ ክልል ከተሞች የበርካታ አማራ ወጣቶችን ደም ያፈሰሰ ነው፡፡
ለአብነት ያህል በባህርዳር ከተማ በአንድ ጀምበር ብቻ ከ75 በላይ ወጣቶች ደማቸው ፈሶ ከጣና ጋር እንዲደባለቅ ሆኗል፡፡ በተመሳሳይ በጎንደር ከተማ የለውጥ ፈላጊ ወጣቶች ደም በየአስፋልቱ ሲጎርፍ በወቅቱ በፎቶ ጭምር ተደግፎ የወጣ መረጃ ነው፡፡ በአጠቃላይ ያለ አማራ ህዝብ የደም መስዕዋትነት ለውጥ የተባለው ነገር ጨርሶ የሚታሰብ አልነበረም፡፡

በዚህ መንገድ የመጣው ለውጥ መሰል ነገር እንዲፀናም የአማራ ህዝብ ግንባር ቀደም አጋርነቱን ለማሳየት የልጆቹ ደም በፈሰሰባቸው የአማራ ክልል ከተሞች ባደረገው ትዕይንተ-ህዝብ ዘር ሳይቆጥር ለውጥ የሚያመጣን ሁሉ ደግፏል፡፡
የአማራ ህዝብ ይህን ድጋፉን ያሳየው ጠላቶቹ እንደሚየስቡት ተላላ ስለሆነ አልነበረም፡፡ ይልቅስ ለውጥ የተባለውን ነገር በደሙ ያመጣው የለውጡ ግንባር ቀደም ባለቤት ስለሆነ፣ ለውጡ እንዳይስተጓጎል ካለው ጥንቃቄ ነበረ፡፡

ነገር ግን የአማራ ህዝብ ለለውጡ ስምረት ሲል ያደረገው ከፍተኛ የአጋርነት ስሜትና ሆደሰፊነት እንደ አላዋቂ ተላላነት አስቆጠረው፡፡ ይህም ለውጡን እንመራለን ብለው ስልጣን በያዙ ሰዎች አፍ በአደባባይ እስከመነገር ደረሰ፡፡
በአማራ ህዝብ የደም መስዕዋትነትና ሁለንተናዊ አጋርነት የመጣውን ለውጥ ለመምራት ወንበር ላይ የወጣው የኦሮሞ ገዢ ቡድን ወንበሩ ላይ በቅጡ ተደላድሎ ሳይቀመጥ ነበር የአማራን ህዝብ በተላላነት መዝለፍና ማቃለል የጀመረው፡፡ ዘለፋና ማቃለሉ አማራን በማንነቱ ለይቶ ወደ መጨፍጨፍ፣ ማፈናቀልና ማሳደድ ጥላቻ ወለድ ጭካኔ የተቀየረውም ወዲያው ነበረ።

ሆኖም የአማራ ህዝብ በትንሽ በትልቁ የማይበረግግ ጠንካራ የስነ-ልቦና ውቅር ያለው ህዝብ በመሆኑ ትናንት አጋር ያለውን አካል ለመንቀፍም የማይቸኩል፣ ከሁሉም በላይ ከራሱ አስበልጦ ሃገሩን የሚወድ የሃገር ምንነትን በውል የተገነዘበ፣ ታሪካዊ ዳራውም ጊዜያዊ ችግርን ተቋቁሞ ሃገረ-መንግስት ጠብቆ የማቆየት ልዕልና ያለው በመሆኑ እየተደረገበት ያለውን በደል ለሃገረ-መንግስቱ ህልውና ያገዘ መስሎት በትዕግስት ተሸክሞ አራት አመታትን አስቆጥሯል፡፡

ሆኖም ፖለቲካ ማለት አማራን ማሳደድ የሚመስለው የኦሮሞ ገዢ ቡድን አሁንም የአማራን ህዝብ ትዕግስት ከፍርሃት በመቁጠር የአማራን ህዝብ አንገት ለማስደፋት ያግዘኛል ያለውን አስነዋሪ ስራ ሁሉ በባለውለታው የአማራ ህዝብ ላይ መፈፀሙን ቀጠለ፡፡ በቤኒሻንጉል የአማራ ህዝብ በጅምላ ተገድሎ በስካቫተር ሲቀበር፣ ወለጋ በተባለው የኦሮሚያ ክልል አማራው በየደቂቃው እየሞተ በየእለቱ ሲፈናቀል ምንም አይነት የተጠያቂነት ስራ ያልሰራው መንግስት በአማራ ህዝብ ላይ በሚፈፅመው ግፍ ዋነኛ ባለሚና እንደሆነ ማረጋገጫ ነው፡፡

አገዛዙ አማራውን በቋሚ ቀውስ አዙሪት የማሰቃየት ተልዕኮ ይዞ እየሠራ ነው፡፡ በመሆኑም ከወያኔ ዘመን በቀጠለ ሁኔታ በአማራ ህዝብ ላይ የያዘው አስከፊ እና አስጸያፊ ዓላማ የተገለጠ ስራ ማድረጉ ፀሃይ የመታው ነውር ሆኗል፡፡ የአማራ እንቂዎችን፣ ወጣቶችን ፣ ተቆርቋሪዎችን እያሳደደ በማሰር አማራውን ያለመሪ የማስቀረቱን ተግባር ተያይዞታል፡፡
ኦሮሞ መር የሆነው ስርዓት በአማራ ህዝብ ላይ እያደረሰ ያለውን ዘር ማጥፋትን እና ዘር ማፅዳትን የጨመረ አስከፊ በደል ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጭምር እየታዘበ ነው፡፡
ይህ አልበቃ ብሎ የአማራ ህዝብ ሞቶ ባመጣው የስርዓት ለውጥ፡ መድረሻ እንዲያጣ ሁለንተናዊ ጥቃት እየደረሰበት ነው፡፡ አማራነቱን የሚገልፅ መታወቂያው የመሳደድ፣ የመገደል እና የመጉላላት ምንጩ ሆኗል፡፡

የአማራ ህዝብ በምድር ትራንስፖርት ወደ ሃገሩ ዋና ከተማ መግባት እንደማይችል ስለሚያውቅ እጥፍ ድርብ ክፍያ ከፍሎ በአየር ትራንስፖርት መጓዝን መርጧል፡፡ ከአማራ ክልል እቃ ጭነው ወደ አዲስ አባባ የሚመጡ የከባድ መኪና ሾፌሮች ግማሽ የመሞት ግማሽ የመትረፍ እድል ይዘው ይጓዛሉ፡፡ ይህ ቅር አትበለው እንዲቀር አድርገው ሴራ ነው፡፡

ደክሞ ባቆማት ሃገር ዋና ከተማ እንዳይገባ ከመከልከል አልፎ በአዲስ አበባ ከተማ ሠርቶ የመኖር መብቱ በዚሁ ጨካኝ አገዛዝ ክልከላ ተጥሎበታል፡፡
በአመዛኙ የአማራ ወጣቶች የተሰማሩበት በአዲስ አበባ ዙሪያ የሚሠሩ የባለሶስት እግር ባጃጅ የትራንስፖርት አገልግሎት ከነጭራሹ ስራ እንዲያቆም ተደርጓል፡፡
በተመሳሳይ በአዲስ አበባ የበግ ንግድ እና የሽመና ስራን ጨምሮ በርካታ የአማራ ተወላጆቸን ከስራ በማስተጓጎል ከኦሮሚያ እና ከአዲስአበባ የማስወጣት ፀረ-ህዝብ ደባ እየተፈፀመ ይገኛል፡፡
ሸገር በሚል ስም በአዲስ አበባ ዙሪያ ሊገነባ የታሰበው ፕሮጀክትም ስራውን የጀመረው የአማራ ተወላጆችን ቤት አፍርሶ ከነልጆቻቸው ሜዳ ላይ አውጥቶ በመበተን ነው፡፡

በአዲአበባ የሚከበሩ በዓላት አማራን ማሳደጃ እና ማጥቂያ ከተደረጉ ውለው አድረዋል፡፡ በቅርቡ ከህግ ውጭ በምኒልክ አደባባይ እንዳይከበር ገዢው የኦሮሞ ኃይል በከለከለው የአድዋ በዓል የሽመና እና አልባሳት አምራቾችን ከማሠር እና ማጉላላት አልፎ በዓሉን ለማክበር በምኒልክ አደባባይ የተገኙ ዜጎች ላይ ነውረኛ ተግባሮችን ፈፅሟል፡፡

በአጠቃላይ ስልጣን የያዘው የኦሮሞ ገዢ ቡድን አማራው አንገቱን እንዲደፋ፣ መሪ እንዳይኖረው፣ ደክሞ ያፈራውን ንብረት እንዲያጣና ጠንካራ የስነ-ልቦና ውቅሩ በድህነት እና ተስፋ ማጣት እንዲኮላሽ፣ በእጁ የያዘውን ሁሉ እንዲጥል እየሰራ ይገኛል፡፡
ይህ መንግስትነትን የማይመጥን እኩይ አካሄድ ውጤቱ እንደታሰበው የአማራን ህዘብ ብቻ ለይቶ ማድቀቅና ማዋረድ አይሆንም፡፡ ይልቁንስ ሠፊው የአማራ ህዝባችን በጨቋኙ አገዛዝ ላይ ለላቀ ትግል እንዲነሳ የሚያደርግ እንጂ ከቶውንም አንገት እንዲደፋ ሊያደርገን አይችልም፡፡

ስለሆነም የአገዛዙ ክፋት እና ጥቃት ሰለባ የሆኑት ኢትዮጵያውያን ሁሉ አገዛዙ የገባበትን ጨካኝ ፀረ-ህዝብ ተግባር ለማስቆም የተለየ ጥረት እንዲያደርግ እንጠይቃለን፡፡
ሰፊው የኦሮሞ ህዝብ በስሙ ወንበር የያዘ አምባገነን ስብስብ በህዝቦች መካከል ጥላቻ እና ጠላትነትን እየዘራ መሆኑን በማሰብ በቃ እንዲሉት ወንድማዊ እና እህታዊ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡
ሰፊው የአማራ ህዝባችን እንደከዚህ ቀደሙ ሁሉ የአምባገነኑን ግፎች ለማስቆም እና ሁለንተናዊ ጥያቄዎቹን ለማስመለስ ለመታገል አንድነቱን አፅንቶ እንዲቆም ጥሪ እናቀርባለን፡፡

የህዝብ ትግል ያሸንፋል!

የአማራ ወጣቶች ማህበር
የአማራ ተማሪዎች ማህበር
የአማራ ጤና ባለሙያዎች ማህበር


መጋቢት ፬/፳፻፲፭ ዓ.ም
436 views08:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-13 09:42:39

450 views06:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ